cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ALAMURA HIGH SCHOOL

ALAMURA HIGHSCHOOL ተማሪዎች ለሆናችሁ ትክክለኛ መረጃዎችን, የትምህርት መርጃ መሳርያዎችን ሁሉም ሚቀርብበት ቻናል ነው ! 🤔አስታያየት ካላቹ @TEME_MAN4 Share your friends using the link below @TOKIHO1234 @TOKIHO1234

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
206Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

👑የተጠራንበትን ጥሪ ማወቅ ክፍል-1 ሰዎች በክርስትና ህይወት የተረጋጋና የሰከነ ህይወት ኖሯቸዉ እንዲጓዙ ከሚያስችሉዋቸዉ ነገሮች አንዱ የተጠሩበትን ጥሪ ማወቅ ነዉ፡፡ ወደ ክርስትና የመጡ ሁሉ ተጠርተዋል፡፡ ለምን እንደተጠሩ ማወቅ ደግሞ ለተጠሩበት አጠራር የቀና ጎዳና ይሆንላቸዋል፤ ነገር ግን የተጠራንበትን ጥሪ ሳናዉቅ በራሳችን ፍላጎት ብቻ ሰልፍ እየገባን እኛ ግራ ተጋብተን ሰዉ ግራ የምናጋባ ብዙዎች ነን፡፡ ‹‹ወንድሞች ሆይ መጠራታችሁን ተመልከቱ›› 1ቆሮ 1÷26 እግዚአብሔር ሰዎችን ለተለያዩ አገልግሎቶችና (ተልዕኮዎች) ይጠራል እነርሱም · ለህይወት የሚጠራቸዉ አሉ · ለምህረት የሚጠራቸዉ አሉ · ለአገልግሎት የሚጠራቸዉ አሉ · ለንስሀ የሚጠራቸዉ አሉ 1. ለህይወት የሆነ ጥሪ አዳም እንደተጠራበት ያለ ጥሪ፡፡ አዳም የእግዚአብሔርን ፀጋ ንቆ አምላክነትን ተመኝቶ እፀበለስን በበላ ጊዜ እንደተመከረዉ አይኑ ቢገለጥለትም ያየዉ ግን ብርሃን አልነበረም ጨለማን እንጂ፡፡ የአምላክነት መጎናፀፊያ ሲጎናፀፍ አይደለም የልጅነት ፀጋዉ ሲገፈፍ እንጂ፡፡ እርቃኑን እንደሆነ ተመለከተ፤ አፈረ፡፡ ከበለስ ቅጠልም ቆርጦ አሸረጠ እፍረቱንም ከለለ ነገር ግነ እርቃኑን ያስቀረዉ የበለስ ፍሬ ነዉና ቅጠሉም ሊከልለዉ አልቻለም፡፡ በዚህ ጊዜ ነዉ በገነት ዉስጥ የህይወት ጥሪ ያስተጋባዉ ሁሉን የሚያዉቅ አምላክ አዳም የተደበቀበት ጠፍቶት ሳይሆን በምን ሁናቴ ላይ በየትኛዉ ቅድስናና የሃጢአት ደረጃ ላይ እንዳለ ይጠይቀዉ ዘንድ ስለወደደ አዳም አዳም ወዴት ነህ? አለዉ፡፡ አዳምም እዚህ ተደብቄያለሁ አለዉ፡፡ እግዚአብሔርም አዳም ያለበትን አዉቋልና ለአዳም አዘነለት፤ ወደደዉ ተድላና ደስታ ካለበት ከገነት አባረረው፡፡ ይህም እግዚአብሔር አዳምን ምን ያክል እንደሚያፈቅረዉ ያሳያል፡፡ ዘፍ 3÷10 ብዙዎች እግዚአብሔር አዳምን ተድላና ደስታ ካለባት ገነት ስላባረረዉ እንዴት ያፈቅረዋል ልንል እንችላለን ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ ነገር ግን በማስተዋል ብንመረምር አዳም አመፀኛ ከመሆን ጋር ህግ አፍራሽ ከመሆኑ ጋር አምላክ ለመሆን ካለዉ ምኞት ጋር ለዘላለም መኖር ቢችል ኖሮ ኑሮዉ ሁሉ ክፋትን ተሞልቶ ከሚኖር ከአጋንንት ጋር ይመሳሰል ነበር፡፡ ብዙ ሰዎች አዳም ከገነት የተባረረዉ እፀበለስ ስለበላ ብቻ ነዉ ብለዉ ያምናሉ፡፡ ይሁንና መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን አዳም እፀበለስን ስለበላ ብቻ አይደለም ከገነት የተባረረዉ እፀበለስን መብላቱ መነሻ ቢሆንም መፅሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ብሎ የሚነግረን ግን እግዚአብሔር አምላክም አለ #እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ አሁንም እጁን እንዳይዘረጋ ደግሞም ከህይወት ዛፍ ወስዶ እንዳይበላ ለዘላለምም ሕያዉ ሆኖ እንዳይኖር ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክ ከዔደን ገነት አስወጣዉ ዘፍ፣3፡ 22 ስለዚህ እግዚአብሔር አዳምን ከገነት ያስወጣበት ምክንያትና መነሻዉ እፀበለስን መብላት ይሁን እንጂ ስለዚህ ብሎ እንደነገረን የህይወትን ዛፍ በልቶ ከነክፋቱ ለዘላለም መኖር እንዳይችል ነዉ፡፡ ይልቁንም አለመታዘዙን በመታዘዝ፣ ክፋቱን በበጎነት ለውጦ አምላክ የመሆን ምኞቱን አሟልቶ በቀራንዮ ተሰቅሎ ለዘላለም የሚኖርበትን የህይወት እንጀራ እስኪሰጠዉ ድረስ ከገነት ገለል አደረገዉ፡፡ ለዚህም ነዉ ሐዋርያዉ ዮሐንስ #የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ አለም ልኮታልና ያለው 1ዮሐ 4÷1 የሚገለጥ ያለና የነበረ ነገር ግን የተከደነ ነገር ነዉ፡፡ በዚህ ለሕይወት በሆነ ጥሪ እኛስ ወዴት ነን? .......ይቀጥላል....... ━━━━━━✦✗✦━━━━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ ─── ❖ ── ✦ ── ❖ ─── SHARE 💯SHARE 💯SHARE💯 JOIN US @zelalemawhiwot @zelalemawhiwot @zelalemawhiwot @zelalemawhiwot
Show all...
#እንደ_ሻማ🕯️#እንሁንለት በዚህ ዘመን ብዙ አገልጋዮች እግዚአብሔር ማገልገል የሚፈልጉት በምቾት እና በተድላ እንዲሁም የእራሳቸውን ክብር በመጠብቅ ነው፤ይህ ደግሞ ልክ አይደለም። ፤በመጽሐፍ ቅዱሳችን ላይ ስማቸው በጉልህ ከሚጠቀሱ ሰዎች መከካል አንዱ ዮሐንስ ነው፤ ይህ ሰው የክርስቶስን መንገድ የጠረገ፥ከራሱ ይልቅ ለአምላኩ ለእግዚአብሔር የታመነ እውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ ነው፤ ለራሱ እንኳን ጊዜ የሌለው፤የሚበላው ምግብ እንኳ የበረሀ ማር እና እንበጣ እንደነበር መጽሐፍ ይናገራል.. “ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።” — ማቴዎስ 3፥4 እግዚአብሔር አምላክ በምድር የሰጣቸውን ተልኮ በድል አጠናቀው ወደ አባታቸው እቅፍ የገቡ እውነተኛ ደቀመዝሙሮች ነበሩ፤ከነዚህም በጥቂቱ 🔥ሐዋሪያው ጳውሎስ 🔥መጥምቁ ዮሐንስ 🔥ሐዋሪያው ጴጥሮስ እና ሌሎችን መጥቀስ ይቻላል፤ በጣም የሚገርመው እነኚ ታማኝ የእግዚአብሔር አገልጋዮች አሟሟታቸው እንኳ መልካም አልነበርም፥ግማሾቹ ተሰቅለው፤ ከፊሎቹ ደግሞ ተቃጥለው ነው የሞቱት። የውላቹ ውድ የአባቴ ብሩካን እግዚአብሔር እናገልግልህ ብለን ከተነሳን በአለም ላይ ለሚመጡብን ችግሮች ሁሉ መጋፈጥ ይኖርብናል፤ እግዚአብሔር በማገልገል ህይወት ውስጥ እስከ ሞት ድረስ ዋጋ ልንከፍል እንችላለን፤ መጽሐፍ ሲናገር... ማቴዎስ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ¹¹ ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ¹² ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። ብናገኝም ......ለጌታ ብናጣም ........ለጌታ ብንጠላም ........ለጌታ ቢመቱንም ..........ለጌታ ብንወገርም ..........ለጌታ ባይመቸንም ...........ለጌታ ቢገፉንም.................ለጌታ እግዚአብሔር ከማንም በላይ ስለ ልጆቹ ግድ ይለዋል፤በእርሱ የሚታመኑትን ያውቃልና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ይጠብቃቸዋል። “እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።” — ናሆም 1፥7 #ጌታ_ዘመናቹን_ይባርክ #ለወዳጃቹ_አጋሩ @zelalemawhiwot @zelalemawhiwot @zelalemawhiwot
Show all...
Show all...
ዘላለማዊ ህይወት

❝አመንዝሮች ሆይ፤ ከዓለም ጋር ወዳጅ መሆን የእግዚአብሔር ጠላት መሆን እንደሆነ አታውቁምን? ስለዚህ የዓለም ወዳጅ መሆን የሚፈልግ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።❞ —ያዕቆብ 4: 4 (አዲሱ መ.ት)

የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳቹ ቴክኒክና ሙያ መማር ለምትፈልጉ የመግቢያ ነጥብ በምስሉ ላይ ተያይዟል:: ከሰኞ ግንቦት 09,2013 ጀምሮ በሬጅስትራር ጽ/ቤት አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ ይዞ በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። @tokiho1234 @tokiho1234
Show all...
በኦሮሚያ ክልል ከ600 በላይ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የ20 ሺህ ብር ሽልማት ተሰጠ። በኦሮሚያ ክልል በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 በላይ ውጤት ላስመዘገቡ 152 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው የ20 ሺህ ብር ሽልማት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ፡፡ በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዕውቅና እና ሽልማት ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በዕውቅና እና ሽልማት መርሐ-ግበሩ ላይ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሚያ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 በላይ ውጤት ካስመዘገቡት 152 ተማሪዎች መካከል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለወጡት ተማሪዎች ዘመናዊ S6 ታብሌትና ሜዳሊያ ተሸልመዋል፡፡ (EPA) Via - tikvah-magazine መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ! https://t.me/temhert_bebete https://t.me/temhert_bebete
Show all...
✍️የፋሲካ በዓል ( የኢየሱስ ሞት) ደሙን ባየሁ ጊዜ ከእናንተ አልፋለሁ ዘፀ 12፡13 ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዷል 1 ቆሮ 5፡7 ——————————————————— ፋሲካ ማለት የቃሉ ትርጉም ማለፍ ሲሆን Hebrew: פֶּסַח Transliteration: peçach Pronunciation: peh'-sakh In English ፡ passover ማለፍ , አንድ ፍርድ በአንድ ነገር ምክንያት ሲያልፍህ ማለት ነው። በብሉይ (በአሮጌው) ኪዳን እግዚአብሔር በግብፅ ሀገር በባርነት ቀንበር ለሚኖሩ እስራኤላውያን ከፈርዖን የጭቆና አገዛዝ ነፃ የሚወጡበትን እና ከእግዚአብሔር የሞት ፍርድ ማምለጥ የሚችሉበትን መንገድ አዘጋጅቶ ሲያድናቸው የምንመለከትበት ነው። እኛም ፋሲካችን በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ የቤዛነት ስራ ከእግዚአብሔር ፍርድ እና ከጨለማ ሀይላት አገዛዝ ነጻ መውጣታችንን የሚያሳይ ነው።
Show all...
====================== Via:ዘካምፓስ Join✨share⚡️ 👉👉@tokoho1234 @tokoho1234 @tokoho1234
Show all...
📚 ስለ ኦዳ ቡልቱም ሙሉ መረጃ ፦ 📚 ከተማሪ ህብረት ፕሬዝዳንት ጋር በስልክ የተነጋገር ነው ፦ ====================== Join✨share⚡️ @tokoho1234 @tokoho1234 @tokoho1234
Show all...
📚 ሙሉ መረጃ ስለ ደብረ ታቦር ዮኒቨርስቲ ፦ ====================== Join✨share⚡️ 👉👉 @tokoho1234 @tokoho1234
Show all...
📚 ሙሉ መረጃ ከመቅደላ አምባ ሶሻል ተማሪ ፦ ====================== Via:ዘካምፓስ Join✨share⚡️ 👉👉@tokiho1234 @tokiho1234 👈👈
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!