cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

አልፋ ና ዖሜጋ ነህ

ራዕይ 1:8 ያለውና የነበረው የሚመጣው ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ ፦ አልፋ ና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል፡፡ ራዕይ 21:6 አልፋ ና ዖሜጋ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ ለተጠማ ከሕይወት ውሃ ምንጭ እንዲያው እኔ እሰጠዋለሁ፡፡ ራዕይ 22፡13 አልፍ ና ዖሜጋ ፊተኛውና ከኃለኛው መጀመሪያው ና መጨረሻው እኔ ነኝ፡፡ @kalyewude

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
178Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

✨በማይመጥንህ ሰፈር አትገኝ አንድ አባት ከመሞቱ በፊት ለልጁ እንዲህ አለው "የሄን ሰአት አያትህ ነው የሰጠኝ በትንሹ 200 አመት ይሆነዋል አሁን ላንተ ከመስጠቴ በፊት "እዚ ሰፈር ያለው የሰአት መሸጫ ሱቅ ሂድና ስንት እንደሚያወጣ ጠይቀህ ና አለዉ" ልጁም ደርሶ መጣና ለአባቱ፡"አባዬ ሰአት ሻጩ ሰዉዬ አሮጌ ሰአት ነው አልገዛም አለኝ" አለው አባቱም አሁን ደግሞ ወደ ካፌ ብቻ ሰዎች ሰብሰብ ያሉበት ቦታ ሄደህ የገዙህ እንደሆን ጠይቅ አለው! ልጁም ደርሶ መጣና አባዬ አንድ ሰውዬ 100 ብር ልግዛህ አለኝ አሁን ደግሞ ሙዚየም ሄደህ ጠይቅ አለው ደርሶም መጣና 100,000 ብር እንግዛህ አሉኝ አለው፡፡ አባትየውም እንዲህ አለው "ያንተን ዋጋ የሚወስነው ትክክለኛ ቦታ ላይ ስትገኝ ብቻ እንደሆነ እንድታውቅ ነው እንዲህ ያረኩት፡፡ እራስህን ባልተገባ ቦታ ለማስገባት አትግፋው ትርፉ መናደድ እና መማረር ብቻ ነው። ዋጋህን የሚያዉቁት የሚያውቁህ ናቸውና አንተን በማይመጥንህ ሰፈር አትገኝ፡፡ ዋጋህ ውድ ነው የተገዛኸው በክርስቶስ ደም ነው ስለዚህ ዋጋህን በማይመጥን ሰፈር አትገኝ፡፡ ✝ @Excellent_youth ✝ ✝ @Excellent_youth
Show all...
. አመለጠች ነፍሴ ሳሙኤል ተ/ሚካኤል || NEW SONG 🕐-6:58Min-||-💾-6.3MB ▷THE GOSPEL IS CHRIST◁ Share 📲 Share 📲 Share ▷ @christ_progeny_tube ◁ ▷ @christ_progeny_tube ◁ △Join us△
Show all...
. አመለጠች ነፍሴ ሳሙኤል ተ/ሚካኤል || NEW SONG 🕐-6:57Min-||-💾-30.3MB ▷THE GOSPEL IS CHRIST◁ Share 📲 Share 📲 Share ▷ @christ_progeny_tube ◁ ▷ @christ_progeny_tube ◁ △Join us△
Show all...
