cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ምስጋና ህብረት

እራስን መሆን😁 For info 👇 @Dadeeeeee

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
184Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አሁን ነው!! ትልቁና ልትጠቀመው የሚገባው አጋጣሚ አሁን ያለህበት ሁኔታና አጋጣሚ ነው። አሁን በዚህ ሰዓት ለአንተ ከዚህ የተሻለ ሁኔታ፣ ቦታና አጋጣሚ የለም። ምንም ለማድረግ ይሁን፣ ምንም ለመጀመር ከዚህ የተሻለ ጊዜ ሊመጣልህ አይችልም፣ በእጅህ ያለውን ነገር ስትጠቀመው ስለ ቀረውና ስለሚመጣው ማሰብ ትችላለህ። አዎ! ጀግናዬ..! አሁን ነው ጊዜህ፣ አሁን ነው ያሰብከውን የምትጀምረው፣ የምትፈፅመው፣ የምታከናውነው። የሚመጣውን መጠበቅህ ጊዜህን፣ ተስፋህን፣ ጥበቃህንም ሊጎዳህ ይችላል። ጀምበር ካዘቀዘቀች፣ ጊዜው ከረፈደ፣ ሰብሉም ከደረቀ፣ ጉልበትም ከደከመ፣ ውሃውም ከፈሰሰ ቦሃላ የምታደርገው ነገር ወጪው፣ ጫናው፣ ድካሙ ብዙ ነው። አዎ! ከዚህ የተሻለ አጋጣሚ የለህምና ማድረግ ያለብህን ነገር አሁን አድርግ።
Show all...
 ደህንነታችን ዘላለማዊ ነው  🙄በዘላለም ዋስትና ብዙውን ጊዜ የሚነሳው ተቃውሞ ይህ አስተምህሮ ሰዎች ድነታቸውን ስለማያጡ እንደፈለጉ እንዲኖሩ ፈቃድ ይሰጣል ወይንም በሀጥያት መኖር ይችላሉ የሚል ነው። ይህ ደግሞ ስናየው እውነት ቢመስልም መፅሀፍ ቅዱሳዊ አይደለም።  🙏አንድ ሰው በእውነት በኢየሱስ ክርስቶስ ከተዋጀ ሀጥያትን ልምምድ ያደረገ ህይወት አይኖረውም።  👉መፅሀፍ ቅዱስ ደህንነት በፀጋ ብቻ፥ በእምነት ብቻ እና በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ እንደሆነ ይነግረናል።( ኤፌ ምዕ. 2) 8፤ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤9፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።  👉ሰው በእውነት በኢየሱስ ክርስቶስ ባመነበት ቅፅበት ድኗል እንደገናም ደህንነቱም ዋስትና አግኝቷል። ነገር ግን አንድ ሰው #ድነት #በእምነት ነው #የምንቀበለው #ካለ በኋላ #ፀንቶ ለመኖር #መስራት አለብን ቢል ይህ መፅሀፍ ቅዱሳዊ #አይደለም።  ጳውሎስ በገላቲያ መልዕክቱ ” እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጸማላችሁን? “(ገላትያ 3:3) 👉 በእምነት ከዳንን ድነታችን ፀንቶ የሚኖረው እና ዋስትና የሚያገኘው #በእምነት ብቻ ነው። ድነታችንን በራሳችን #ጥረት ማግኘት #አንችልም። ስለዚህ ድነታችንን በራሳችን ጥረት #ማፅናት #አንችልም። 