Christ message
#አላማው ፦ # መንፈሳዊ ፅሁፎችን # ትምህርታዊ ፅሁፎችን # ጤና ነክ ትምህርቶች # የክርስትና እይታ እየሱስ ብቻ መሆኑን *አብረውን ማገልገል ከፈለጉ በዚህ @Sarfii
Show more205Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
መክብብ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የሞቱ ዝንቦች የተቀመመውን የዘይት ሽቱ ያገሙታል፤ እንዲሁም ትንሽ ስንፍና ጥበብንና ክብርን ያጠፋል።
² የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።
³ ደግሞም ሰነፍ በመንገድ ሲመላለስ እርሱ ልብ ይጐድለዋል፥ የሚያስበውም ሁሉ ስንፍና ነው።
@Christofmessage
👉 ከሦስት አመት በፊት ከወጣው ጊዜው መፅሄት ተቀንጭቦ የተወሰደ ስለ አዲስ አመት ደስ የምትል አጭር ፅሁፍ በጥበበሥላሴ መንግስቱ የተዘጋጀ
@Sda_songs
“በሽተኞችን ፈውሱ፤
ሙታንን አስነሡ፤
ለምጻሞችን አንጹ፤
አጋንንትን አስወጡ፤
#በነጻ_የተቀበላችሁትንም_በነጻ_ስጡ።”
( ማቴዎስ 10፥8 )
@Christ message
✍✍ኤልያስ ባትሮ
" በዚህ ህይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:19)
************
ወንጌል በተገኘ አጋጣሚ ሁሉ መሰበክ አለበት።በግሌ የማምነው ዛሬ በዙሪያችን ያሉ ማናቸውም ዓይነት ጩኸቶችና ውጥረቶች፣ሉል አቀፋዊም ሆነ አገራዊ ሁኔታዎች አንዳች ነገር ጠቋሚ ናቸው።እሱም ወደ እግ/ር መመለስ እንዳለብን።ወደ እግ/ር ለመመለስ ወደ ቃሉ እውነት መመለስ ነው።
#ኢየሱስ በምድራዊ አገልግሎቱ ማናቸውንም አጋጣሚዎች በመጠቀም የእግ/ርን መንግስት ሚስጢር ያሰተምር ነበር።በተረራራ፣በትልልቅ ጉባኤዎች፣በቤተመቅደስ፣በግብዣ ቤት(በሰርግ)፣በህዝባዊ በዓላት ፣በሀዘን ቤት፣በባህር ላይ በጀልባ ላይ ሁላ ተቀምጦ ያስተምር ነበር።በጥቂቶቹ ሳያዝንና ተስፋ ሳይቆርጥ፣በብዙሃኑ ደግሞ ሳይደመም ለሁሉም በሚገባቸው መንገድ
ያስተምር ነበር።
#ዛሬ በቀን 05/11/20014 ዓ.ም.በሲዳማ ክልል ብላቴ ዙሪያ ወረዳ በኪታዎ ዳንቤ ቀበሌ ውስጥ በመንፈሳዊ እና በማህበራዊ ህይወታቸው ለአካባቢው ማህበረሰብ አርአያና አለኝታም የሆኑ አንዲት አንጋፋ እናት አርፈው፣ወንድማችንና የስራ ባልደረባችንም የሆነው ልጃቸው ደምሴ(ዘለቄ)ላታሞን ምክንያት በማድረግ ብቻ ሳይሆን፣የክታዎ ዳንቤ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤ/ክ ባደረገችልኝ ጥሪ ጭምር በመገኘት በዚያ ለተሰበሰቡት የጌታ ጸጋ በበዛልኝ መጠን የእግ/ርን ቃል አካፍያለሁ።"" እናንተ። ገና አራት ወር ቀርቶአል መከርም ይመጣል ትሉ የለምን? እነሆ እላችኋለሁ፥ ዓይናችሁን አንሡ አዝመራውም አሁን እንደ ነጣ እርሻውን ተመልከቱ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 4:35)"ተብሎ እንደተጻፈ ብቻ እኛ ተነስተን ከሰራን አሁን ትውልዱ አንጡራውን ወንጌል እንደተጠማ በአገልግሎቱ መባረካቸውን የገለጹልኝ የስራ ባልደረቦቼ በአካልና በinbox በሰጡኝ ማበረታቻና ማደፋፈሪያ መገንዘብ ችያለሁ።