እንካ ልቤን        ወዳጄ ኢየሱስ አንተ የልብ አምላክ ነህ። የልቤን በር በፍቅር ማንኳኳት ሳይሰለችህ በልቤ ደጃፍ ቆመሀል እኔ ግን በምቾት ሰንሰለት፣ በስንፍና ገመድ፣ በእንቅልፍ ቁልፍ በሬን ቀርቅሬ ደጅ አስጠናሁህ። አሁን እንኳ ምቾትን ልጠየፍ፣ ስንፍና ይሰልቸኝ፣ ከእንቅልፌም ልንቃ። እንካ የልቤን ቁልፍ፣ እንካ የሕይወቴን ቁልፍ።       ቁልፍ ለታማኝ እንጂ ለሌባ አይሰጥም፣ ቁልፍ ለጨዋ እንጂ የእጅ አመል ላለበት አይሰጥም፣ ቁልፍ እንደልብ ለሆነ ሰው እንጂ እንደ ልቡ ለሆነ ሰው አይሰጥም አንተ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ነህና እንኳ ቁልፌን ክፈተኝ፣ አስተካክለኝ።       ካንተ የምደብቀው ምስጢር የለኝምና የደስታዬን በር ተቆጣጠረው፣ የኅዘኔ መግቢያ ባንተ ብቻ ተከፍቶ ይዘጋ፣ የስኬቴና የውድቀቴ መስኮቶችም ባንተ ይዘወሩ፣ እኔ እንኳን የማላውቃቸው በሮቼ ሁሉ ባንተ ቁጥጥር ስር የዋሉ ይሁኑ።      ካንተ የምሸሽገው ጓዳ የለኝም ስለ ትዳሬ የምጨነቅበት ቁልፍ ይኸው፣ ይህ ደግሞ የልጆቼ ቁልፍ ነው፣ የሰርጌና ምላሹ ነገርም አንተ ካልከፈትከውና ካልዘጋኸው ባዶ ነው። ከማንም የምደብቀው የውስጥ ምሥጢሬ ቁልፍም ይኸው! እስከዛሬ እኔ ይዤው ሸክም ነው የኾነብኝ። አምላኬ ሆይ የኑሮዬን ቁልፍ ተቀበለኝና ሸክሜ ይቅለልልኝ።        እኔ ስከፍትና ስዘጋ ወና የነበረውን ሕይወቴን እስኪ ቁልፉን ያዝና አንተ ሙላው። ለብቻዬ ይዤው እኔ ምን ፈየድኩ? ካንተ ተነጥዬ ያፈራሁት በርና መዝጊያ ኹሉ ስንት ዝብርቅርቅን ፈጥሯል መሰለህ!? ጌታዬ ሆይ ይኸው ቁልፉ… እስኪ አንተ ግባና አስተካክለው፡፡           ይቀጥላል........................              ከተማርኩበት ✍አዶኒ @adonigospel @adonigospel
Show all...
Show comments
እ/ር ተስፋ አደርጋለሁኝ እሱም ይረዳኛል ❤️የዘማሪው የትላንት ታሪክ መዝሙር 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው? ² ክፉዎች፥ አስጨናቂዎቼ ጠላቶቼም፥ ሥጋዬን ይበሉ ዘንድ በቀረቡ ጊዜ፥ እነርሱ ተሰናከሉና ወደቁ። ³ ሠራዊትም ቢሰፍርብኝ ልቤ አይፈራም፤ ሰልፍም ቢነሣብኝ በዚህ እተማመናለሁ። ⁴ እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ። ⁵ በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛልና፥ በድንኳኑም መሸሸጊያ ሸሽጎኛልና፥ በዓለት ላይ ከፍ ከፍ አድርጎኛልና። ⁶ እነሆ፥ አሁን በዙሪያ ባሉ በጠላቶቼ ላይ ራሴን ከፍ ከፍ አደረገ፤ በድንኳኑም የእልልታ መሥዋዕትን ሠዋሁ፥ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ እዘምርለትማለሁ። ♥አሁን ዘማሪው ህይወትተ መዝሙር 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ፤ ማረኝና አድምጠኝ። ⁸ አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ። ⁹ ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ። ¹⁰ አባቴና እናቴ ትተውኛልና፥ እግዚአብሔር ግን ተቀበለኝ። ¹¹ አቤቱ፥ መንገድህን አስተምረኝ፥ ስለ ጠላቶቼም በቀና መንገድ ምራኝ። ¹² የሐሰት ምስክሮችና ዓመፀኞች ተነሥተውብኛልና ለጠላቶቼ ፈቃድ አትስጠኝ። ♥ግን ወደፊት በእኔ ዘመን መዝሙር 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕያዋን ምድር አይ ዘንድ አምናለሁ። ♥ስሙ ቅዱሳን ¹⁴ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ። ከቃልኪዳን ንጋቱ @Kalyekal
Show all...
