cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

መልካም ምሳሌነት አላማው ለክርስቶስ ተልዕኮ

መልካም ምሳሌነት አላማው ለክርስቶስ ተልዕኮ ይህ channel ለመልካም ስራ የሚውል በመልካም አላማ የተቀናጀ ነው

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
138Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from N/a
እንዲሁ በፀጋ እንዲሁ በነፃ https://youtube.com/watch?v=X1orFShLcmE&feature=share
Show all...
እንዲሁ በፀጋ እንዲሁ በነፃ

✍️አንድ ክርስቲያን በክርስቶስ አምኖ ከዳነ በኃላ በምድር ላይ በዋጋ የተገዛ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ሲሆን የሰማይን ሕይወት እንዲገልጥ እና የክርስቶስ የጽድቁ እና የቅድስናው መገለጫ ለመሆን ተጠርቷል። ነገር ግን በዚህ ደካማ ስጋ ምድር ላይ ሲኖር መድከሙ የማይቀር ነው በሚደክምበትም ጊዜ በሕብረት ንስሃ በድካሙ ሊራራለት ከሚችለው እና ጸጋና ምህረትን ከሚሰጠው ከሊቀካህኑ ከኢየሱስ ጋር መጨረስ ይችላል። ✍️ነገር ግን አንድ ክርስቲያን ከሊቀካህኑ ከኢየሱስ ጋር በንስሃ መጨረስ አቅቶት ቤተመቅደስነቱን ረስቶ #በተገለጠ_ሃጥያት ውስጥ ቢገኝ እና የጌታውንም ስም ቢያሰድብ #በስጋው ጌታ #ይገስጸዋል ፍርድንም ይቀበላል። ✍️
Show all...
የአዲስ ኪዳን መካከለኛ የአዲስ ኪዳን መክከለኛ እንድ እርሱ ሌላ የሌለ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ የሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። " የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።" (ወደ ዕብራውያን 12፥24) " አሁን ግን በሚሻል ተስፋ ቃል በተመሠረተ በሚሻል ኪዳን ደግሞ መካከለኛ እንደሚሆን በዚያ ልክ እጅግ የሚሻል አገልግሎት አግኝቶአል።" (ወደ ዕብራውያን 8፥6) ሰው እና ሰው ቢጣላ በመካከል የሚገቡት አስታራቂዎች ከአንድ በላይ ቢሆኑ ምንም አይደለም። ነገር ግን ጠቡ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ሲሆን ከአንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር በመካከል የሚገባና የሚያስታርቅ ሌላ መካከለኛ (አማላጅ) የለም። እግዚአብሔር አንድ ባይሆን ኖሮ ከምርጫው ብዛት የተነሳ የሰው ልጆች ግራ ሊጋቡ ይችሉ እንደነበር : እንደዚሁ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ባይሆን ወደ እግዜአብሔር የመቅረቢያው መንገድ ዝብርቅርቁ ይወጣ ነበር። በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩትን የመካከለኛነት አገልግሎት ሁሉ አጠቃሎ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ እንዲሆን የተመረቀውና የተሾመው አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ስለዚህ እርሱ ሙሴ አስቀድሞ እግዚአብሔር እንደ እኔ ያለ ነብይ ያስነሳላችኋል ያለው ነብይ ነው።