cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

✨✨ኮቻ ታይምስ✨✨

ስለኮምቦልቻ እና አካባቢዋ ወቅታዊና አሁናዊ ሁኔታ ይከታተሉ ግሩፕ ለመቀላቀል👇 https://t.me/joinchat/WU8HqsdKu7JKDVGJ

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
179Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#ነፃ_ዋይፋይ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ፣ እንጦጦ ፣ አንድነት ፓርክ እና የወዳጅነት አደባባዮች በከፍተኛ ወጪ የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት ገንብቶ በነጻ ማቅረቡን ዛሬ ገልጿል። @kochatimes
Show all...
#Update ከደሴ እስከ ወልዲያ ያሉት ከተሞች ኤሌክትሪክ አግኝተዋል። ከደሴ እስከ ወልዲያ ሲከናወን የቆየው ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መስመሮች የመጠገን ሥራ ትናንት ምሽት ተጠናቆ ከተሞቹ ከ 10:05 ጀምሮ ኃይል አግኝተዋል። ጥገናው ትናንት ምሽት ቢጠናቀቅም መስመሩ በሚያልፍበት አካባቢ በደሴ እና በሀይቅ መካከል እንዲሁም መርሳ አካባቢ የበቀለ ዛፍ ከመስመሩ ጋር ተገናኝቶ ባለመቆረጡ የተነሳ ኤሌክትሪክ ማገናኘት አልተቻለም ነበር። ይሁንና ዛሬ ዛፎቹ በመቆረጣቸውና ኃይል ለመስጠት የሚያግድ ነገር ባለመኖሩ ከተሞቹ ኤሌክትሪክ ማግኘት ችለዋል። በተጨማሪ ፥ ለወልዲያ ከተማና አካባቢው አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶ የተዘረፈው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚሰጠውን አገልግሎት የሚተካ ዘላቂ ሥራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጀምሯል። የተጀመረው ሥራ በቀጣዮቹ ከ4 እስከ 5 ወራት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ከፍተኛ ኃይል ለመስጠት የሚያስችል ነው። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል @kochatimes
Show all...
#Update የደሴ - ወልዲያ የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና እየተገባደደ ነው። ፍተሻው በስኬት ከተጠናቀቀ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች በሰዓታት ውስጥ ኤሌክትሪክ ሊያገኙ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል። ተቋሙ እስከዛሬ ድረስ በተከናወነው ጥገና ጉዳት የደረሰበት መስመርና ምሰሶ ከ97 በመቶ በላይ ተጠናቋል ብሏል። ቀሪ ሥራዎችን በርብርብ በማጠናቀቅ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች ማምሻውን አልያም እስከ ነገ እኩለ ቀን ድረስ መብራት እንዲያገኙ ይደረጋል ሲል አሳውቋል። @kochatimes
Show all...
በሳምንት ከአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚከለክለው መመሪያ ማንሳቱን ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ‼️ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሳምንት ከአምስት ጊዜ በላይ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚከለክለው መመሪያ መነሳቱን ይፋ አድርጓል። ብሔራዊ ባንክ ካለፈው ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ የባንኮች ደንበኞች በሳምንት ከአምስት በላይ የባንክ ዝውውሮችን እንዳያደርጉ የሚያዝ መመሪያ ማውጣቱ ይታወሳል። ይህም መመሪያ መደበኛ ባልሆነው የልውውጥ ገበያ ውስጥ ያሉ ተጫዋቾችን ተስፋ ለማስቆረጥ ያወጣው ደንብ መሆኑን አስታውቆ ነበር። ይሁን እንጂ ካሳለፍነው ሳምንት ታህሳስ 27 ቀን 2014 ጀምሮ ይህ መመሪያ መነሳቱን በብሔራዊ ባንክ የባንክ ሱፐርቪዥን ዳይሬክተር ፍሬዘር አያሌው፣ መግለፃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። “ የዝውውር ገደቡ አሁን ሙሉ በሙሉ በመመርያ ተነስቷል ” ያሉት ፍሬዘር፣ ነገር ግን ባሳለፍነው ዓመት የወጣው የገንዘብ ወጪ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ገደቦችም አሁንም ድረስ ተፈፃሚ ሆነው ይቀጥላሉ ሲሉ ተናግረዋል ። © አዲስ ማለዳ @kochatimes
Show all...
#Update የነጩ ቤተመንግስት (ዋይት ሀውስ) መግለጫ ፦ ዋይት ሀዋስ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ከኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በስልክ መወያየታቸውን አሳውቋል። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በኢትዮጵያ ስላለው ግጭት እና ሰላምና ዕርቅን ለማስፋት በሚደረገው ጥረት ላይ መክረዋል። ፕሬዝዳንት ባይደን በቅርቡ ስለተፈቱት በርካታ የፖለቲካ እስረኞች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ምስጋና አቅርበዋል። ሁለቱ መሪዎች በድርድር የተኩስ አቁም ስምምነትን ማፋጠን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፣በመላው ኢትዮጵያ የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦትን በአስቸኳይ ስለማሻሻል ፣ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ስር ስለታሰሩ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ሁሉም የተጎዱ ኢትዮጵያውያን የሰብአዊ መብት ጥያቄዎችን መፍታት በሚያስፈልግበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። ጆ ባይደን በቅርቡ የተፈጸሙትን የአየር ድብደባዎች ጨምሮ እየቀጠለ ያለው ግጭት በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳትና ስቃይ እያስከተለ እንደሚገኝና ይህም እንደሚያሳስባቸው ገልጸው አሜሪካ ከአፍሪካ ህብረት እና ከአካባቢው አጋሮች ጋር በመሆን ኢትዮጵያውያን ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ለማድረግ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ሁለቱም መሪዎች የ #አሜሪካ እና #ኢትዮጵያ ግንኙነት አስፈላጊነት፣ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያለውን ትብብር ለማጠናከርና ግጭቱን ለመፍታት ተጨባጭ እርምጃ እንደሚያስፈልግ አስምረውበታል። @kochatimes
Show all...
#Update በኢትዮጵያ 🇪🇹 የመጀመሪያ የሆነውን የፊልድ ማርሻል ወታደራዊ ማዕረግ ለጀነራል ብርሃኑ ጁላ ተሰጠ። በተጨማሪ ፦ • 4 ሌትናል ጀነራሎች ወደ ሙሉ ጀነራልነት፣ • 14 ሜጀር ጀነራሎች ወደ ሌትናል ጀነራልነት፣ • 24 ብርጋዴር ጀነራሎች ወደ ሜጀር ጀነራልነት፣ • 58 ኮሎኔሎች ወደ ብርጋዴር ጀነራልነት በአጠቃላይ 100 ከፍተኛ የጦር አመራሮች እድገት ተሰጥቷል። ሹመቱ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አህመድ አቅራቢነት በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በኩል ነው የተሰጠው። መረጃው የኢብኮ ነው። @kochatimes
Show all...
#Update የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፥ በኢትዮጵያ ቁልፍ ተቃዋሚዎችን ጨምሮ በርካታ እስረኞች ከእስር መፈታታቸውን በደስታ እቀበላለሁ ብለዋል። ዋና ፀሀፊው ፥ ሁሉም ወገኖች ግጭት እንዲቆምና ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት በማድረግ ፣ እንዲሁም ተአማኒና ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ውይይትና የእርቅ ሂደት እንዲጀመር በመስማማት ይህን ትልቅ የመተማመን ግንባታ ሂደት እንዲያጎለብቱ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል። ጉተሬዝ ፥ በኢትዮጵያ ግጭት እንዲቆም እና ሰላምና መረጋጋትን ወደነበረበት ለመመለስ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በንቃት እሰራለሁ ሲሉም አሳውቀዋል። @kochatimes
Show all...
#Update እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ከእስር ተፈቱ። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ጃዋር መሀመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ሀምዛ አዳነ ከእስር ተፈተዋል። ከሰዓታት በፊት ከጠበቃቸው መካከል ከሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ እነአቶ ጃዋር መሀመድ ስለመሸ እንደማይወጡ እንደነገሯቸው ለቢቢሲ ቢገልፁም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ከማረሚያ ቤት ወጥተዋል። ሶስቱን እስረኞች የጫነ ተሽከርካሪ የቃሊቲ ማረሚያ ቤትን ለቅቆ የወጣው ከምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ገደማ እንደነበር ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። እስረኞቹን የያዘው ተሽከርካሪ፤ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አባላትን በጫኑ ሶስት ፒክ አፕ መኪናዎች ታጅቦ ወደ ቦሌ አቅጣጫ ሲጓዙም እንደነበር ተገልጿል። እነ ጃዋር ከእስር ሲለቀቁ አቀባበል ለማድረግ በርካታ ደጋፊዎቻቸው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቅራቢያ ሆነው ለሰዓታት ሲጠብቁ ቆይተዋል። ከእነ አቶ ጃዋር ቀደም ብሎ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ ሸምሰዲን ጣሃ ሌሎችም በአቶ ጃዋር መዝገብ ስር ያሉ እስረኞች ተፈተዋል። @kochatimes
Show all...
የእነ ጃዋር መሐመድ፣ እስክንድር ነጋ እና ስብሐት ነጋ ክስ እንዲነሳ የተደረገው በቀጣይ የሚደረገውን ሃገራዊ የምክክር መድረክ ሂደት ውጤታማነት እና አካታችነት ከፍ ለማድረግ በማሰብ መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል‼️ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በእነ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል መዐሾ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ውስጥ እነ ስብሐት ነጋ የጤና እና የዕድሜ ሁኔታን ከግምት በማስገባት ክሱ ተነስቶላቸዋል ብሏል።
Show all...
አቶ ጃዋር መሀመድ ከእስር መፈታቱ ታውቋል።
Show all...