#የሕይወት ትርጉም ኢየሱስ ➥ ወንድሜ በሕይወትህ አንድ ቀን እደርስበታለው ብለህ ያሰብከው ህልምህ የደረስክበት ቀን ሕይወትህ ከዚያን ቀን በኋላ ትርጉም እንደሚሮረው የምታስብ ከሆነ እንግዲያውስ ልንገርህ አንተ ከሁሉም ሰው ይልቅ ሞኝ ነህ። መኖርህ ትርጉም ሊያገኝ የሚገባው ዛሬ ነው። አንተ እንድትኖር የተፈለገው ዛሬን ነው ። እርካታና ደስታ ከብዙ ጥረትና ስራ በኋላ የምትደርስባቸው እንደሆኑ አስበህ ሩቅ አታድርጋቸው። ወንድሜ ከሰሎሞን ተማር እንጂ ሕይወትህ ትርጉም የሚያገኘው በሰበሰብከው ገንዘብ፣ዕውቀት፣የሰዎች ፍቅር፣የእናንትህና የአባትህ አድናቆት አይደለም።ንጉስና ጠቢብ የነበረው ሰሎሞን አንተ በሕይወት ዘመንህ የምትመኛቸው ነገሮች በሙሉ እንዲያውም ከዚያ በላይ ነበረው ነገር ግን ለሰለሞን ሁሉ ከንቱ ነበረ። እነዚህ አሁን አንተ እየሰበሰብካቸው ያለሀቸው ነገሮች ያንተን ሕይወት ትርጉም ሊሰጧት በፍፁም አይችሉም። ሕይወትህን ትርጉም የሚሰጣት ነገር አጠገብህ ነው ያለው። ኢየሱስ ይባላል! ወንድሜ አይንህን ክፈት ደስታ አጠገብህ ነው ያለው። እርካታ አጠገብህ ነው ያለው። ምናልባት ይሄን የምታነቡ ፕሮቴስታንት ልጆች ለቀባሪው አረዳው በሚል አስተሳሰብ እያነበባቹት ሊሆን ይችላል ሚገርመው ግን መልዕክቱ ለናንተ ነው። የተቀበልከው ሐይማኖት አይደለም ሕይወት ነው። የዘለዓለም ደስታና ዕርካታ ያለበት ሕይወት። የሚያሳዝነው ግን አንተም ጌታን እንደማያውቅ ሰው ሕይወትህን በምትሰበስባቸው ነገሮች ትርጉም ልትሰጣት መሞከርህ ነው። “የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።” — ሮሜ 14፥17 ➛ ብራዘር የመዳን ቀን ዛሬ ነው የሚለው ቃል ለጴንጤም የተፃፈ ነው። የደስታ ቀን ዛሬ ነው! የመርካት ቀን ዛሬ ነው! የተቀበልከው ፅድቅ የዛሬ ነው። በእግዚአብሔር አለም ነገ የሚባል ነገር የለም። ሁሉም ነገር አሁን ነው። አሁንና አሁን ነው። ጌታ አሁን ከወደደህ በላይ ነገ አይወድህም። ጌታ እንድትደሰት የሚፈልገው አሁን ነው። “ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤” — 1ኛ ዮሐንስ 1፥2 ፀጋና ሰላም ይብዛላቹ። Share Share Share 👇👇👇👇👇👇👇 @Pure_Christianity @Pure_Christianity @Pure_Christianity
Show all...