👉 እግዚአብሔር ብቻ ነው ድነታችንን ማፅናት የሚችለው። ( ይሁዳ 24)  የእግዚአብሔር እጅ ነው ማንም እንዳይወስደን አጥብቆ የያዘን።( ዮሀንስ 10:28~29)  የእግዚአብሔር ፍቅር ነው ማንም ከእርሱ ሊለየን እንዳይችል የደረገው ( ሮሜ 8:38~39)  👉በዘላለም ዋስትና(ያለመጥፋት) ላይ የሚነሳ ማንኛውም ተቃውሞ ድነትን #በሰው #ጥረት እና #አቅም #የሚፀና እንደሆነ #ማመን ነው።ይህ ደግሞ በፀጋ መዳን ከሚለው ጋር #የሚጋጭ ነው። ምክንያቱም የዳንነው በኢየሱስ መልካምነት እንጂ #በእኛ $መልካምነት አይደለም።(ሮሜ 4:3~8)… ድነታችንን ለማፅናት/ላለመጥፋት የሙሴ ሕግ መጠበቅ ወይንም መስራት አለብን ማለት የኢየሱስ #ሞት ለእኛ #ሀጥያት #በቂ #ክፍያ #አይደለም #ማለት #ነው። #የኢየሱስ ሞት ግን #ላለፈው ፥ላሁኑ እና #ለወደፊቱ ሀጥያታችን የተከፈለ ከ በቂ በላይ የሆነ ዋጋ ነው። (ሮሜ 5:8 ;1ቆሮ 15:3 ; 2 ቆሮ 5:21)  👉ታዲያ ይህ ማለት አንድ ክርስቲያን 🚫እንደፈለገው መኖር #ይችላል እና #ድነቱን #አያጣም #ማለት ነውን?  መፅሀፍ ቅዱስ ለዚህ ጥያቄ መልሱ #ክርስቲያኖች #እነሱ እንደፈለጉ ሊኖሩ #አይችሉም የሚል ነው። ✔ክርስቲያኖች አዲስ ፍጥረት ናቸው።( 2 ቆሮ 5:17)  ✔ክርስቲያኖች የመንፈስ ፍሬዎች የሚገለጥባቸው ናቸው።( ገላ 5: 19~21)  ✔ክርስቲያኖች ሀጥያትን እንደልምድ አርገው ሊኖሩ አይችሉም።( 1 ዮሀ 3:6~9)  🔊ሐዋሪያው ጳውሎስ ስለዚህ ነገር ሲናገር ፥ ( ሮሜ ምዕ. 6) 1፤ እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ #በኃጢአት_ጸንተን እንኑርን? #አይደለም።2፤ ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? 👉 ስለዚህ የዘላለም ዋስትና 🚫የሀጥያት ፈቃድ ማለት አይደለም። የእግዚአብሔር ፍቅር በክርስቶስ ለሚያምኑ ለዘላለም እንደሚኖሩ የሚያረጋግጥ #ዋስትና #ነው። የእግዚአብሔርን ውድ የድነት ስጦታ ማወቅ እና መረዳት ለሀጥያት ፈቃድ ከመስጠት ጋር ምንም ግንኙነት #የለውም። ሮሜ ምዕ 6:14፤ ኃጢአት አይገዛችሁምና፤ ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደላችሁምና። 15፤ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን!! ✍ kb aman
Show all...
