cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

⁉️ ሴት እና ወጓ 🗞🗞🗞

🛎 ህይወትን እንደ ሙከራ አስቦ መኖሩን አቁም! ዛሬ የመጨረሻ ቀንህ እንደሆነ አስበህ ጥግ ድረስ ተጠቀምበት፤ ትላንት ላይመለስ አልፏል ነገም አስተማማኝ አይደለም።

Show more
Advertising posts
224Subscribers
No data24 hours
-17 days
+630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

..      ቫይረሱ  እንዴት ነው የሚሰራጨው? ሁለት ጤነኞች እኔ እና አንተ ተቀምጠን ቡና እየጠጣን ነው፤ በድንገት አንድ ደደብ መጥቶ ስድባዊ እውቀቱን ተጠቅሞ ሰደበህ፤ አንተም ደም ፍላትህን ለማብረድ መልሰ ሰደብከው!። አሁን ሁለት ደደቦች ካጠገቤ አሉ.. አንደኛው ቆሟል ሁለተኛው አብሮኝ ቁጭ ብሎ ቡና እየጠጣ ነው.. 🥱
Show all...
👍
👏
👎
ለምሳሌ አንተ 500 ብር አለ..ፍቅረኛ ደግሞ 300 ብር አላት። ይ ሄ ም ን ማ ለ ት ነ ው? ፍቅረኛ 800 ብር አላት ማለት ነው😀 @kidusanfelix
Show all...
ህይወት እኮ መለወጥ እንደምትችል በየጊዜው አንድ የተለየ ነገር እያደረክ ማረጋገጥ ነው። ማፍቀር እንደምትችል አረጋግጠሃል፤ መርሳት እንደምትችል አረጋግጥ..❞ ፦አዳም ረታ - መ ረ ቅ 📖 @kidusanfelix
Show all...
And I do feel quite alone again. From nowhere to nowhere. `` እና እንደገና ብቸኝነት ይሰማኛል፤  ከየትም ወደ የትም.. ``   ፦Virginia Woolf / fictional essay 📖 @kidusanfelix
Show all...
`` በመጨረሻ የምናስታውሰው የጠላቶቻችን ንግግር ሳይሆን የወዳጆቻችንን ዝምታ ነው። ``                 ፦ማርቲን ሉተር ኪንግ
Show all...
`` በመጨረሻ የምናስታውሰው የጠላቶቻችን ንግግር ሳይሆን የወዳጆቻችንን ዝምታ ነው። ``                 ፦ማርቲን ሉተር ኪንግ @poems_essay
Show all...
የተራበ ሆድ ፥ ባዶ ኪስ እና የተሰበረ ልብ በህይወት ውስጥ ምርጥ ትምህርቶች ያስተምራሉ። 🤝
Show all...
አንዲት ማራኪ የዜን ታሪክ አለች… ጎን ለጎን ያሉ ሁለት ቤተ መቅደሶች ነበሩ፡፡ የሁለቱ ቤተ መቅደሶች ካህናት ተጣልተዋል፡፡ አይነጋገሩም፡፡ ለነገሩ እነዚህን ካህናት ለማለት እንኳ ይከብዳል፡፡ የይስሙላ ካህናት ናቸው፡፡ ስለዚህም ተጣልተው እርስ በርስ አይነጋገሩም፡፡ ሁለቱም ቤተ መቅደሶች ደግሞ ሁለት የሚላላኩላቸው ትንንሽ ልጆች ነበሯቸው - ከገበያ አትክልቱን፣ ፍራፍሬውን ሌላ ሌላውን እንዲገዙ የሚልኳቸው እነዚህን ልጆች ነበር… እናም ካህናቱ ተጣልተው የለ … እርስ በርስ አይነጋገሩም አይደል - ልጆቹንም እንዳትነጋገሩ ብለዋቸዋል፡፡ ልጆች ደግሞ ያው ልጆች ናቸው - ማውራት ይፈልጋሉ - ደግሞ የተከለከለ ነገር እንዴት እንደሚጥም… ስለዚህም አንድ ቀን አንደኛው ልጅ ሌላኛውን ልጅ እንዲህ ሲል ጠየቀው፣ “ወዴት ነው የምትሄደው ?” “ንፋሱ ወደ ወሰደኝ ቦታ” አለ ሁለተኛው ልጅ፡፡ እንግዲህ ይሄ ሁለተኛው ልጅ ቤተመቅደሱ ውስጥ መንፈሳዊ ክርክር ሲደረግ የሰማትን መመለሱ ነው…፡፡ ሥነ መለኮት ሲሰማ ስለሚውል በልጅነቱ ፈላስፋ ሆኗል… የመጀመሪያው ልጅ የሚመልሰው ጠፋው፡፡ ምን ይበል ? ዝም አለ፡፡ ያልጠበቀው መልስ ነበራ፡፡ ተናደደ… እናም ደግሞ ተፀፀተ - ‘መምህሬ ተው ሲለኝ ! እውነትም እነዚህ የሌላኛው ቤተ መቅደስ ሰዎች አደገኞች ናቸው፡፡ መጥፎዎች ናቸው፡፡ እኔ ‘ወዴት ነው የምትሄደው’ ብዬ ቀላል ጥያቄ ብጠይቀው እሱ የተራቀቀ ፍልስፍና ይመልስልኛል ?’ ልጁ ወደ ቤተ መቅደሱ ተመልሶ፣ “ትዕዛዝዎትን አፍርሼ አጥፍቻለሁ መምህር ሆይ …” አለ እናም የሆነውን ነገራቸው… “ኦ … ይሄማ አይሆንም” አለ መምህሩ በንዴት፣ “ማሸነፍ አለብህ፡፡ እንዳሳፈርህ ማሰፈር አለብህ፡፡ መቼም ቢሆን ከእነሱ ጋር በክርክር ተሸንፈን አናውቅም፡፡ አንድም ጊዜ !!! ስለዚህም ነገ እዛው ቦታ ትጠብቀውና ‘ወዴት ነው የምትሄደው’ ትለዋለህ፡፡ እንደ ልማዱ ‘ንፋሱ ወደ ወሰደኝ ቦታ…’ ሲል፣ ‘ንፋሱ ባይነፍስስ… ምን ታመጣለህ ?’ ብለህ ታፋጥጠዋለህ” ልጁ በጣም ተደሰተ፡፡ ነግቶ ብድሬን በመለስኩ ብሎ እንቅልፍ ባይኑ ሳይዞር አደረ፡፡ ለሊቱን ሙሉ እንዴት ብሎ እንደሚጠይቀውና እንደሚያሳፍረው ያጠናትንን ሲደጋግም አደረ፡፡ በቀጣዩ ቀን በጠዋት መንገድ ላይ ሆኖ ልጁን ይጠብቀው ጀመር፡፡ ልጁ ሲመጣ “ወዴት ነው የምትሄደው ?” ሲል ጠየቀው፡፡ “እግሬ ወደ ወሰደኝ ቦታ” አለ ልጁ፡፡ ያልተጠበቀ መልስ፡፡ አሁንም ልጁ የሚመልሰው አጥቶ እንደሞኝ ፈዝዞ ቀረ፡፡ ምክንያቱም ያጠናት መልስ አሁን ለዚህች ጥያቄ አትሰራማ… ‘ምን አይነት መጥፎ ሰዎች ናቸው ግን እነዚህ የዛኛው ቤተ መቅደስ ሰዎች’ አለ ልጁ፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ ተመልሶ ለመምህሩ የሆነውን ሁሉ ነገረው፡፡ “ችግር የለውም፡፡ የፈለገ ቢሆን ማሸነፍ አለብን፡፡ እርግጥ እነሱ መሰሪዎች ናቸው፡፡ ቢሆንም በክርክር ተሸንፈን አናውቅማ፡፡ ስለዚህ መሸነፍ የለብህም፡፡ ነገ እዛው ቦታ ትጠብቀውና፣ ‘ወዴት ነው የምትሄደው’ ትለዋለህ፡፡ ‘እግሬ ወደ ወሰደኝ ቦታ…’ ሲልህ ወዲያው ቀበል አድርገህ ‘ሽባ ሆነህ ብትወለድስ ኖሮ … በምንህ ትሄዳለህ’ ትለዋለህ - አዎን እንዲያ ብለህ ታፋጥጠዋለህ” አለ መምህሩ፤ “እንጂ መሸነፍማ የለብህም” በቀጣዩ ቀን እዛው ቦታ መጠበቅ ጀመረ፡፡ ልጁ ሲመጣ፣ “ወዴት ነው የምትሄደው ?” አለው፡፡ “ሰላጣ ለመግዛት ወደ ገበያ እየሄድኩ ነው” አለ ልጁ… እሺ አሁን ልጁ ምን ይበል… ሕይወት እንዲሀ ነች፡፡ ጥያቄ አዘጋጅተህ ስትመጣ እሷ ትቀይረዋለች፤ “ሰላጣ ልገዛ ወደ ገበያ እየሄድኩ ነው” ትልሃለች፡፡ የተዘጋጀ መልስ ለሕይወት አይረዳህም፡፡ የትላንት መልስ ለዛሬ ዋጋ የለውም፡፡ እያንዳንዱን ቅፅበት በጥልቀት እያየህ ለየቅፅበቱ ምላሽ ካልሰጠህ ከሕይወት ጋር ትተጣጣላችሁ፡፡ ቅፅበት በቅፅበት ኑር፡፡ የትላንት መረጃ እና እውቀት የዛሬን ሁነት እንዳታይ እንዳይከልልህ ተጠንቀቅ… ቅፅበት በቅፅበት ኑር… ትርጉም በግሩም ተበጀ Join us
Show all...
ሰው ለዝምታ ራቅ ያለ ገጠራማ ስፍራ ምርጫው ነው። ለእንደኔ ላለ ከተምኛ ዝምታ የማይቻል ነው። ይልቅ ለነገሬ ሁሉ ለሊትን እመርጣለሁ። ሰማያዊ ሰማይ ብርሃን፤ብልጭ ድርግም የሚሉ የመንገድ መብራቶች፤ የግርግዳ ላይ ስዕሎች፤ በንፋስ የሚገፉ ስስ ፌስታሎች፤ በየጣርያው የሚዘሉ ድመቶች፤ ውሃ ያቆሩ ግርድፍ መሬቶች፤ የገደል ማሚቱ የዋጠው ጭር..ረጭ! ያለ ከተማ ውስጥ ዝም ማለት ባልችል እ'ኳ ከራሴ ጋር አወራለሁ: :
Show all...
ምንም ብር ሳታወጡ እንዴት ብር እንደምታገኙ እዚ ቦት ላይ ገብታቹ ኬኖ በመጫወት ብቻ መጀመሪያ እራሱ 15 ብር ይሰጣቹሀል ማውጣትም ትችላላቹ ሞክሩት ይጠቅማቹሀል 👌
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!