ኢየሱስ ዛሬም አማላጃችን ነው።❗️ “የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።” — ሮሜ 8፥34 ➛ክርስቶስ ይማልዳል ማለት ያስታርቃል ማለት ነው። ሐጢያትን ያስተሰርያል ማለት ነው። አሁንም ቢሆን በክርስቶስ በኩል ወደ እግዚአብሔር ለሚመጡ ሰዎች ክርስቶስ መሀከለኛ ነው። ክርስቶስ የአለምን ሁሉ ሀጢያት የተሸከመ የእግዚአብሔር በግ ነው። ሰዎች ሁሉ ስለበደሉት በደል ማስተሰሪያ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር ራሱ ያቀረበው ንፁህ ፣ቅዱስና ያለ ነውር የሆነ መስዋዕት ነው።በክርስቶስ በኩል ሆነን ወደ አብ የመግባት ድፍረት አለን። አሜን! ➞ኢየሱስ ክርስቶስ ሀጢያሠታችንን በማስተሰረይ ከዘላለም ሞት የሚያድነን ፣ ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርበን በእግዚአብሄርና በኛ መካከል መካከለኛ ሆኖ እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ሊያስታርቅ ብቃት እና ውክልና አለው።ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእርቅ ውላችንና ሠነዳችን ነው። ➫ በክርስቶስ ደም ምክንያት ከ እግዚአብሄር ጋር ሠላም አለን። በሀጢያት ወድቀን ብንገኝ እንደወደቅን እንዳንቀር ከ አብ ዘንድ ለድካማችን ጠበቃ አለን!!ሀሌሉያ ጠበቃ አለን።ጠበቃ ማለት እኛን ከተከሰስንበት ክስ ለማዳን የእኛ በሆነ ነገር ሁሉ ላይ ስለኛ ተወክሎ የሚቆም ማለት ነው። ክርስቶስ ጠበቃችን ነው። የክርስቶስ ክህነት ፍፁም እና ለዘላለም ነው።አሜን እንደዚህ አይነት ሊቀ ካህን ይገባናል ➛ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራኒዮ መስቀል ላይ የከፈለዉ የደሙ ዋጋ ለዘላለም ቤዛ ሁኖ፣ ለዘላለም አስታራቂ ሁኖ ለዘላለም አማላጅ ሁኖ የሠው ልጆችን ሁሉ በራሱ በኩል ከእግዚአብሄር ጋር ማስታረቅ ይችላል። ➥የእግዚአብሔር እውነት አንድ ነው እርሱም ወደ ዘላለም ሒወት ለመግባት የሚወድ ቢኖር በክርስቶስ ኢየሱስ /በደሙ/ በኩል እንዲመጣ ነው!! 📖“ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።” ዕብራውያን 7፥25 📖“አንድ እግዚአብሔር አለና፤ ደግሞም በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል አንድ አስታራቂ አለ፤ እርሱም ሰው የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤”— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5 (አዲሱ መ.ት) 📖“ልጆቼ ሆይ፤ ይህን የምጽፍላችሁ ኀጢአት እንዳትሠሩ ነው፤ ነገር ግን ማንም ኀጢአት ቢሠራ፣ በአብ ዘንድ ጠበቃ አለን፤ እርሱም ጻድቁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።” — 1ኛ ዮሐንስ 2፥1 (አዲሱ መ.ት) 📖“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥” — ዕብራውያን 10፥12 📖 የእግዚአብሔር ጠላቶች ሳለን በልጁ ሞት ከእርሱ ጋር ከታረቅን፣ ዕርቅን ካገኘን በኋላ፣ በሕይወቱማ መዳናችን እንዴት የላቀ አይሆንም! ይህ ብቻ አይደለም። ነገር ግን አሁን ዕርቅን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ ሐሤት እናደርጋለን። ሮሜ 5 ፥10-11(አዲሱ መ.ት) 📖“በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ ሰላምን በማድረግ በምድርም ሆነ በሰማይ ያለውን ነገር ሁሉ በእርሱ በኩል ከራሱ ጋር አስታረቀ።” — ቆላስይስ 1፥20 (አዲሱ መ.