cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

እውነተኛ ክርስቲያን️

"እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ ስለበደላችንም ደቀቀ የድኅነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን።" for any question https://t.me/amani7775 anagrugn

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
401Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሰላም ሰላም እንዴት ናቹ የቻናሌ ቤተሰቦች እኔ እግዚአብሔር ይመስገን ደና ነኝ ዛሬ አንድ ሐሳብ ላካፍላችሁ ብቅ ብያለው ያው ሰው ነንና በህይወታችን መጥተው የሚሄዱ በጣም ብዙ ጉዳዮች አሉ የሚገርማቹ ነገር ደግሞ እያንዳንዱ ጉዳዮች መጥተው ሲሄዱ እግዚአብሔር ያያቸዋል "አይኖቼ በስፍራው ሁሉ ናቸው"ይላልና ስለዚህ የሚያስፈራ ነገር እንኳ መጨረሻው ክፉ አይሆንም bc "በክፉ አይፈትንም" ይላልና አትፍሩ በህይወታችሁ መጥተው የሚሄዱ ሁሉ ይምጡ ደግሞም ይሂዱ የህይወታቹ ባለቤት እናንተ ስላልሆናችሁ ሰሪው(ባለቤቱ) እንደፈለገ ያርጋቹ ስጡት እራሳችሁን...። ተባርካቹሀል😇😇😇🙏 @truthchristiyanity @truthchristiyanity
Show all...
ፍቅር ፍቅር እደዚ ነው እኔ አይቸዋለሁ፡ ብዙ ንብረት ነበር ባባቴ ቤት ሳለሁ፡ ጥጋቤ በዛና ከዛ ከሞቀው ቤት፡ አባቴን በትእቢት እዲህ ተናገርኩት፡ በላ ድርሻየን ስጠኝ ራሴን ልቻልበት፡ እሂን መጠየቄ የለብኝም ስተት፡ አሁን ስጠኝና ቶሎ ልሂድበት፡ አባቴ በኔ ላይ እጂጉኑ ቢያዝንም፡ ኧረ የድርሻየን አልከለከለኝም፡ ወጣሁ ካባቴ ቤት ከሞቀው ጓዳየ፡ በገንዘብ በሀብት በራሴ ታብየ፡ ያላዩትን ሀገር ናፋቂ ሆኩና፡ የምታምር መስሎኝ አለም ስትለኝ ና፡ ገዘቤን በተንኩት ውርሴ መና ቀረ፡ ሰውም በኔ ስራ እጂጉን አፈረ ፡ ድህነት ወረሰኝ እጂግ ተጓሳቆልኩ፡ እኔም ከራሴ ጋ እዲሁ ተማከርኩ፡ እዴው ባባቴ ቤት ተመልሸ ብሄድ፡ እደልጂነቴ ባይኖርም መወደድ፡ ልጂነቱ ቀርቶ እደ ባርያው ልሁን፡ ኧረ ይሻለኛል ናፈኩኝ ያቺን ቀን፡ አባቴ ሲያየኝ ገና ከሩቁ፡ የቆሸሸውን ልብስ ቶሎ አውልቁ፡ የደለበውን ለልጀ ረዱ፡ የጠፋው ልጀ ተመለ ሰልኝ፡ እያለጮኸ በይኖቹ እያየኝ፡ ታዲያ ፍቅር ከዚ በላይ አለ፡ በደልን ሳይቆጥር ባለም ላይ ያየለ፡ በደሌን ሳይቆጥር እዲህ የወደደኝ፡ የሰማዪ አባቴ ስሙ ይክበርልኝ፡፡ ❤️ፍቅር በደልን አይቆጥርም!
Show all...
