cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

addicted to holy spirit

addicted to holy spirit

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
179Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ክርስቶስ የተወለደው የሚሞት፣ የሚደማ፣ የሚቦጨቅ ስጋ ለመልበስ ነው ውልደትን enjoy እንድናደርግ የሚያደርገን ሊሞት ስለሆነ ነው መወለድ አንድ ደስታ አለው ከሁሉም በላይ የሚያስደስተው ግን የተወለደበት ሰው የሆነበት ምክንያቱ እኛን ከእርሱ ጋር ለማኖር መሆኑ ነው በክርስቶስ ልደት ውስጥ የዘላለም ውልደት ስላየንበት ነው enjoy የምናደርገው መሲሁ ኢየሱስ ተወልዶአል
Show all...
እንዴት አላችሁ ዛሬ አንድ ስሰማው በጣም ያስደነቀኝን እና ያስገረመኝን ታሪክ ልንገራችሁ በአንድ አገር ውስጥ የሚኖሩ አንድ የተለመደ ስርዓት ያላቸው ህዝቦች ይኖሩ ነበር። በዚህ ስርዓት መሰረት አንድ ልጅ ወይም ወጣት ለአቅመ አዳም መድረሱን ለማረጋገጥ እና ከዚያም እንደ አዋቂ እንዲታይ አንድ ለሊት ብቻውን ጫካ ውስጥ እንዲያድር ይደረግ ነበር። ያቺን ለሊት ተቋቁሞ ማለፍ ከቻለ የትልቅነት ማዕረግን ይገኛል። እናም በዚህ ስርዓት ውስጥ ማለፍ የነበረበት አንድ ወጣት ተራው ይደርሳል ። እንደተለመዱው ዐይኑን ታስሮ በዚያ ጨለማ ወደ ጫካ አባቱ ይዞት ይሄዳል። እናም በአንድ ዛፍ ግንድ ስር እጁን እና እግሩን በገመድ ያስረው ጀመር። ገና ታስሮ ሳይጨርስ እንኳን የተለያየ የአውሬ ድምፅ ይሰማው ነበር። በጣም ፈራ ይንቀጠቀጥ ጀመር ከፍርሀቱ የተነሳ ሰውነቱ በላብ ተጠመቀ ነገር ግን ላሰበው ክብር ለመብቃት የግድ ያ ለሊት ሲነጋ ነው የታሰረው ዐይኑን እና እጁን መፍታት የሚችለው ። አንበሳ ሲያገሳ፣ ጅብ ሲጮህ እና እባብ በአጠገቡ እየተሳበ ሲያልፍ እየሰማ እንዲው እንደተሳቀቀ እያለቀሰ...... እይነጋ የለምና ነጋ። የፀሀይዋ ብርሃን በታሰረው ዐይኑ ላይ ሲያርፍ ትልቅ ደስታ እና ኩራት ተሰማው ወዲያውም እጁን ቀጥሎም ዐይኑ ላይ ያለውን ጨርቅ መፍታተ ጀመረ ። ዐይኑን ሲገልጥ ግን ያልጠበቀውን ነገር ነበር የተመለከቱው የሆነ ሰው ጦር ይዞ አጠገቡ ቆሞ ነበር.... ይህም ሰው አባቱ ነበር ።ለካ በራሱ አልነበረም የተረፈው፣ ለካ ሊበሉት የነበሩትን አውሬዎች አባቱ ነበር የከለከለለት፣ ለካ አባቱ ጥሎት አልሄደም ነበር፣ ለካ እርሱ ማየት ተስኖት እንጂ አባቱ አጠገቡ ነበር ። አባቱም እነሆ ልጄ አለሁልህ ብሎ አቀፈው😭። እህት ወንድሞቼ በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንዳላችሁ አላውቅም ግን አንድ ነገር ልበላችሁ ዛሬን ማየት የቻልነው እግዚአብሔር ስለጠበቀን ነው እንጂ በራሳችን አይደለም እናም አሁንም በጭንቅ ብቻዬን ነኝ ላላችሁ እርሱ የናንተን ጥንካሬ እንጂ ክፉ አይሻምና አሁንም አጠገባችሁ ነው። ስለ መልካም አባትነቱ እግዚአብሔር ይመስገን❤️። እዚህ ላይ አበቃሁ ተባረኩልኝ😍 @ addictedtoholyspirit
Show all...