ት) ➫ ኢየሱስ ክርስቶስ አድኖአችኋል ማለት ከነበረባቹ የሀጢያት ህመም ወይንም በሽታ ተፈውሳችሁ ፃዲቅ ሆናችኋል ማለት ነው። ➙ ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተበት ዋነኛ አላማውም ይሄ ነው። ❗️ ➙ በረከቶች ሀዲስ ኪዳን ስለ ፅድቅ ብቻ ነው የሚያስረዳን ፣ ፅድቅ እንዴት ሰዎች ጋር እንደሚደርስና ሰዎች እንዴት በእግዚአብሔር ፊት ተመልሰው መቆም እንደሚችሉ ነው የሚያወራው። ሀዲስ ኪዳን ይዞ የመጣው ትልቁ የምስራች ፅድቅ ነው። ፅድቅ ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት መቆም የሚቻልበት ድፍረት ወይንም አቅም ነው። 〰️ አንተ በራስህ አቅም ስለማይቻል ይህን ችሎታ ከእግዚአብሔር ለመቀበል በመሀል ፀጋ የሚባል ነገር አስፈላጊ ሆነ። ፀጋ ማለት ፅድቅ የተቀበልክበት መንገድ ነው። አንተ ፃዲቅ የምትሆነው በፀጋ ነው። ማለትም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሰርቶ በጨረሰው ስራ በኩል ነው። አለቀ! ➙ማንም ሁኑ፣የትም ሁኑ ፣ምንም ሁኑ እንዴትም ሁኑ ወዴትም ጌታ ይወዳቹሀል❗️🥰 ከዛሬ ጀምሮ ህይወቴን ለዚ ጌታ ሰጥቼ ከዚ ጌታ ጋር በፍቅሩ መኖር እፈልጋለሁ የምትሉ ይህንን መልዕክት የምታነቡ ሠዎች። ይህንን ፀሎት ባላቹበት ቦታ ሁናቹ ፀልዩ። ጌታ ኢየሱስ ሆይ በመስቀል ላይ ስለ እኔ ሀጢያት እንደሞትክ በሶስተኛው ቀን ለዘላለም ከአንተ ጋር በሕይወት እንድኖር ከሞት እንደተነሳህ በልቤ አምናለሁ በአፌም እመሰክራለሁ። አንተ ጌታዬ ነህ። አለምን ፣ሀጢያትን፣ዲያቢሎስን ክጃለሁ። ነብሴን ለአንተ አደራ እሰጣለሁ ተቀበለኝ። ስለተቀበልከኝ አመሰግንሀለሁ። አሜን! ፀጋና ሠላም ይብዛላቹ። 🙏ይሄንን መልዕክት አንብባቹ የጨረሳቹ ሼር ሳታደርጉ እንዳታልፉ❗️ 👇👇👇👇👇👇👇 ቻናሉን ለማግኘት @Pure_Christianity @Pure_Christianity @Pure_Christianity @Pure_Christianity
Show all...
ወደ ክብር አገልግሎት እንዴት ልግባ🔥🔥 1⃣.ልብህን አንፃ ⛳️በፍቅር፣በትህትና፣በምህረት የተሞላ ሰው ሁን። 📖ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። 2⃣.ፀልይ ⛳️አንተ እግዚአብሔርን ስትፈልግ ብቻ ሳይሆን እርሱ ሲፈልግህ ተገኝለት ⛳️ጥያቄ ማቅረብ ብቻ ሳይሆን ድምፁን መስማት ተለማመድ 3⃣.ህይወትህ በአምልኮ የተሞላ ይሁን፤ 📖ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው። 4⃣.በፍፁም ልብህ እግዚአብሔርን ታመን ⛳️ጥርጣሬ፣አለማመን፣ገደብን ከህይወትህ አስወግድ እርሱ ባሰበልህ ልክ ተጓዝ ፤ ለአሰራሩ ገደብ አታበጅ፤ 📖የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ይህን ሾላ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል ብትሉት ይታዘዝላችሁ ነበር። 5⃣.ከቅዱሳን ጋር በእውነትና በአንድ መንፈስ ህብረት አድርግ ⛳️አጠገብህ ካለው ሠው ጋር ፀጋን ተካፈል 📖የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፥ ሥጋ ለባሹም ሁሉ በአንድነት ያየዋል፥ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና። 🗞ማቴ 5:8 ዮሐ 10:27 ያዕ 1:27 ሉቃ 17:6 ኢሳ 40:5 @jesusministry
Show all...
🎄 #የማለዳ_ስንቅ የመንፈስ ረሃብ የሚለቅ አምልኮ አድምጡልኝ! @nazrawi_tube @nazrawi_tube
Show all...