ሰው ሰራሽ ደመና! - አንዳንድ የዘመናችን “ቤተ ክርስቲያናት” በአምልኮ ሰዓት (በልዩ ልዩ ክዋኔዎች) ለታዳሚው “አስደሳች ድባብ” ለመፍጠር የሚኼዱበት ርቀት አስደንጋጭ እየሆነ መጥቷል፡፡ የመድረክ አገልግሎቶች የገበያ ፍልስፍና (marketing philosophy) የሚከተሉ ይመስላሉ፡፡ የደንበኞችን ፍላጎት በማጥናት ተፈላጊውን ምርት እንደሚያቀርብ አምራች፣ ጆሮን የሚያሳክክ ትምህርትና ስሜትን የሚኮረኩር ሸቀጥ ሁሉ መድረኩ ላይ መሰጣት ከጀመረ ቆየ፡፡ ስብከቱ በአዎንታዊ ሐሳቦች የተሞላ፣ ለአድማጩ ጊዜያዊ ስሜት የሚጨነቅ፣ ቀላልና ዘና የሚያደርግ ሲሆን፤ የሚያስተምር፣ የሚወቅስ፣ የሚገስጽና የሚያቀና ጠንካራ ትምህርት ከብዙ ምስባኮች ተሰድዷል፡፡ ስለ ኀጢአት፣ ስለ ፍርድ፣ ስለ ሕይወት ንጽሕና፣ ስለ ንስሐ፣ ስለ ወንድማማች መዋደድ፣ ስለ ጌታ ምጽአት አይነሳም፡፡ ትምህርቶች፣ ለአድማጭ እንዳይጎረብጡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይዘታቸው ሳስቶ ሥነ ልቡናዊና አነቃቂ ይደረጋሉ፡፡ አምልኮ እየተባለ የሚከወነውም ድርጊት እንዲሁ ነው፡፡ መዝሙሮች ከመልዕክት አዘልነት ይልቅ ምዕመናንን ለማውረግረግ የሚጨነቁ፣ በተራ ቀረርቶና በባዶ ተስፋ ታዳሚን ማስፈንጠዝን ግባቸው ያደረጉ ሆነዋል፡፡ የጥሩ ‹‹አስመላኪ›› መለኪያው ‘ሕዝቡን ምን ያህል አንቀሳቀሰ? ድምጹና ደንሶ የማስደነስ ችሎታው ምን ይመስላል?’ የሚል የሆነ ይመስላል፡፡ መልዕክት አልባውን ጩኸት የሚያጅበው ሙዚቃ፣ የሚብረቀረቁ የመድረክ መብራቶችና ከጀርባ የሚለቀቀው ባዕድ ጭስ፣ ተመልካችን በስሜት የሚያጦዝ ድባብ ይፈጥራሉ፡፡ ከሁሉ የከፋው ነገር፣ ይህ ሰው ሰራሽ ድባብ “የእግዚአብሔር ሕልውና” እየተባለ መጠራቱ ነው፡፡ (ከጥቂት ዓመታት በፊት ወደ ሐገረ አሜሪካ ተጉዞ የተመለሰ አገልጋይ፣ በዚያ ስላያቸው አንዳንድ ቤተ ክርስቲያናት ሲናገር፣ “የመንፈስ ቅዱስ ደመና ጠፍቶባቸው፣ አርቴፊሻል ደመና ፈጥረው ከመድረክ ያቦንናሉ” ብሎ የተናገረው ትዝ ይለኛል፡፡) በኮምፒዩተር ቴክኖሉጂ “user friendly” የሚባል የተለመደ ቃል አለ፡፡ ለተጠቃሚ የሚቀርቡ ሶፍተዌሮችና ፕሮግራሞች ለተጠቃሚው የማይከብዱና ያልተወሳሰቡ እንዲሆኑ አደርጎ ማቅረብ ማለት ነው፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎትም እንዲሁ user friendly እየሆነ መጥቷል፡፡ አይደን ቆዘር የተባሉ መጋቢ (ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት) በአሜሪካ ቤተ ክርስቲያናት ላይ የተመለከቱትን ለውጥ አስመልክቶ፣ “ተዝናኖት (ወይም Entertainment) የወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያናትን እያጠቃ ያለ እጅግ የከፋ ኑፋቄ ነው! ተዝናኖት ራሱ እውነተኛውን አምልኮ የተካ ‘ሌላ አምልኮ’ ሆኗል” ብለው ነበር፡፡ የዘመናችንን ቤተ ክርስቲያን በትኩረት የታዘቡት ፌሚ አደለይ የተባሉ ጸሐፊም እንዲሁ፣ “ፈንጠዚያ ከመውደዳችን የተነሳ የእኛ ዘመን ቤተክርስቲያን