ይፃፍልኝ amezing song😳😳❤️❤️❤️❤️❤️❤️😳❤️😳 ይቀዳ መልዕክቴ ለትዉልድ ይለፍ እንደምትረዳ እንደምታሳርፍ ይፃፍልኝ ቃሌ ይተረክ ለሌላዉ የሕይወት ቃል እንደሆንክ እንደምትበላ ይቀዳ መልዕክቴ ለትዉልድ ይለፍ አባት እንደምትሆን እንደምታሳርፍ ይፃፍልኝ ቃሌ ይተረክ ለሌላዉ የሕይወት ቃል እንደሆንክ እንደምትበላ እንዳይደለ ተረት ተረት እንዳየሁ በኔ ህይወት እንዳይደለ ሰሞንኛ እንደምትሆን ወዳጅ ቤተኛ እንዳይደለ ተረት ተረት እንዳየሁ በኔ ህይወት እንዳይደለ ሰሞንኛ እንደምትሆን የልብ ጓደኛ ከልጅነቴ ጀምሮ በማውቀው ኮልታፋ አንደበት በሚገባኝ በራሴ ቋንቋ መርቶኛል ያንተ እረኝነት ምክርህ ፍቅር አለበት ቁጣም ፍቅር አለበት ማን ተወቀሰ ባንተ አድጎ?ጥጉነህ ያባትነት ማንተሰደበ ባንተ አድጎ? ጥጉነህ ያባትነት እንዳይደለ ተረት ተረት እንዳየሁ በኔ ህይወት እንዳይደለ ሰሞንኛ እንደምትሆን ወዳጅ ቤተኛ እስከዛሬ በተጓስኩት በመጣሁት ሁሉ መንገድ ከምዳስሰው ሰው ሁሉ ይልቅ ህያውነህ አንተ በኔ ዘንድ እስከዛሬ በተጓስኩት በመጣሁት ሁሉ መንገድ ከምጨብጠው ሰው ይልቅው እርግጥ ነህ አንተ በኔ ዘንድ ለማለት ያህል አልልም ስላየውነው በዘመኔ ለማበረታታት ለማጀገን ማን ሊቆም እንዳንተ ለኔ? HELINA DAWIT NEW SONG ይፃፍልኝ amezing song😳😳❤️❤️❤️❤️❤️❤️😳❤️😳 @yegetahayalan
Show all...
❤ጉዳዩ መኖሪያህን ማወቁ ነው።❤ “ሽኮኮዎች ያልበረቱ ሕዝቦች ናቸው፥ ቤታቸውን ግን በቋጥኝ ድንጋይ ውስጥ ያደርጋሉ።” — ምሳሌ 30፥26 “እንሽላሊት በእጅ ይያዛል፥ በነገሥታት ግቢ ግን ይኖራል።” — ምሳሌ 30፥28 👉እዚህ ክፍል ላይ በጣም የሚገርሙኝ እነዚህ ጥቃቅን እስሶች ናቸው። 👉ሽኮኮ የሚኖሩት በህብረት ነው/ህዝብ/ ሆነው ማለት ነው፤ ነገር ግን ያልበረቱ ህዝቦች ናቸው። እነዚህ እንስሶች ጠቢብ ያደረጋቸው ነገር መኖሪያቸውን መምረጣቸው ነው። የሚኖሩት #በቋጥኝ ድንጋይ# ውስጥ ነው። 👌ወዳጄ አስተውል ብርቱ አለመሆንህ አያሳስብህ፤ ብርቱ አለመሆንህን አውቀህ መኖሪያህን #በቋጥኝ ድንጋይ# ውስጥ አድርግ። የኔ እና ያንተ የቋጥኝ ድንጋይ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሽኮኮዋ ከቋጥኝ ድንጋዩ የተነሳ አትፈራም፣ አትሰጋም፤ መተማመኛዋም ድንጋዩ ነው። እኔና አንተ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ስለሆንን ከምንሰማው ከምናየው ነገር ተነስተን አንናወጥም፣ አንፈራም፣ አንሰጋም። አሜን!!! 🐊እንሽላሊት ራሷን የምትከላከልበት አቅም የላትም፤ በቀላሉ በእጅ የምትያዝ ናት። ነገር ግን ጠቢብ ናት ምክንያቱም አቅሟን አውቃ መኖሪያዋን #በነገስታት ግቢ# ውስጥ አረገች። ወዳጄ እንሽላሊቷ ምንም ያለመሆኗ ምስጥር ከራሷ ብቃት አይደለም ከመኖሪያዋ አንጂ። 👉ወዳጄ በአለም ላይ ምንም አይነት ነገር ሊፈጠር ይችላል የማንፈራው፣ የማንሰጋው ሰው ስላልሆንን አይደለም መኖሪያችንን መምረጣችን ነው። መኖሪያችን #የዘላለም አምላክ እግዚአብሔር# ነው። 👌ወንድሞቼ አንድ ነገር ላሳስባችሁ ከሁለቱ ጠቢብ ጥቃቅን እንስሶች አንድ ነገር ተማሩ በመረጣችሁት መሮሪያ መታመን ይሁንላቹ። መኖሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። አሜን። @addictedtoholyspirit
Show all...