እስራታችሁን ፍቱና ልቀቁት! አንድን ስህተት ይዛችሁ የማትለቁትን ልማዳችሁን ዛሬውኑ ልቀቁት፡፡ የሰውንም ሆነ የራሳችሁን ስህተት አለመልቀቅ የእስራት ሁሉ እስራት ነው! ሰዎች አንድን ጥፋት ካጠፉ ወይም ስህተትን ከሰሩ፣ ለዚያ ስህተት ተገቢውን ምላሽ ከሰጣችሁ በኋላ ያንን ሁኔታ በመተው ወደፊት መሄድን ልመዱ፡፡ የአንድን ሰው ስህተትና ጥፋት እደየጋገሙ ማሰብም ሆነ ማውራት አደገኛ የሆነን ጠንቅ በሕይወታችን ያመጣል፡፡ ስህተቱ ሊነገረው የሚገባውን ሰው በጨዋነት ንገሩት፣ መታረም የሚገባውን ሰው በቅንነት አርሙት፣ ሊታገዝ የሚገባውን ሰው ባላችሁ አቅም አግዙት፣ በፍጹም መታረም የማይፈልገውንና ችግር ፈጣሪ የሆነን ሰው ደግሞ ራቅ በሉት፡፡ ይህንን ካደረጋችሁ በኋላ የአንድን ሰው ስህተት ማውጣትና ማውረድ ተወት አድርጉና ለትልቅነታችሁ ወደሚመጥነው ዓላማችሁ ዘወር በሉ፡፡ ራሳችሁም አንድ ስህተት ከሰራችም ሆነ ጥፋትን ካጠፋችሁ በኋላ፣ ለዚያ ስህተታችሁ ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ያንን ሁኔታ በመተው ወደፊት መሄድን ልመዱ፡፡ የራሳችሁን ስህተትና ጥፋት እየደጋገማችሁ ማሰላሰልም ሆነ በስህተቱ ምክንያት ራስን ሲወቅሱ መኖር አደገኛ የሆነ በሽታ ነው፡፡ በስህተታችሁ ምክንያት ያበላሻሁት ነገር ካለ አርሙ፣ የጎዳችትን ሰው ይቅርታ ጠይቁ፣ ያከሰራችሁትን ሰው ካለ እንደ አቅማችሁ ካሱ፣ ስህተታችሁን ደግሞ ላለመድገም ሞክሩ፡፡ ይህንን ካደረጋችሁ በኋላ የራሳችሁን ስህተት በማውጣትና በማውረድ ሲጸጸቱ መኖርን ተወት አድርጉና ለትልቅነታችሁ ወደሚመጥነው ዓላማችሁ ዘወር በሉ፡፡ ✍️ ኬቢ አማን
Show all...
"ችግርም በነፃ አይገኝም" ዋጋ ጨመረ ብለህ አትገረም፣ ገና ይጨምራል፡ካንተ የሚጠበቀው ከዋጋው በላይ መጨመር ነው! ቀኑ ይሮጣል ሰአቱ ይነጉዳል ብለህ አትደመም፣ ገና ይሸመጥጣል፤ ካንተ ሚጠበቀው ጊዜን ቀድሞ በእቅድ መወንጨፍ ነው! ሰው አያምነኝም፣ አይረዳኝም አትበል...ቁርጥህን እወቅ ራስህን በሚገባ እስክትረዳ ማንም አይረዳህም!!!! እኔ ለእኔ አንተም ላንተ የሆንን እለት ልዩ ይሆናል የእኛ ህብረት!!! ሳታማርር ቆም ብለህ አስብ እየገጠመህ ያለው ችግር ሳይሆን "ሊቀሰቅስህ የመጣ እድል ነው" ምን ፀልዬ ነው? ምን ተመኝቼ ነው? ምን ሊሰጠኝ ነው? ብለህ ቆም ብለህ አስታውስ እኔ ተቀብያለሁ እናንተስ? ✍ kb aman
Show all...
ምንም ነገር ሊከሰትብህ ይችላል ። ተፈጥሮ የረገመችህ ሊመስልህ ይችላል የማታስፈልግ ሊመስልህ ይችላል። የፈለገ ቢሆን ግን አንተ ያመንከውን ከማሳካት የሚያግድህ የለም ማንም ምንም አያስቆምህም አለምን ማስደመም ትችላለህ!!!! የተፈጥርከው በምክንያት ስለሆነ!!! ✍ ኬቢ አማን
Show all...
ደና አደራችሁ🤗🥰 1. ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!!!! 2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!!!! 3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!!!! 4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!!!! 5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!! 6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ!!! 7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ አይደለም ባለህ ነገርጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ስራ ውደድ ማለት እንጂ!!!! 9. ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ!!!! 10. ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም ምንም ቁም ነገር ስትሰራ አትሙት ማለት እንጂ!!!! 11. ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም ልብህን ግዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈ ለመስጠት ዝግጁ ሁን ማለት እንጂ!!!! 12. እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነትተናገር ማለት አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት ማለት እንጂ!!!! 13. አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትኑር ማለት አይደለም ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ!!!! 14. ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ!!! 15. ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሻልክህ ነህ ማለት አይደለም አምሮብሃል ማለት እንጂ!!!! 16. አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም ብልህ ሁን ማለት እንጂ!!! መልካም ቀን🌝😍🤗🎯 ✍ kb aman
Show all...
የ ስው ልጆች ወንኛ ጭንቀት በሕይወቴ ምን ልሥራበት የሚለው ነው። ምን ትፈልጋለህ? እጅህን ላይ አስቀምጥና ምንድነው የምፈልገው? ብለህ ራስህን ጠይቅ ቀድሞ ወደ አእምሮህ የሚመጣው ነገር ፍላጎትህ ነው። ሕልምህን እንዳታሳካ የሚያሰናክሉህ ስለራስህ የነበሩህ እምነቶች፣አመለካከቶችና ማጠቃለያዎች በመኾናቸው አስቀድመህ እነርሱን ለማስወገድ ሞክር። ራስህን ከማንም ጋር አታነጻጽር ምክንያቱም አንተ ጋ ያለው ክህሎት ከሌላ ከማንም ዘንድ አይገኝም። ✍ kebi aman @kamytat
Show all...
🐓🐓🐓ልጄ ሆይ ሙቀት ያስፈልጋቸዋል!🥚🥚🥚 ልጄ ሆይ👸 እንዴት ነሽ? ክረምቱ🌨 እንዴት ነው? ጓደኞችሽስ እንዴት ናቸው? ምን አዲስ ነገር አለ? ሁሌ እኮ ነው ስለአንቺ የማስበው፤ ሁሌም ደግሞ ደስተኛነትሽንና ስኬትሽን እናፍቃለሁ። ✍እንደምታውቂው ሁሉም የስኬት ከፍታ ደግሞ አንድ በአንድ የምትወጪው መሰላል🎢 ወይንም ደረጃ ይፈልጋል ተዘሎ አይደረስበትም። ዛሬ የማወራሽ ትልቁ የስኬትሽ መሰላል ደግሞ 🔥🔥🔥🔥🔥ሙቀት🔥🔥🔥🔥🔥 ይባላል። 👉ምን ማለቴ መሰለሽ? እስኪ አንድ ነገር ላስታውስሽ፦ ዶሮ🐓:- ልጅ(ጫጩትም ቢሆን) ወልዳ እንደማታውቅ አስበሽ ታውቂያለሽ? የምትወልደው(የምትጥለው) እኮ 🥚እንቁላል🥚 ነው። እናም ከእንቁላሉ ነው ጫጩት የሆኑ ልጆቿ የሚወጡት፤ ግን የሁሉም ዶሮ እንቁላል አይወለድም(አይፈለፈልም)። ከእንቁላልነት🥚ወደ ዶሮነት🐓 የሚቀየሩበት ሚስጥር አንድ ነው፥ ተገቢ የሆነውን ያህል ♨️ሙቀት♨️ ማግኘት! 🥚ሌላኛው አስገራሚው ነገር ጫጩቷ ነች በቂ ሙቀት ስታገኝ እንቁላሉን ከውስጥ ሰብራ በመውጣት ህይወት የሚገኘው፤ እናትየው🐓 ቸኩላ ከውጪ ከሰበረችው ግን ህይወት ይሞታል!⚠️ 🔍አየሽ? ልክ እንዲሁ አንቺም አሁን ላይ ገና እንቁላል የሆኑ ብዙ 🥚እቅድ፣ 🥚ትምህርት፣ 🥚ህልም፣ 🥚ራዕይ እና 🥚እድሜ አለሽ፤ በጣም ሃብታም ነሽ! ማወቅ ያለብሽ ግን የአንቺን የዓላማ እና የህልም እንቁላሎች ማንም ታቅፎ አያሞቅልሽም! ለእንቁላሎቹ መበላሸት ማንም ❓ተጠያቂ❓ አይሆንም ከአንቺ በስተቀር። ዶሮዋ እንቁላሎቿን ጥላ ዝም ብላ አትዞርም፤ ብትዞርስ? ሌላ ዶሮ እኮ አታቅፍላትም፤ ይገማሉ! ይበላሻሉ! ስለዚህ እባክሽ አንቺም ⚠️⚠️⚠️አትተያቸው!⚠️⚠️⚠️ በመዘናጋትሽ ደግሞ የሚበላሸው ውዱ እና ዋናው ነገርሽ እድሜሽ ነው። 🥚ሁሉም ነገርሽ የአንቺን ጊዜ⏰ እና ትዕግስት ይፈልጋል። 🥚እንቁላሎችሽ ከአንቺ በዋናነት የሚፈልጉት ጊዜ እንድትሰጪያቸው ነው። ብዙዎች ትዕግስት በማጣት ተገቢውን ሙቀት ለእንቁላሎቻቸው ሳይሰጡ እንቁላሎቻቸውን ሰብረዋል። ትምህርታቸውን አቋርጠዋል፣ ያለእድሚያቸው እጮኛ ያዙ፣ ሳያገቡም ወለዱ፣ ድንገት አገቡ... ህይወታቸው በአላማ ሳይሆን በድንገት ተሞላና የተበላሸ ሆነ! 💎ስለዚህ ልጄ ሆይ አንቺ ታጋሽ ሁኚ! ለአላማሽ እና ለእድሜሽ ታማኝ ሆነሽ ሙቀት ስጪያቸው! ለራስሽ ጊዜ ይኑርሽ! አትዙሪ! ልጄ ሆይ ሙቀት ያስፈልጋቸዋል! ሁሌም ❤️ከሚወድሽ❤️ Kebi aman
Show all...
⚠️⚠️⚠️ልጄ ሆይ ተመለስ!⚠️⚠️⚠️ ልጄ ሆይ🤴 የዛሬ ምክሬ በቶሎ ተመለስ የሚል ነው። 👉ለምን መሰለህ እንዲህ የምልህ? ለረዥም አመት ❌ከተሳሳትክ❌ ለመመለስ አመቶች ያልቁብሃል! 🌕🌖🌗🌘🌑 ይመሽብሃል! ዛሬ ግን ገና ወጣት ነህ 1 ብለህ ብትጀምር እንኳ ብዙ መቁጠር ትችላለህ። ደግሞ የምታውቃቸው ሰዎች የሉም? በወጣትነታቸው ተራ ነገር ላይ አተኩረው አሁን ሲነቁ ለመመለስ መሽቶባቸው በዚያው በጨለማ እየሄዱ ያሉ? አንተ ግን ለምን ይመሽብሃል? ለምንስ የተበላሸ የሰው ታሪክ ትደግማለህ? ለምንስ ጉልበትህን💪 ለከንቱ ነገር ትጨርሳለህ? አንተ እኮ ቢያንስ ቢያንስ ጥሩ ልጅ👪፥ ጥሩ ወንድም👬፥ ጥሩ ጓደኛ👫፥ ጥሩ ባል💏 እና ጥሩ አባት👨‍👧‍👦 መሆን ትችላለህ! 🎯ይሄንንም ግን ለመሆን ዛሬ የምትወስነው ውሳኔ አለ!⚖ ምክንያቱም የትኛውም አቅም እና ጥንካሬ በጊዜው⏰ ብቻ ነው የሚሰራው! አለዚያማ ያልፍብሃል! ሁሌ ወጣት፥ ሁሌ ጎበዝ፥ አይኮንም! 🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆 📌ትልቁ አቅምህ ያለው ሰውነትክ🏋‍♀ እና እድሜክ ላይ ሳይሆን የዛሬው ምርጫህ እና ውሳኔክ🎯 ውስጥ ነው! 🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆 እነዚህ ቁልፎች ወይ ወደክብር ትገባባቸዋለህ አለዚያም ደግሞ እንደህፃን ልጅ እራስህ ላይ ትቆልፍባቸዋልህ፦ 🔑ጓደኞችክ👋 እነማን ናቸው? 🔑ውሎክ የት ነው? 🔑ምንድን ነው የሚያስደስትህ? አእምሮህን🧠 አሰራው እንጂ፤ ተራ እና የማይጠቅሙ ነገሮችን እያሰብክ አእምሮህን አታበላሽ፥ ደሞ ማወቅ ያለብህ የህክምና ማዕከል ሆስፒታል እንኳን ብትሄድ ሃኪም (Doctor)👨‍⚕👩‍⚕ ጭንቃላትህን (Brain) እንጂ አእምሮህን(Mind) አያክምልህም፤ ጤነኛ ያደርግሃል እንጂ ጤነኛ አስተሳሰብን አይሰጥህም፤ ምክንያቱም አንተ ነህ ምን ማሰብ እንዳለብህ የምትመርጠው! ደግሜ ልንገርህ ምን ማሰብ እንዳለብህ አስብ! 🕺አሪፍ ማለት ሳይመሽበት ❌ ከማይሆን መንገድ 🏃‍♂የሚመለስ ማለት ነው!🕺 👇ዛሬ የግድ 👋 "ቻው"👋 የምትላቸው አስተሳሰቦች🙇‍♂ እና ሰዎች መኖር አለባቸው! አንተ ቻው ማለት ያለብህን ቻው የማለት አቅም ካጣህ ህልምህ እና ስኬትህ ያለጥርጥር ቻው ይሉሃል! 👋👋👋👋👋 👌ስለዚህ ዛሬ መንገድህን🛤🛣 ምረጥ እና አስተካከል🚧። መመለስ ካለብህ መንገድም🏃‍♂ ተመለስ! በመመለስህም ውስጥ አስተዋይነትህን ትገልጣለህ፤ አለዚያ ግን እድሜህ ቢጨምርም መቼም ትልቅ አትሆንም! ልጄ ሆይ👨‍👦 ምክሬን ስለሰማህና ስለምታደርገውም አመሰግንሃለሁ!🙏 የህይወትህንም ስኬት🏹 አብሬህ አያለሁና አምላኬን አመሰግናለሁ ✍ ኬቢ አማን
Show all...
