cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሁሉን አቀፍ / hulun akef

ይህ ቻናል ዋና አላማ ያለን መጠቀም የተረሳን ማስታወሰ ነዉ። ፍቅር ደስታ ተስፋ ለእናንተ ለእኛ ለሁላችን ይሁን።

Show more
Advertising posts
387Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በቅድሚያ እንኳን ለ2016ዓ.ም የዘመን ዘመን መለወጫ ባሕል አደረሳችሁ !!! አደረሰን እያልኩ ዘመኑ ያለፀብ በፍቅር ያለ ሕመም በጤና ያለ ሐሜት በፀሎት ያለቂም በይቅርታ ያለስስት በምፅዋት ያለ እርኩሰት በቅድስና እንዲሆንልን ፈጣሪ ይርዳን!!! #ማስሬ🙄 ውብ ለሊት ይሁንልን😍🙏🙏🙏 share us 👇👇👇👇👇👇 @hulemalemedia @hulemalemedia @hulemalemedia 👆👆👆👆👆
Show all...
🥰 1
Repost from N/a
አዎ! ሁሉም ነገር በጥሩ ሁኔታ እየሰራ ነው ሁሉም ሰው ቀድሞውኑ በ 200 ETB ለ CBE ቻናል ተመዝግቧል! CBE Telegram ቻናልን ሰብስክራይብ በማድረግ 200 ብር ያግኙ! ቻናል እዚህ አለ። 🇪🇹👇
Show all...
ቀላል 200ETB! ቻናሉን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
ከዜሮ መጀመር ትችላለህ!!! ____ ● ያለንን ነገር ሁሉ ብናጣ ፡ የተመካንባቸው ሰዎች ቢርቁን ፡ በሽታ ቢያሰቃየን ፡ የባንክ አካወንታችን ባዶ ቢሆን ፡ ተስፋ የሚያስቆርጡ ነገሮች ቢከሰቱብን ፡ ሁሌ ከዜሮ መጀመር ይቻላል። ● እድሜያችን ቢገፋ እንኳን በልጅነታችን የተመኘነውን ማንነት በየትኛውም ጊዜ መገንባት እንችላለን ። ከኛ የሚጠበቀው ለመለወጥ ያለን ቁርጠኝነታችን ፡ ፅናታችን ፡ እምነታችንና ትዕግስታችን ነው። ማትኮር ያለብን ችግሩ ላይ ሳይሆን ወይም ስለችግሩ ማልጎምጎም ሳይሆን ችግሩን ለመፍታት የሚረዱንን መሰረታዊ ጽንስ ሀሳቦች ቁርጠኝነት ፡ ጽናትና ፡ ትዕግስት ላይ ነው። ● የሕይዎትህ መለወጫ መሪ ያለው በራስህ እጅ ላይ ነው። ሌሎችንና ሌላ ጊዜን አትጠብቅ። ጊዜው አልፏል ብለህም አትቁም ፡ ያንተ ጊዜ አሁን ነው። ጉዳይህ ያለቀና ያበቃለት ቢመስልም አንተ ከጠነከርክ እንዲሁም ከልብህ ፡ እኔ አሁንም ተስፋ አለኝ ብለህ ከባዶ የመነሳቱ ድፍረቱ ካለህ ያኔ አንተ አንፀባራቂ ብርሀንን ታያለህ። ራስህንም ድሮ ከነበርክበት ባዶነት አውጥተህ እንደገና ሕይዎትን የመኖር ፅንሱን ውስጥህ ትፀንሳለህ። ● ያኔ አንተ ተቆርጠህ ከተጣልክበት ትቢያ እንደገና አገግመህና ፡ አቆጥቁጠህ ትታያለህ። ልምላሜህም ከበፊቱ የበለጠ ይሆናል። ቅርንጫፎችህ ፡ ተቆረጡ እንጂ ዋናውን የሕይዎት ምስጢር የያዘችው አንተን