cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሐመረ ኖህ በገና ክረር መስንቆ መገኛ💒

በገና ክራር መሰንቆ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገኙበት አዳዲስ እና ቆየት ያሉ የበገና መዝሙሮችን የሚገኙበት channel ነው

Show more
Advertising posts
21 214Subscribers
-1824 hours
-697 days
-43130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

​​ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ክቡር ሌሊቱን በብርሃን የሚማር መምህር(፪) በጨለማው ግርማ ኮከብ የደመቀ በመከራው ፅናት ይህን ዓለም ናቀ መምሕር ሆኖ ሳለ ከመማር ያልራቀ የትዕቢትን ጅረት በትሕትና ተዋርዶ አደረቀ         ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ         አኮኑ አጽባዕት እምነ አጽባዕት የአቢ         ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ ፍርሃትን በሚጥል ፍፁም ፍቅር ያደረ ከመስቀል አውርዶ ጌታውን ቀበረ የመግነዙን በፍታ በሽቱ ያከበረ ከመቅደሱ አንቀጽ ላይረሳ አምድ ሆኖ ታጠረ         ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ         አኮኑ አጽባዕት እምነ አጽባዕት የአቢ         ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ነገረች ህጉን ለሚያስበው ምክር አለኝ እያለች ከጨለማው ኃጢአት ነቅታ ብርሃን ካየች እንደ ኒቆዲሞስ ነፍስህም ተምራ ተመለሰች         ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ         አኮኑ አጽባዕት እምነ አጽባዕት የአቢ         ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ         በሌሊት አጋማሽ መምህር ለመምህር ሰገደ ፤         ጣትስ ከጣት ይልቅ አይደለምን?                    መዝሙር        ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ @hameranohh💚 @hameranohh💛 @hameranohh❤️
Show all...