ከ”ታላቁ ተልዕኮ ወደ ታላቁ ተዝናኖት” (from Great Commission to Great Entertainment) እየተሸጋገረች ይመስለኛል” ብለዋል፡፡ የገበያ ሕጉ፣ ሰዎች ምን ያስፈልጋቸዋል ከሚለው ይልቅ ሰዎች ምን ይፈልጋሉ የሚለው ላይ አተኩሩዋል፡፡ የታዳሚ ስሜት ላይ የቆመ “ተጠቃሚ ተኮር (consumer-oriented)” አገልግሎትም ተፈጥሯል፡፡ እግዚአብሔር ራሱም፣ “ዓላማችን የደንበኞች እርካታ ነው” የሚል ጥቅስ ለጥፎ፣ ‹‹ተደሰቱልኝ፣ ተዝናኑልኝ›› እያለ እንደሚያስተናግድ አስተናጋጅ የፍላጎታችን አገልጋይ ተደርጎ ተስሏል፡፡ በዚህም ሳቢያ፣ ብዙ ምስባኮች የወደቀውን ሰው የልዕልና መሻት እና ‹ኤጎ› እያከኩ አዳምን በሚቀልቡ ተናጋሪዎች ተሞልተዋል፡፡ ኮምጨጭ ያለው የቃል እውነት የሚነገርባቸው አዳራሾች ባዶ እየሆኑ፣ ጊዜው በጠየቀው የገበያ ስልት የሚመሩት ደግሞ ጠጠር መጣያ እያጡ ነው፡፡ አንዳንዶች ይህን አስነዋሪ ድርጊታቸውን፣ “ወጣቱንና አማኝ ያልሆነውን ማኅበረሰብ በአውዱ ለማግኘት የሚደረግ ነው” በማለት ለማመናፈስ ይጥራሉ፤ “በሁሉ እነርሱን መሰልኩ” የሚለውን የጳውሎስን ቃል ዋቢ አድርገውም ይጠቅሳሉ፡፡ ይህ ጳውሎስንም ሆነ ቃሉን ጠንቅቆ አለማወቅ ነው፡፡ ጳውሎስ ሰውን ለማስደሰት መልዕክቱን የሚያቀጥን የመድረክ አጫዋች አልነበረም፡፡ ዓለምን ለማዳን እንደ ዓለም መሆንን አልሰበከም፡፡ የዘመናችን ቤተ ክርስቲያን፣ ዓለም የራሷ የሆኑትን ለመሳብ የምትጠቀማቸውን ዘዴዎች ኮርጃ መጠቀሟ የክፍለ የዘመናችን ታላቅ መንፈሳዊ ቅሌት ይመስለኛል፡፡ ትውልዱ የሚያስፈልገው ይህ አልነበረም፤ ስጋዊ አፒታይቱን የሚያረካ ኀይማኖታዊ ተዝናኖት ወደ ክርስቶስ አያቀርበውም! በዳንኪራ የዳነ፣ የኮሜዲ ምሽት በመሰሉ ስብከቶች የተለወጠና በአነቃቂ ዲስኩሮች ያደገ ክርስቲያን አላየንም፡፡ የሚያስፈልገን ወደ እግዚአብሔርና ወደ ቃሉ የሚመልሰን ጥልቅ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርትና ክርስቶስንና ወንጌሉን የሚያልቅ አምልኮና አገልግሎት ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አጥሯ ፈርሶ የዓለም ኮተት ሁሉ ማራገፊያ እንዳትሆን መከላከል ይገባናል፡፡ ከተያያዝነው አደገኛ ቁልቁለት የሚመልሱንን እውነተኛ እረኞች እግዚአብሔር ይስጠን፡፡ መልካም ቀን! የኤል ቃሉ ጆሲ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Show all...
“በመልካም ቀን ደስ ይበልህ፤ በክፉም ቀን ተመልከት፤ ሰው ከእርሱ በኋላ መርምሮ ምንም እንዳያገኝ እግዚአብሔር ይህንም ያንም እንደዚያ ሠርቶአል።” — መክብብ 7፥14 @truthchristiyanity
Show all...
ክርስትናችንን እነድንወደው የሚያደርገን ኑሮአችን ሳይሆን ፊቱ ነው የሱን ፊት ስናይ በረከት እናገኛለን የሱን ፊት ስናይ ማንነቱን እንረዳለን የሱን ፊት ስናይ በደስታ እንሞላለን ሐዘናችንን እንረሳለን የሱን ፊት ስናይ ጥበቡና ሞገሱ ይገለጥልናል ... ፊቱን ስናይ ይሄ ሁሉ ስለሚታየን ክርስትናችንን እንወደዋለን። እንጂ ከሚገጥመን ከምናየው ከሚደርስብን... ነገር አኳያ ክርስትናችንን ካየነውማ🙉 ክርስትናን እንጠላው ነበር ነፃነት የለውም ብለን እንሸሸው ነበር ክርስትና እያወቅን የምንታሰርበት ሰንሰለት ነው ግን ያንን የምንረሳው ፊቱን ስናይ ብቻ ነው
Show all...
ክርስትና እያወቅን የምንታሰርበት ፈቅደን የምንገባበት እስር ቤት ነው። ክርስትና ከድሎት ርቀን ከምቾት ርቀን ለክርስቶስ ደስታ የምንኖርበት ህይወት ነው። ክርስትና በንግግር ክህሎት በእውቀት ብዛት በማገናዘብ ልክ የምንኖርበት ህይወት ሳይሆን በሞኝነት የምንመራበት የእምነት ቤት ነው። ♦️@truthchristiyanity♦️ ♦️@truthchristiyanity♦️ 🔺🔺🔺JOIN US🔺🔺🔺
Show all...
😮👆Amezing short video how he saved us!...and his plan😢
Show all...
Show all...
የፀጋ ወንጌል

📌በዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶች ይለቀቃሉ 📌ጥያቄዎች ከመፅሐፍ ቅዱስ አንፃር ይመለሳሉ 📌የእናንተ ድርሻ Share በማድረግ ሰው የእውነትን ወንጌል እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ ነው Group

https://t.me/Graceofjesushighpriestgroup

ሀሳብ እና አስተያየት +251985406785(@yabsen) +251953843618(@josi1423) ✍የጌታን ፀጋ ይብዛላቹህ

👉 መንፈስ ቅዱስ ምን ያህል ይገለጥልናል የሚለው የሚወሰነው ምን ያህል እንፀልያለን በሚለው ሳይሆን ምን ያህል በንፁህ እንፈልገዋለን በሚለው ነው።የእርሱ መገለጥ የሚገኘው በብዙ ጩህት ሳይሆን በንፁህ ልብ ነው። @truthchristiyanity
Show all...
ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³¹ እንግዲህ ስለዚህ ነገር ምን እንላለን? እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን ይቃወመናል? ³² ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠው ያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዴት አይሰጠንም? ³³ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው? ³⁴ የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። @truthchristiyanity @truthchristiyanity
Show all...