እጅግ እፁብ ድንቅ የሆነውን ቀን ላሳየን አመስግናለሁ😍😍🎯💫💫💫 🎯🎯🎯🎯🎯🎯 🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂ “ትንሽ ሲቀር…” 🔹ጊዜው አሜሪካ ‘የወርቅ ትኩሳት’ ተብሎ በሚጠራው አባዜ የተለከፈችበት፤ ሁሉም ሰው ወርቅ ለመቆፈር ‘ወርቅ ይገኝበታል’ ወደተባለበት ቦታ ሁሉ የሚጎርፍበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ የንግዱ ባለሞያው የአቶ ዳርቢ አጎትም ጉዳዩን ሰምቶ ወደ አንድ ተራራ ያመራል፡፡ ብዙ ርዕይ ሰንቋል፡፡ ወርቁን አግኝቶ የሚኖረውን ሀብት እያሠበ በጉጉት እና በአዲስ ጉልበት ወደ ቦታው አመራ፡፡ በቦታውም ደረሰ፤ መቆፈር ጀመረ፡፡ ቆፈረ… ቆፈረ… ከሳምንታት በኋላ… አንዲት ብልጭ የምትል ነገር አየ፡፡ ዓይኑን ማመን አልቻለም፤ የተብለጨለጨው ነገር ወርቅ ኖሯል፡፡ በደስታ እጅጉን ፈነጠዘ፡፡ ይህንን ወርቅ ግን በትንሹ ለመውሰድ አልፈለገም፡፡ ይልቁንም በደንብ እና በስፋት አድርጎ ለመዛቅ እንጂ! ይህንን ለማድረግ ግን አካፋ እና ዶማ ብቻ በቂ አልነበረም… አዲስ እና በብዛት የሚቆፍር ማሽን አስፈለገው፡፡ ይህንን ለመግዛትም ወደ ሜሪላንድ ከተማ ተመለሰ፡፡ በከተማው ውስጥ ለነበሩትም ባለሀብቶች ያገኘውን ነገራቸው፡፡ እነርሱም ተደሰቱ፡፡ ገንዘባቸውንም አሰባስበው እና በብዛት የሚቆፍረውን ማሽን ገዝተው ላኩት፡፡ እርሱም ደግሞ አቶ ዳርቢን ይዞ ወደ ቦታው ተመልሶ መቆፈር ጀመረ፡፡ ቆፈሩ፡፡ ቆፈሩ፡፡ የመጀመሪያው ቁፋሩ ሙሉ ወርቅ ሆነ፡፡ እጅግ ተደሰቱ! በዚህ አካሄድ ምን ያህል ሀብታም እንደሚሆኑ እያሰቡ በደስታ ይሳሳቁ ጀመር፡፡ የተቆፈረው ወርቅ በአጠቃላይ ወደ አንድ ትልቅ ወርቅ አቅላጭ ዘንድ ተላከ፡፡ ከዚያም ደግመው ቁፋሮ ቀጠሉ፡፡ ቢቆፈር… ቢቆፈር… ቢቆፈር… አንዲት እፍኝ ስንኳ ሊገኝ አልቻለም! በዚህ እጅግ አዘኑ፡፡ ተስፋ ቆረጡ፡፡ ከአሁን በኋላ ወርቅ አናገኝም ብለው፤ ትልቁን መቆፈሪያ ማሽንም ለአንዱ ብረት ገዢ ሸጠውለት ወደ ቀያቸው ተመለሱ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን የመቆፈሪያ ማሽኑን የገዛው ሰውዬ፤ ወርቅ ቆፍረው አለማግኘታቸውን ሰምቶ ነበርና ወደ አንድ የማዕድን ተመራማሪ ዘንድ በመሄድ ሁኔታውን አጫወተው፡፡ በዚህ ጊዜ የማዕድን ተመራማሪው ፈገግ እያለ “አይይ… ያሳዝናል፡፡ እነዚህ ተስፋ ቆርጠው የሄዱት ሰዎች ምንም ስለ ማዕድን ቁፋሮ የሚያውቁት ነገር የለም ማለት ነው፡፡ ሦስት ክንድ ሲቀራቸው ተስፋ ቆርጠው ሄዱ!” ይለዋል፡፡ ይህንን የሰማው ብረት ገዢም እነ ዳርቢ ይቆፍሩበት ወደነበረው ቦታ ሄዶ እነርሱ የተዉትን መቆፈር ቀጠለ፡፡ ቆፈረ… ቆፈረ… ቆፈረ… በመጨረሻም በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላርን ያስገኘለትን ወርቅ እንደጉድ መዛቁን ቀጠለ! ይኸውልህ ወዳጄ በህልምህ መቼም ተስፋ አትቁረጥ የሞት መጀመሪያው ተስፋ መቁረጥ ነውና ስለዚህ በርታ ሽልማትህ ሦስት ክንድ ነው የቀረው ጀግነህ ቆፍር ሁሌም ስኬት የሚገኘው ከድካም በውኋላ ነው።
Show all...