✍ ወዳጄ ሆይ በምን ሰከርክ? ************************ 📌 አብዝተህ የጠጣኸው ነገር ያሰክርሀል.....ትንገዳገዳለህ.......ከቁጥጥርህ ውጭ ሆነህ ያሰከረህ ይቆጣጠርሀል!! ✍ የምትሰክርለት አብዝተህ ለጠጣኸው ጉዳይ ነው!! 📌 ቀንህን የምታሳልፈው ምን እየጠጣህ ነው? ✍ ያልጠጣኸውን መስከር የጠጣኸውን አለመስከር አትችልም!! 📌 አብዝቶ ፖለቲካ የጠጣ ሰው ሰክሮ የሚንገዳገደው ለፖለቲካ ነው!! ✍ አብዝቶ ኳስ የጠጣ ሰው ሰክሮ የሚንገዳገደው ለኳስ ነው!! 📌 አብዝቶ ጥላቻ የተጋተ ሰው ሰክሮ የሚንገዳገደው ለጥላቻ ነው!! ✍ አብዝቶ ክርስቶስን የጠጣ ሰው ሰክሮ የሚንገዳገደው ለክርስቶስ ነው!! 📌 ወዳጄ አብዝተህ የምትጠጣው ምንድን ነው? ✍ ስትሰክር የምትተፋው የጠጣኸውን ነው........በፖለቲካ ሰክረህ ያገኘኸው ሰው ሁሉ ላይ ፖለቲካ እንጂ ኢየሱስ ካፍህ አይወጣም.........በክርስቶስ ስትሰክር ያገኘኸው ሰው ሁሉ ላይ ክርስቶስ እንጂ ጥላቻ ካፍህ አይወጣም!! 📌 የሰከርከው በምንድን ነው? ✍ በክርስቶስ ስትሰክር ስካር ራሱ ያምርብሀል? መንፈስ ሞልቶብህ የምትሰክረው ስካር ለሕይወት የሆነ ትርፋማ ስካር ነው!! ✍ የሰከርከው በክርስቶስ ካልሆነ ሰክረሀል ሳይሆን ከስረሀል ነው የሚባለው!! 📌 እናልህ ወዳጄ ሰክረሀል ወይስ ከስረሀል? @addictedtoholyspirit
Show all...
bezeh mezmure resersu😍❤️💙 tebarkulg wedachewalwe🙏🙏😢😢 @addictedtoholyspirit
Show all...
“በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።” — 2ኛ ቆሮ 6፥2 https://t.me/heyawyeegezeyabehermenegest
Show all...
✍የማያምን አማኝ ***************** የችግሩን ባህር እንደቀልድ ከፍለኸው ፊልም በሚመስል ተራምዶ እያለፈው ተርቢያለሁ ቢልህ መና ብትመግበው ተጠማሁኝ ቢልህ ከአለት ብታጠጣው እግሩ እየረዘመ ጫማዎች ባያጥሩት ሰውነቱ ሲገዝፍ ልብሶቹ ባይጠቡት ጠላቶቹን ሁሉ ብታሸንፍለት ፅልመቱን አንስተህ ጎህ ብትቀድለት "የማያምን አማኝ" እንቅፋት እያየ በልቡ ያምፃል ለተድላ ቢታጭም ባርነት ይመኛል። Share &join👇 @eyobapoem #ኢዮብ ጥላሁን።
Show all...