Hiwot በገና ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ 🔵በገና ክራር እና መሰንቆ በሚያምር ዲዛይን እና በተመጣጣኝ ዋጋ ተሰርተው  ይደርሶታል። 🔵ከእርሶ እሚጠበቀው  ማዘዝ ብቻ ነው።በሚፈልጉት ቅርጽ አይነት እና ብዛት እንደ ፍላጎቶ በጥራት እንሰራለን። 👉ለማከፋፈል ብዛት ለሚገዙ ታላቅ ቅናሽ እናደርጋለን። ውጭ ሀገር ለምትኖሩ ወገኖቻችንም እንልካን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ዉጭ ላላቸው በ 24ሰዓት ውስጥ እናደርሳለን። በገና 5000 10000 እና 12000 ክራር 3500እና 4000 መሰንቆ 2500እና3500              በጥራት አንደራደርም!!!!! ✍️+251934841025 ይደውሉ @hameranohh💚 @hameranohh💛 @hameranohh❤️
Show all...
👍 7
Hiwot በገና ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ 🔵በገና ክራር እና መሰንቆ በሚያምር ዲዛይን እና በተመጣጣኝ ዋጋ ተሰርተው  ይደርሶታል። 🔵ከእርሶ እሚጠበቀው  ማዘዝ ብቻ ነው።በሚፈልጉት ቅርጽ አይነት እና ብዛት እንደ ፍላጎቶ በጥራት እንሰራለን። 👉ለማከፋፈል ብዛት ለሚገዙ ታላቅ ቅናሽ እናደርጋለን። ውጭ ሀገር ለምትኖሩ ወገኖቻችንም እንልካን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ዉጭ ላላቸው በ 24ሰዓት ውስጥ እናደርሳለን። በገና 5000 10000 እና 12000 ክራር 3500እና 4000 መሰንቆ 2500እና3500              በጥራት አንደራደርም!!!!! ✍️+251934841025 ይደውሉ @hameranohh💚 @hameranohh💛 @hameranohh❤️
Show all...
👍 6 2
☘️ሰላም ለልደትከ✨ ኦ አማኑኤል፤ ዘቀዳሚ ወዘደኃሪ ✨ብሉየ መዋዕል፤ ኢየሱስ ክርስቶስ✨ ዘአብ ቃል፤ እፎ እፎ✨ አግመረተከ ድንግል፤ ወእፎ እንዘ አምላክ ✨ሰከብከ በጎል።         እንኳን 🍁ለአምላከ አማልክት✨ ወእግዚአ አጋእዝት✨ ወንጉሠ ነገሥት ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወወልደ ማርያም ሥግው ✨ኢየሱስ ክርስቶስ✨ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ✨ ከሁለት አካል አንድ አካል✨ከሁለት ባሕርይ ✨አንድ ባሕርይ✨አድርጎ ያለመከፈል ያለመለወጥ ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን✨✨ ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም✨ ነፍስን ነስቶ ያለ ዘርዓ ብእሲ✨ በፍጹም ተዋሕዶ✨ በዓለም ✨ለዓለም✨ ለታየባት✨ለቅድስት ልደቱ✨ በሰላም አደረሳችሁ።🌱መልካም በዓል H𝑖𝑤𝑜𝑡 G𝑒𝑧𝑎ℎ𝑒𝑔𝑛
Show all...
🙏 12👍 3 2
ኦ! ለዝንቱ መንክር ልዑል ላዕለ ኩሉ ሕሊናት:: ✝️ 🍀ብእሲት ምድራዊት ወለደቶ ለእግዚአብሔር ቃል ዘኮነ ሰብአ:: ✝️🌱 ድንግል ወለደቶ ለገባሪሃ:: ወለሊሁ ፈጠረ ወላዲቶ . . . ከሕሊናት ሁሉ ለራቀ ለዚህ ድንቅ ምሥጢር አንክሮ ይገባል! ✝️🌿ምድራዊት ሴት ሰው የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ወለደችው:: ✝️🍀 ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው:: ✝️☘️ እርሱም እናቱን ፈጠረ:: ከእርሷም እርሱ የፈጠረውን ሥጋ ተዋሐደ:: 🌿 ተዋርዶ በእኛ ባሕርይ ተወለደ:: እርሱም እኛን ስለ መውደዱ ፈጠረን:: (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤፍ ሶርያዊ ቁ. 2) ኦ ማርያም! በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዓብየኪ። እስመ ወለድኪ ለነ መብልዐ ጽድቅ ዘበአማን። ወስቴ ሕይወት ዘበአማን። "ማርያም (እመቤታችን) ሆይ! ስለዚህ ነገር እንወድሻለን። ከፍ ከፍ እናደርግሻለን። የጽድቅ መብልን የሕይወት መጠጥን ወልደሽልናልና።" (አባ ሕርያቆስ ዘብሕንሳ) ከበረከተ ልደቱ ይክፈለን) 👉 @hameranohh
Show all...
👍 4
​​እንኳን #አቡነ_ገብረመንፈስ_ቅዱስ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን! አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሀገራቸው ንሂሳ (ግብጽ ) ነው። አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌያስ ይባላሉ። ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል። አንድ ቀን አቅለያስ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከስዕለ ስላሴ ስር ወድቃ ስትማጸን "" ንስኢ ወልደ ዘይትሌአል ቅርኑ አምኑኅ ሰማይ ... ክብሩ ከሰማይ ከፍታ የሚበልጥ ልጅ እንኪ ተቀበዪ " የሚል ድምጽ ሰማች። በዚህም መሰረት አባታችን መጋቢት 29 ቀን ተጸንሰው ታህሳስ 29 ቀን ተወለዱ። አይን በገለጹ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ብለው ተነስተው "" ስብሐት ለአብ , ስብሐት ለወልድ , ስብሐት ለመንፈስቅዱስ ዘአውጻእከኒ እምጽልመት ውስተ ብርሐን >> ብለው በማመስገናቸውና ሀላም ምድራዊ መብል እና መጠጥ ሳይመገቡ : ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው በመኖራቸው መልአክትን ይመስላሉ ሶስት አመት ሲሆናቸው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእመቤታችንና በገነት ካሉ ቅዱሳን ዘንድ አስባርኮ ገዳማውያን ካሉበት ምኔት ወስዶ ከበሩ አኖራቸው :: አበመኔቱም አባ ዘመድብርሐን ምልክት ተነግሮት ቢሄድ ፍሱሐ ገጽ ሆነ አግኝተዋቸዋል። አበመኔቱም አሳድጎ አስተምሮ ከመአረገ ምንኩስና አድርሰዋቸዋል። ከዚህ ቡሐላ ሐብተ ