cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Adiss tv

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
514Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አሳዛኝ ሰቅጣጭ ዜና‼️‼️ 😢😢 ------------------------- የ47 ሰዎች ህይወት በመኪና አደጋ አጣን። ዛሬ ዕለተ እሁድ ጥር 15/2014 ከ ባህር ዳር እና እብናት ከ50 ሠዉ በላይ አሣፍሮ ወደ ሠቆጣ ይጎዝ የነበረ ባስ ምሽ ላይ 150ሜትር በላይ ገደል በመግባቱ አንዲት የ2አመት ህፃን እና ሌላ 3 ሠዉ በከባድ ቁሥለት በህይወት ሢተርፉ ሌሎች ሙሉ ህይወታቸዉ አልፏል!! በሚገርም ሁኔታ አንዲት ተሣፋሪ ወደ ሠቆጣ ለመሄድ ሂሣብ ከፍላ እቃዋን ጭና ጥሏት ሥለሄደ ህይወቷ ሊተርፍ ችሏል። ሌለኛዉ 50ብር ጎሎት ወርዶ በመቅረቱ ህይወቱን በአጋጠሚ ሊተርፍ ችሏል። የሞቱትን ነብስ ይማር። 👉 @Adisstv
Show all...
#ONLF ኦብነግ ከሶማሊያ የሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ። የሶማሊያ ካቢኔ እ.ኤ.አ. በ2017 ( የቀድሞው ካቢኔ ) የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) ን “አሸባሪ ድርጅት” ሲል ያሳለፈው ውሳኔ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ሽሮታል። ኦብነግ ከ5 ዓመት በኃላ ከሽብረተኛ ድርጅትነት ተሰርዟል። ካቢኔው የኦብነግ ኮማንደር አብዲከሪም ሼክ ሙሴን ወደ ኢትዮጵያ ተላልፎ መሰጠትንም “ህገወጥ” ሲል ገልጿል። አብዲከሪም ሼክ ሙሴ እ.ኤ.አ. በ2018 በኢትዮጵያ ከመጣው ለውጥ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ከእስር ነፃ መደረጋቸው ይታወሳል። የዛሬው የሶማሊያ ካቢኔ ውሳኔ በ23 ድምጽ ድጋፍ ፣ በ1 ተቃውሞ እና በ1 ድምፀ ተአቅቦ ነው የፀደቀው። ኦብነግ በትዊተር ገፁ በጠቅላይ ሚኒስትር መሀመድ ሁሴን ሮብሌ እና በካቢኔያቸው ዛሬ የተላለፈውን ውሳኔ በደስታ መቀበሉን ገልፆ ውሳኔውን " ታሪካዊ ነው " ብሎታል። ኢትዮጵያ እንደ እ.ኤ.አ. በ2018 የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)ን ከሽብርተኛ ድርጅቶች ዝርዝር መሰረዟ ይታወሳል። @Adisstv@Adisstv
Show all...
የጁንታው እቅድ😁😁❗ ወያኔ ዛሬ በራያ ዋጃ ኣከባቢ ያሉትን አጋሮቹን ሰብስቦ በመጪው ሳምንት አዲስ ኣበባ እንገባለን እያላቸው ነው😁😁 ጁንታው ጊዜ ተሰጥቶት በደንብ ዝግጅት እያደረገ ነው። 😁 @Adisstv
Show all...
#GeneralDagallo ጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር እንዲሁም ከሌሎች አመራሮች ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል። ጄነራሉ ባጋሩት ፎቶ : ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ጋር መገናኘታቸውን ያሳያል። ሄሜቲ ጉብኝቱን በተመለከተ ፥ " ... ዛሬ አዲስ አበባን በመጎብኘቴ እና የዚህችን ውብ ሀገር መሪዎች በወንድማማችነት መንፈስ በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ። ይህም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ጥልቀት እና ጥንካሬ ያረጋግጣል " ብለዋል። @Adisstv@Adisstv
Show all...
13/5/2014 ዓ.ም ጁንታው ከደቡብ ወሎ ዞን የዘረፈው የእንስሳትና የሰብል ሀብት ትግራይን እስከ ሁለት ዓመት ሊቀልብ እንደሚችል ተገለፀ። ሸብርተኛው በዞኑ በወረራ በቆየባቸው ጊዚያት የአርሦአደሩን የሰብልና የእንስሳት ሀብት የሚችለውን ያህል ዘርፎ ያልቻለውን ደግሞ ለብልሽና ለውድመት ዳርጎ መሄዱን የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብዱ ሁሴን /ዶክተር/ ተናግረዋል። በሰብል ልማት የተዘረፈው ሀብት ከአሁን በፊት የተገለፀው እንዳለ ሆኖ በእንስሳት ሀብት ብቻ ሲታይ በትንሹ 29 ሸህ722 የዳልጋ ከብቶችን ዘርፏል።በተጨማሪም 315 ሽህ በግና ፍየል፣540 ሽህ ዶሮ አና 304 ግመሎችን ዘርፎ አጓጉዟል ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው።ከዚህም ሌላ 267 የእንስሳት ክሊኒኮችን ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ገልፀዋል። @Adisstv @Adisstv
Show all...
የድረሱልኝ ጥሪ ከራያ ‼ የትህነግ ወራሪ ቡድን በራያ አላማጣ ዋጃ ጥሙጋ እና አካባቢው ከበፊቱ የባሰ አስቃቂ በደሎችን እየፈጸሙ መሆኑን ታውቋል። የመረጃ ምንጮቻችን አክለዉም አሁን ላይ መከራችን በዝቷል ከፍተኛ በደል እየደረሰብን ነዉ የሚሰማ ወገን ካለ አሰሙልን ያሉ ሲሆን ሰው ከቤቱ ወጥቶ ጫካ ነው ያለነው! የሚበላ የሚለበስ የለንም በጣም ከፋን ሲሉም በምሬት ተናግረዋል ። ወራሪዉ ቡድን በተለይም በአላማጣ ከተማ የትግራይ ተወላጆችን ከቦታው በማይታወቅ ሁኔታ እያስወጡ መሆኑንና የተወሰኑ የአማራ ተወላጆችን አፍነው መዉስዳቸዉን ጨምረው ተናግረዋል ። ሰራዊቱ እሰይ መጣል ብለን ተደስተን ሳንጨርስ ወደ ኋላ መሸሹ አግባብ አይደለም የሚሉት ምንጮቻችን መንግስት በደላችን እያወቀ ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ ማለፉን ለምን መረጠ ሲሉ ጠይቀዋል ። አሁን ላይ የራያ ህዝብ ከፍተኛ ችግር ዉስጥ የሚበላ የለም ህዝቡ ቤቱን ለቆ ጫካ ነዉ ያለዉ በመሆኑም ይህ ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነዉ ። በተመሳሳይ የትህነግ ወራሪ ቡድን በአድርቃይ በአበርገሌ አንዲሁም በማይጠብሪ በንፁሃን ዜጎች ላይ ግድያ እና እንግልት ዘረፋ እያካሄደ ይገኛል። ጌትነት ያለዉ 👉 @Adisstv Adisstv
Show all...
የክልል መለያ ከተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ላይ እንዲነሳ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ተመራ! የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሐሙስ ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው አራተኛ መደበኛ ስብሰባው፣ የክልል መለያ በተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ላይ እንዲነሳ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ መራ፡፡ምክር ቤቱ የተወያየበት ረቂቅ አዋጅ ከተሽከርካሪ መለያ፣ መመርመርያና መመዝገቢያ አዋጅ ጋር በአባሪነት ተያይዞ ያለውን ሰንጠረዥ ይሽራል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ የሚሻረው ሰንጠረዥ የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶችና ምልክቶችን በዝርዝር የደነገገ ሲሆን፣ እንደ ተሸከርካሪዎቹ አገልግሎት የሚኖራቸውን ቀለምና መለያ አስቀምጧል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሰንጠረዡ እንደ አአ፣ ኦሮ፣ አማ፣ ደሕ እና ሌሎች አሥራ ሁለት የክልልና ከተማ አስተዳደሮችን የሚወክሉ ምህፃረ ቃሎችን ዘርዝሮ፣ ተሽከርካሪዎቹ እንደ ተመዘገቡበት ክልል ወይም የከተማ አስተዳደር ሰሌዳቸው እንዲሠፍር ያዛል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አሁን ያዘጋጀው የመንገድ ትራንስፖርት አዋጅ፣ ይኼንን አሠራር በማስቀረት ወጥነት ያለው ብሔራዊ የተሽከርካሪ ሰሌዳ አሠራር ለመዘርጋት አልሟል፡፡በሚኒስቴሩ የሕግ አማካሪ አቶ አበጀ ማሞ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ለተወካዮች ምክር ቤት የተመራው ረቂቅ አዋጅ ከፀደቀ በኋላ የክልል መለያ የያዙ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ተግባራዊ የሚሆኑት አዲስ ብሔራዊ ሰሌዳ ይፋ እስኪደረግ ብቻ ነው፡፡ እንደ አማካሪው ገለጻ፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የፈረመችው እ.ኤ.አ. የ1968 ‹‹የቬዬና የመንገድ ትራፊክ ኮንቬንሽን››፣ ፈራሚ አገሮች ብሔራዊ ደረጃን የያዘ መለያ በአገሮች ውስጥ ለሚገኙ ተሽከርካሪዎች እንዲሰጡ ያዛል፡፡ ይሁንና የተሽከርካሪ መለያ፣ መመርመርያና መመዝገቢያ አዋጅ ላይ የተቀመጠው አሠራር ክልሎች የየራሳቸውን መለያ የያዘ ሰሌዳ እንዲሰጡ እንጂ፣ ወጥነት ያለው አገር አቀፍ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ተግባራዊ እንዲደረግ አይፈቅድም፡፡ ‹‹ተሽከርካሪ ዓለም አቀፍ ቁስ ነው፣ አንድ መኪና ከዚህ ተነስቶ ኬንያም ሆነ ሱዳን ሲሄድ የአገሮቹ መንግሥት ግራ ሊጋቡ አይገባም፤›› ያሉት አቶ አበጀ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ ተግባራዊ የሚደረገው የሰሌዳ ዓይነት የሚገልጸው ተሽከርካሪነታቸውን ብቻ እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡ https:/adusstv/adisstv Via Reporter @Adisstv@Adisstv
Show all...
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ13ኛ ጊዜ 360 ጠቅላላ ሐኪሞችንና ለ5ኛ ጊዜ 40 ስፔሻልስት ሐኪሞችን ያስመረቀ ሲሆን ከጠቅላላ ሐኪሞች መካከል 246 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 74 ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክሴክዩቲቪ ዳይሬክቴር ዶ/ር አንተነህ ጋዲሳ ዩኒቨርሲቲው የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን በፌደራል መንግስት መወሰኑን ተከትሎ ለድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ከፍተና ትኩረት በመስጠት አሁን በኮሌጁ የሚሰጡ የ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞችን ወደ 15 እንዲሁም የሕክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራሞችን ወደ 8 ማሳደጋቸውን አስረድተዋል፡፡ ዶ/ር አንተነህ አክለውም የሥርዓተ ትምህርት ቀረጻና ግምገማቸው ተጠናቆ በዩኒቨርሲቲው ሴኔት የፀደቀ ሁሌት አዳዲስ የሕክምና ስፔሻሊቲና ሁሌት የማስቴርስ ዲግሪ ፕሮግራሞች ከሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎችን በተጨማሪነት ለመቀበል መዘጋጀታቸወን አብራርተዋል፡፡ ፨ለጥቆማ 👇 @Adisstv 🔔Adisstv
Show all...
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የመጀመሪያ የ6 ወር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካህዷል፡፡ የ6 ወራት የሥራ እቅድ አፈጻጸሙን የመሩት የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ ሲሆኑ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ዘርፍ ፤የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ዘርፍ ፣ የቢዝነስ እና ልማት አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ዘርፍ ፣ የአስተዳደር እና የተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ዘርፍ ፣ የስትራቴጅክ አጋርነት እና የዉጭ ግንኙነት ም/ፕ/ጽ/ቤት ዘርፍ ዉስጥ ያሉ ዳይሬክተሮች፣ኮሌጅ ዲኖች፤ምክትል ዲኖች፤ት/ት ክፍል ኃላፊዎች የተገኙበት ሲሆን በሁሉም ዘርፎች የተጠናከረ ሪፖርት ቀርቦ ዉይይት ተደርጓል፡፡ ፕሬዝዳንቱ አክለዉም ለቀጣይ ስድስት ወራት ዕቅድ ላይ ለሁሉም የሥራ ዘርፎች አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ ፨ለጥቆማ 👇 @Adusstv 🔔ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇 @Adisstv @Adisstv @Adisstv @Adisstv
Show all...