ከአፈሩና ፡ ከውሃው የምታገናኝህ ስራህ አልተቋረጠችምና እንደገና ትለመልማለህ። እንደገና እራስህን በእድገት ምናብ ከዋጀኽው በድጋሚ ታብባለህ። ● በድጋሚ ቀንበጥ ፡ ቀንበጥ የሆኑ የሚያስጎመጁ ፡ አረንጓዴ ቅጠሎችንና ፡ ቅርንጫፎችን ፡ ታቆጠቁጣለህ። ግመል በበረሓ ስትጓዝ በረሓው ላይ ውሃ እንደሌሌ ታውቃለች። ግን ወደ በረሓው እንድትገባና ፡ እንድትጓዝ ስናደርጋት ፡ ወደ ኋላ አታፈገፍግም ወይም አትፈራም። ምክንያቱም ፡ የሻኛው ጮማ ውስጥ በቂ የሆነ ምግብና ፡ ውሃ እንዳለ እርግጠኛ ስለሆነች እሷ የምትዘጋጀው ከበረሓው ፡ ከመግባቷ በፊት ውስጧ ምግብ በማጠራቀም ነው። ● አንተም እንደ ግመሏ ውስጥህ ላይ አትኩር። ሌሎችን የበረሓው ግለት ፡ የበረሓው ንዳድ ፡ የበረሓው አሸዋና ፡ የበረሓው መጨረሻ መራቅ ተስፋ ቢስ ሲያደርጋቸው ፡ አንተ ግን ለድል አነሳሳቸው ፡ ውስጣቸው ያለውን የአሸናፊነት  ጮማ ፡ የተስፋ ጮማ ፡ የፍቅር ጮማ ሻኛ እንዳለ ንገራቸው። አንተ ከፊት ሆነህ ባለህ የዕውቀት ፡ የፅናት ፡ የትዕግስት ፡ ብረሀንህ ጉዟቸውን አቅልጥላቸው። ● ያኔ የተቆረጠው ፡ የወደቀው ፡ የተረሳውና የተናቀው ማንነታቸው እንደገና ያቆጠቁጣል። በ "አይሳካም" ስሜት ሊደመደም ፡ የነበረውም ጉዞ ይቀጥልና ፍጻሜውን ያገኛል። ባዶ ነው ፡ ጭር ያለ ነው ፡ ትርጉም አልባ ነው ፡ ያልነው ሁሉ የኢላማችንን አቅጣጫ ስናስተካክል እናደገና ዜሮ ፡ አንድ ፡ ሁለት ፡ ሦስት ....እያለ መቁጠር ይጀምራል። ● አንተ ራስህን ከምንምና ፡ ከባዶ አንስቶ ለትልቅ ደረጃ የሚያበቃ አቅም በውስጥህ አለ። አንድ ልታውቀው የሚገባህ ትልቅ ቁምነገር ፡ ዜሮ ፡ የቁጥሮች መጨረሻ ሳይሆን ፡ የቁጥሮች መጀመሪያ መሆኑን ነው። ያለህ ነገር ሁሉ ዜሮ የሆነ ከመሰለህ ፡ እንግዲያው አንተ ደስ ሊልህ ይገባል። ምክንያቱም ፡ በህይዎትህ ያለህ ደስታ ሁሉ ፡ ያለህ ሀብት ሁሉ ፡ ያለህ ዝና ሁሉ ፡ ያለብህ ገንዘብ ሁሉ ፡ ያለህ ተቀባይነት ሁሉ ፡ እንደገና ከዜሮ ፡ መጨረሻ ፡ ወደሌለው ቁጥር "ሀ" ብሎ ሊንደረደር ነውና !!!!!! #ማስሬ🙄 ውብ ለሊት ይሁንልን😍🙏🙏🙏 share us 👇👇👇👇👇👇 @hulemalemedia @hulemalemedia @hulemalemedia 👆👆👆👆👆
Show all...
https://www.youtube.com/@hulunakefmedia3443 በአዲስ መልክ ስራ ልንጀምር ስለሆነ subscribe በማድረግ እንተባበር 1k*
Show all...
እንኳን ለ1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
Show all...
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!
Show all...