በተለይም የኦሮቶዶክስ ሀይማኖት ተከታይ የሆኑ አንድ አባት ቀርበው የሰጡኝ እጅግ ገንቢ አሰተያየትና ኢየሱስን"እንዲህ ያለ እምነት ከእስራኤል ዘንድም አልተገኘም"ያስባለ ምስክርነት ውስጤን ነክቶ ያመላከተኝ ነገር አለ።
የነገርከበችሁ አገልግሎቴን ሳይሆን ዕድሎቻችንን አለመጠቀማችንንና
ሽፋኑን ብቻ በማየት ወንጌል ተዳርሷል ብለን ስንኩራራ ገና የብዙዎች ጆሮ አንጡውን ወንጌል አለመስማቱን ነው።
#አጋጣሚው መልካም እንዲሆን ሎጅስቲክ በማመቻቸት ምቹ ሁኔታ ለፈጠሩልኝ ባልደደረቦቼና ወዳጆቼን፣የኃይሉ ታላቅነት እኖዲገለጥ በሸክላ ዕቃ ውስጥ ለተቀመጠው መዝገብ ዕውቅና ሰጥታ በር ለከፈተችው ቤተክርስትያንና ምርጫቸው ላደረጉኝ ቤተሰብ አድናቆቴና ምስጋናዬ ላቅ ያለ ሲሆን፤ላዘኑ ወገኖች ሁሉ መጽናናት እንዲሆንላቸው ጸሎቴ ነው።
#ሁሌም እንደምለው"እውነተኛው የክብሬ ክልል ወንጌል ነው"
" ቃሉን ስበክ፥ በጊዜውም አለጊዜውም ጽና፥ ፈጽመህ እየታገሥህና እያስተማርህ፥ ዝለፍና ገሥጽ ምከርም።"
(2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:2)-ሻሎም!!!!!
✍✍ኤልያስ ባትሮ
Show all...
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
በመመለስ መጠገን
የችግሮቻችን መንስኤዎች የተለያዩ ቢሆኑም፣ መፍትሔያቸው ግን አንድ ነው። እርሱም ሁሉን ወደሚችለው አምላክ መመለስ ነው።
እርሱ መጠገን የማይችለው ስብራት የለም።
እርሱ መቀጠል የማይችለው የተበጠሰ ነገር የለም።
እርሱ የማይፈታው እንቆቅልሽ የለም።
እርሱ የማይለጠው ህይወት የለም።
ወደ እርሱ ስንመለስ እጁን ዘርግቶ የሚቀበለን፣ ወደ እርሱ የመጣውን ወደ ሜዳ አውጥቶ የማያባርር መልካም አምላክ ነው። ምናልባት ወደ እርሱ መጥተን እንዳንጠገን እንቅፋት የሆነብን የሸሸግነው ክፋት ቢኖር፣ ዛሬ ጨክነን እንወስን። ይህ መልካም ጌታ እንዲህ ብሎ ሲጠራንም እንስማው።
“እንዲህ በላቸው፤ ‘በሕያውነቴ እምላለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዳቸው ተመልሰው በሕይወት እንዲኖሩ እንጂ በክፉዎች ሞት ደስ አልሰኝም። ተመለሱ ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ለምን ትሞታላችሁ?’
” ህዝ 33:11
አባት ሆይ፣ “ወደ አንተ መልሰን፤ እኛም እንመለሳለን” ስብራታችንን ጠግንልን፤ አዲስ ህይወት ስጠን። አሜን።