cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

✞Semayawi~tesfa✞

Semayawi~tesfa 👉የዚህገጵዋናአላማ:-መልእክቶች:መጽሀፍቶች:ትምህርቶች:የቅዱሳን ታሪኮቻቸው እንዲሁም ሌሎችንም በተዘጋጁበት ቋንቋ ጥራት እና መጠን ሁሉ በ1ቦታ እንዲገኙ ለማድረግ ነው◈

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
189Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

††† እንኳን ለቅዱስ አባ ሞይስስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ቅዱስ አባ ሞይስስ ጻድቅ ††† ††† ቅዱሱ በኋላ ዘመን ከተነሱ አበው አንዱ ሲሆን ትውልዱ: ነገዱ ከግብፅ ነው:: ዘመኑ ዘመነ ዐጸባ ቢሆንም ክርስቲያኖች ጠንካሮች ነበሩ:: አባ ሞይስስ ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: ገና በልጅነት ወደ ትምህርት ቤት ገብቷል:: ††† የዘመኑ ትምሕርት ሁለት ወገን ሲሆን 1ኛው የሃይማኖት ትምሕርት: 2ኛው ደግሞ ፍልስፍና ነበር:: የጻድቁ ምርጫው የቤተ ክርስቲያን ትምሕርት ነበርና ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምሯል:: እንደሚገባ ተምሮ ስለ ነበርም ዲቁናን ሹመውት ተግቶ አገልግሏል:: ከጥቂት ዘመናት በኋላም በተሻለው ጐዳና እግዚአብሔርን ሊያገለግል ተመኘ:: ይህቺን ዓለምም ይንቃት ዘንድ ወደደ:: መልካም ምኞትን መፈጸም ለእግዚአብሔር ልማዱ ነውና የልቡናውን ተምኔት ፈጸመለት:: ከከተማ ወጥቶ: ቁራጭ ጨርቅ ለብሶ ገዳም ገባ:: በዚያም በረድእነት ያገለግል ገባ:: በፍጹም ልቡ በትሕትና እግዚአብሔርን ደስ አሰኘ:: በጉብዝናው ወራት ይህንን መርጧልና:: ገዳሙንም ሲያገለግል ዕረፍትም አልነበረውምና በመነኮሳት ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነው:: ከጊዜም በኋላ "በቅተሃል" ብለው አበው ከአሞክሮ ወደ ምንኩስና: ከምንኩስና ወደ አስኬማ አሸጋግረውታል:: እርሱም ለአሥራ ስምንት ዓመታት አገልግሎቱን ሳያስታጉል: ወጥቶ ወርዶ ገዳሙን ረድቷል:: በእነዚህ ጊዜያት በጸሎት: በጾምና በስግደት ይጋደል ነበር:: በጠባዩም ትእግስትን: ትሕትናን: ተፋቅሮን የሚያዘወትር ነበር:: ጐን ለጐንም ለቤተ መቅደስ አገልግሎት ይፋጠን ነበር:: በዘመኑ የግብፅ ፓትርያርክ አባ ሚካኤል ይባሉ ነበር:: አውሲም በምትባል አውራጃ ኤጲስ ቆጶስ ዐርፎባቸው "ማንን ልሹም" እያሉ ይጨነቁ ነበርና እግዚአብሔር ስለ አባ ሞይስስ ገለጠላቸው:: አባ ሚካኤልም "ለሕዝቤ የሚጠቅም መልካም እረኛ አገኘሁ" ብሎ ደስ አለው:: ጊዜ ሳጠፋም እርሱን አስጠርቶ "ተሾም" አለው:: አበው ትሕትና ሙያቸው ነውና "አይቻለኝም: ተወኝ ይቅርብኝ" ሲል መለሰ:: አባ ሚካኤል ግን "የምሾምህ መቼ በሰው ፈቃድ ሆነና: በእግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ" ብሎ ዕለቱኑ ሹመውታል:: እርሱም የአውሲም ጳጳስ ሆኗል:: ቅዱሱ አባ ሞይስስም ወደ ሃገረ ስብከቱ ሔዶ አገልግሎቱን ጀመረ:: በጵጵስና ዘመኑ እንደ ከተማ ሰው መኖርን: የሥጋ ምቾትን አልፈለገምና ጠባቡን መንገድ መርጧል:: በገዳም ሲሰራው ከነበረው ተግባር መካከል ያቋረጠው አልነበረም:: ከብቃቱ የተነሳ ለወደፊት የሚደረገውን ያውቅ ነበር:: እርሱ የተነበየው ሁሉ ተፈጽሟልና:: ሕዝቡን ይመራቸው ዘንድም ተግቶ ያስምራቸው ነበር:: ዘወትርም ከክፋት: ከኃጢአት ይጠብቃቸው ዘንድ ይጸልይላቸው ነበር:: ያዘኑትን ሲያጽናና: በደለኞችን ሲገስጽ ዘመናት አለፉ:: አንድ ወቅት ላይም ስለ ሃይማኖቱ ታሥሮ በረሃብ ተቀጥቷል: ግርፋትንም ታግሷል:: ጻድቁ ጳጳስ አባ ሞይስስ እንዲህ ተመላልሶ የሚያርፍበት ቀን ቢደርስ ሕዝቡን ሰበሰባቸው:: "እኔ ወደ ፈጣሪዬ እሔዳለሁና ሃይማኖታችሁንና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቁ" ብሏቸው በትእምርተ መስቀል አማትቦ ዐረፈ:: ምዕመናንም በብዙ እንባና ምስጋና ቀብረውታል:: ከተቀደሰ ሥጋውና ከመቃብሩም ብዙ ተአምራት ታይተዋል:: ††† አምላከ ቅዱሳን ከቅዱሱ አባት በረከት ይክፈለን:: ††† ነሐሴ 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ አባ ሞይስስ 2.ቅዱስ አብጥልማዎስ 3.ሦስት መቶ ሰማዕታት (የቅዱስ ፋሲለደስ ማኅበር) ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ያሬድ ካህን 2.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት 3.ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና 4.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ 5.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት ††† "ስለዚህ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት: ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ:: ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ እኔ አውቃለሁ:: ስለዚህ ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሰጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ::" ††† (ሐዋ. ፳፥፳፰) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
Show all...
""✝ የጾመ ፍልሠታ ትምህርት✝  "" ወላዲተ  አምላክ በገድለ ጻድቃን ኢትዮጵያውያን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ  2011  ክፍል  9⃣  ቀን ፲(10)         ❇️መልከአ ኤዶም ትርጓሜ❇️ ✝በመምህር ዲ/ዮርዳኖስ አበበ ✝ ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር። " ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/ https://t.me/zikirekdusn 🛑የ2011
Show all...
✝እንኳን አደረሳችሁ!✝ ✝ከፋሌ ባሕረ ተከዚ አቡነ ዓቢየ እግዚእ! ☞መንስኤ ሙታን ☞ፈዋሴ ዱያን ☞መምህር ዘበአማን ☞ምዑዝ ከመ እጣን . . . ❀ተከዜን በየብስ የተሻገራት፥ ፱፻፵፩ አሕዛብን ያጠመቀ፥ ጎንደርን ከአራዊት ይታደጋት ዘንድ ቃል ኪዳንን የተቀበለ! በረከቱ ይደርብን! (ስዕሉ ከጥንታውያኑ አንዱ ነው) https://t.me/zikirekdusn
Show all...
✝✝✝ እንኳን ለቅዱሳን #ማኅበረበኲር ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ ✝✝✝ ☞ማኅበረ በኲር (ዕብ. ፲፪:፳፫) ማለት ከዓለም ፍጥረት እስከ መድኃታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ድረስ የተነሱ/የሚነሱ ቅዱሳን ሁሉ የጋራ መጠሪያ ነው፡፡ ☞እነዚህም አበው፡ ነቢያት፡ ሐዋርያት፡ ጻድቃን፡ ሰማዕታት፡ ደናግል፡ መነኮሳት፡ ባሕታውያን፡ ሊቃውንት፡ ጳጳሳት፡ ካህናት፡ ዲያቆናት፡ ነገሥታት እና ምዕመናን ናቸው፡፡ ☞ታቦታቸው/ቤተክርስቲያናቸው ታች አርማጭሆ #ደብረመጉና (ሞጊና) ውስጥ ይገኛል፡፡ ☞ነሐሴ10 ደገኛ በዓላቸው ነው፡፡ <<< በረከታቸው በዝታ ትደርብን፡፡ >>> ✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊትጉባኤ ዘጎንደር✝ " ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/ https://t.me/zikirekdusn
Show all...
✝ የጾመ ፍልሠታ ትምህርት 2014/፳፻፲፬ ✝ (ክፍል ፱/9) ✝"ኪሩቤል/፬ቱ እንስሳና እመቤታችን!" ✝የተፈሥሒ ማርያም ትርጓሜ! (ነሐሴ 8 - 2014) ✝በመምህር ዲ/ዮርዳኖስ አበበ ✝ ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር። " ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/ https://t.me/zikirekdusn  
Show all...