ከባዱን ተሻገር! ፨፨፨//////፨፨፨ ተሰብሮ መኖር ከባድ ነው፤ ይቅርታ አለማድረግ ከባድ ነው፤ ስራ ማጣት ከባድ ነው፤ ወገን ማጣት፣ ረዳት ማጣት እጅግ ከባድ ነው። ነገሮች እንዳሰቡት ሳይሆኑ ሲቀሩ፣ እቅዶች አልሳካ ሲሉ፣ መንገዶች ሁሉ ምቾት ሲያጡ፣ ሸክሞች ሲበዙ፣ ጫናዎች ሲያይሉ ተስፋ አስቆራጭ ከባድ የህይወት ከስተቶች ከፊታችን ይደቀናሉ። ለአመታት የለፋንበት ትምህርት በቀናት ወይም በወራት ውስጥ ፍሬ አፍርቶ መመልከት እንፈልጋለን። ለረጅም ጊዜ አብሮን የነበረ ሰው በአንዴ ሲለየን በቅፅበት ልንረሳው እንሞክራለን፤ የፈተናዎችን እድሜ ማሳጠር፣ ችግራችንን ወዲያው መቅረፍ የሁልጊዜ ምኞታችን ነው። የደስታ ሰዓታት ቢረዝሙ፣ የፈተና ጊዜያት ቢያጥሩ መልካም ነበር። ነገር ግን ከባዱም ቀላሉም ነገር የእራሱ ቀነ ገደብና የተመጠነ ጊዜ አለው። ገፍተህ ወይም ሸውደህ የምታልፈው የፈተና ወቅት የለም፤ ይዘህ የምታቆየውም የደስታ ጊዜ አይኖርም። እጅጉን በብዙ ጥበቃህን የፈተነ፣ እንቅልፍህን ያሳጠህ ነገር ካለ የትኩረት አቅጣጫህን ቀይረው፤ እርሱ ካለሆነ ብለህ በጥበቃ ብዛት ሰውነትህን አታዝለው። ብዙ አሻጋሪ አማራጭ መንገዶች እንዳሉ ተመልከት። ቀጥተኛ መንገድ ባለሙያ አሽከርካሪ እንደማይፈጥር ሁሉ የተስተካከለና የተመቻቸ አካሄድም ሊያጠነክርህና ሊያሻሽልህ እደማይችል አስብ። ከባዱን ተሻገር! በፅናት ተፋለመው፤ በትግስት ተጋፈጠው፤ እራስህን አበርታ። ከባድ መሆኑን እንደማይታለፍ አትቁጠረው፤ አስቸጋሪ መሆኑ እንደማያልፍ አይሰማህ። የማያልፍ የለም፤ የማይረሳ፣ የማይዘነጋ ጊዜ አይኖርም። አስጨናቂ ሰዓታት ይረዝማሉ ምክንያቱም ሙሉ ትኩረታችን ጉዳዩ ላይ ስለሆነ፤ አስደሳች ጊዜያት ያጥራሉ ምክንያቱም ቅፅበቷን ከማጣጣም ይልቅ የማለቂያዋን ጊዜ ስለምንጠብቅ። አንተ ጋር የመጣ ሁሉ የሚታለፍ፣ የሚረሳ ነውና በቶሎ እጅ አትስጥ፤ ለመሰበር አትጣደፍ፤ ካንተ የቀረ ከሌለ አምላክህ የሚያስብልህን ጠብቅ፤ የእርሱ ምርጫ እንደሚስማማህ አትጠራጠር፤ በፅናትና ትዕግስትህም ተማመን። #ማስሬ🙄 ውብ ለሊት ይሁንልን😍 share us 👇👇👇👇👇👇 @hulemalemedia @hulemalemedia @hulemalemedia 👆👆👆👆👆
Show all...
"በማንነቴ አመስጋኝ ነኝ" ፨፨፨፨፨/////////፨፨፨፨፨ በእራስ ማስታወሻ እራስህን ቃኝ፤ ወደውስጥ ተመልከት፤ መንፈስህን አግኘው፤ ትክክለኛውን አንተ አናግረው እንደዚህም በለው፦ " እኔ ማንም አይደለሁም፤ እኔ እኔ ብቻ ነኝ። ምርጫዎች አሉኝ፤ ፍላጎቶች አሉኝ፤ መኞት፣ ህልም፣ ራዕይ አለኝ፤ መንገዴን አውቃለሁ፤ መድረሻዬም ግልፅ ነው፤ የሚጠበቅኝና የማደርገው ተስማምተውልኛል፤ ደስታ አለኝ፤ እርጋታ ውስጥ ነኝ፤ የሚያስጨንቀኝን ጥዬአለው፤ የሚያሳርፈኝን ተቀብዬአለው፤ በስራዬ ምስጉን በማንነቴም አመስጋኝ ነኝ። እራሴን በጣም እወዳለሁ፤ አከብራለሁ፤ እንከባከባለሁ፤ አስብለታለሁ። ነፍሴ እርካታ አላታ፤ ውስጤ ባለው ነገር በጣም ደስተኛ ነው፤ ቢኖረኝ እያልኩ በባዶ የምመኘው ነገር የለም፤ እንዲኖረኝ ዋጋውን እከፍላለሁ፤ የእራሴን ድንቅነት ለእራሴ አረጋግጬያለው። ማነህ ብባል የማላፍርበት ማንነት፣ የት ነህ ብባል የማልሳቀቅበት ማረፊያ ገንብቼያል። መንፈሴን አደምጣለሁ፤ ለእርሱ ተገዝቼያለሁ። አምላክ ፍቅሩን በእኔ ገልጿል፤ መውደዱን እስከ ጥግ አሳይቶኛል፤ ከፈተና ነጥሎኛል፤ ከመከራ አውጥቶኛል፤ ከጥፋት ገላግሎኛል፤ ለዛሬ ልዩ ቀን አብቅቶኛል። አመሰግነዋለሁ! አዎ! እርሱን ህያው አባቴን አምኜ መቼም አላፍርም፤ ብገፋውም አልተወኝም፤ ብሸሸውም ከእኔ አልራቀም፤ ብገዳደረውም፤ ብፈታተነውም ጠብቆቱ አልተለየኝም። ድንቅ፣ ሩህሩህ አባት አለኝ፤ መቼም እንደማይረሳኝ አውቃለሁ፤ ፍቅሩን በውስጤ ዘርቷል፤ በመንፈሱ ገዝቶኛል፤ ወዶኛል፤ አክብሮኛል፤ አሳርፎኛል፤ ድንቅና ብርቱ አድርጎኛል፤ ከወደኩበት አንስቶ፤ ካቀረቀርኩበት ቀና አድርጎ በሁለት እግሬ አቁሞኛል። የምመካው በአምላኬ ነው፤ በእራሴ ነው። የምኮራው በአባቴ ነው፤ በእራሴ ነው። የተሰጠኝ ብዙ ነውና፣ የተደረገልኝ ይበልጣልና የጎደለኝ አያስጨንቀኝም። በእራሴ እገረማለሁ፤ መነሻዬን ሳስብ እደነቃለሁ፤ ዛሬ ያለሁበት ስፍራም መጨረሻዬ አለመሆኑን ሳስብ በእራሴ እኮራለሁ። አምላክን አሳስቤያለሁ፤ ተማፅኜያለሁ በእራሱ መንገድ፤ በመረጠልኝ ጎዳና መልካሙን ሃሳቤን፣ ትልቁን ህልሜን ያሳካልኝ ዘንድ ጠይቄዋለሁ፤ አሁን ወደፊት እጠይቀዋለሁ፤ እንደሚያደርግልኝም አውቃለው፤ በሙሉ ልብ አምናለሁ። አሁን የሆንኩትን ሰው ስላደረገኝ ዘወትር አመሰግናለሁ፤ ከእኔ ጋር ስለሆንክ ሁሌም አመሰግናለሁ፤ አምላኬ፣ አባቴ እወድሃለሁ፤ ፍቅር ሆነ ፍቀርን ሰተሀኛልና በእየቀኑ አመሰግንሃለሁ።" እያልክ መንፈስህን አድስ፤ እራስህን አግኝ፤ አምላክህን አክብር፤ ስሜትህን ግዛ፤ ማንነትህን ውደድ፤ በእራስህ ተደነቅ፤ ደስታህን ፍጠር፤ ነፍስህን በሃሴት ሙላት፤ ቀንህን አሳምር፤ ያለህን አወድስ፤ አመስጋኝ ልበ ቀና በመሆን ወደፊት ብቻ ተራመድ። #ማስሬ🙄 ውብ ለሊት ይሁንልን😍 share us 👇👇👇👇👇👇 @hulemalemedia @hulemalemedia @hulemalemedia 👆👆👆👆👆
Show all...
እንኳን ለ127ኛው የአድዋ ድል ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
Show all...
_እንኳን ለ2015 የአብይ ፆም በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ፆሙ የፍቅር፣ የሰላም፣ የበረከትና የአንድነት እንዲሆንልን ከልብ እንመኛለን። ፆም ነፍስን ታበረታለች፤ መንፈስን ታድሳለች፤ ከአምላክ ታስታርቃለች፤ በረከትንም ታድላለች። #ማስሬ share us 👇👇👇👇👇👇 @hulemalemedia @hulemalemedia @hulemalemedia 👆👆👆👆👆
Show all...