(ዘዳ18፥15-17፣ሐዋ 3፥20-27፣ሉቃ13፤33) እንደ መልከ ጼድቅ የዘላለም ካህን ነው።(ዕብ 5፥6፣ዕብ3፥5፣ዕብ 7፥26፣ዕብ4÷10 የዘላለም ንጉስ ነው። (ሚክ 5፥2፣መዝ 2፡6፣ኢሳ 9፥6-7፣ሉቃ19፥32፣ራዕ 20፥4-5) የሰብአዊ መጠሪያው ስሙ የሆነው "ኢየሱስ" የሚለው ቃል እና መለኮታዊ ስሙ "ክርስቶስ"የሚለው ቃል ሁለቱም መካከለኛነቱን የሚያንጸባርቁ ናቸው። መለኮታዊነቱን የሚገልጸው "ከክርስቶስ" የሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን የቃሉ መሠረታዊ አመጣጥ ግን በብሉይ " መሲህ " ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል ነው ። መሲህ (ክርስቶስ)ማለት የተቀባ ማለት ነው።በብሉይ የሚቀቡት ነቢያት፣ካህናትና ነገስታት እንደነበሩ ሁሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚህን ሦስቱንም ማዕከላዊ አገልግሎት አጠቃሎ ለማሟላት የተቀባ(የተመረጠ) በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለ ብቸኛው መካከለኛ ነው።"ኢየሱስ " ማለት "እዳኝ" ማለት ነው። ኃጢአተኛን ከኃጥያት ዕዳና ፍርድ ነጻ የሚያደርገውና የሚያድነው ከእርሱ በቀር ሌላ ማንም የለም።
Show all...
ሽቶዉን ዉድ ያደረገዉ የብልቃጡ ዲዛይን አይደለም ዉስጡ ያለዉ የከበረዉ መአዛ ነዉ። እህቶቼ እኔንና /እናንተን ዉድና እርካሽ የሚያደርገን ሰዉነታችን አለባበሳችን እስታይላችን አይደለም በሰዉነታችን ዉስጥ ያለዉ የከበረዉ የእግዚአብሔር መዝገብ ነዉ። የብልቃጡ አድናቂዎችአንሁን ማለትም (የቁንጅናን የአካልን) እኔንና እናንተን ዉድ ያደረገን ግን የከበረዉ የእግዚአብሔር ማንነትና ሀሳብ ነዉ። ❤️🤗 ሰዎች የሚፈልጉትም አካላችንን አይደለም በዉስጣችን ያለዉን ነዉ። ያቺ ሴት ይዛ የመጣችዉ ሽቶ ስሰብረዉ በወጥ በሌላም ነገር የከረፋዉን ቤት መአዛ ሞላዉ። እየቀፈፈ ያለዉን የሀገሬን የቤተክርስቲያንም የብዙ ወጣት ህይወት መለወጥ የሚችለዉ ይሔ ስጋችን አይደለም እዛ ዉስጥ ያለዉን የከበረዉ የእግዚአብሔር ዉድ እቃ ነዉ ። ❤️🤗
Show all...
ነጭ ቬሎ ለብሳ ያጌጠች ሙሽሪት ጭቃ ውስጥ ገብታ ብትገኝ። ከጭቃው እንድትወጣ ከተፈለገ በትክክል ማወቅ ያለባት ነገር ምንድን ነው? 👉ጭቃ ውስጥ እንዳለች? 👉ጭቃው በጣም አስቀያሚ እንደሆነ? በእርግጥ እነዚህን ነገሮች ብታውቅ ይጠቅማት ይሆናል። ቢሆንም ግን ከጭቅው እንድትወጣ ማወቅ ያለባት ዋናው ነገር- 👉የለበሰችው ንፁህ፣ ነጭ፣ ውድ እና ጭቃ #የማይመጥነው ልብስ መሆኑን ነው። የልብሱን ንፅህና እና ዋጋ ስትረዳ የት መዋል እንዳለባት ይገባታል። 🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 ከሐጢአት ልምምድ ለመውጣት መፍትሄው በየቀኑ ስለሰራሀው ኃጢአት ዝርዝር ቁጭ ብለህ ማሰብ ሳይሆን አንተ ያለህን #ክብር ማወቅ ነው። #የንጉስ ልጅ መሆኑን ያልተረዳ የንጉስ ልጅ ቆሻሻ ሰፈር ቢውል፣ ለምኖ ቢበላ አይገርምም❗ በየመድረኩ አሁን ያለንበት አዘቅት ይነገረናል። ግን ምን እንደለበስን አይነገረንም። አቤት! በክርስቶስ የለበስነውን ክብር ብናውቅ! ..እንኳን ኃጢአት፡ የምድር ክብሯ እራሱ አይመጥነንም እኮ! 🙏ጌታ አይኖቻችንን ይክፈትልን🙏
Show all...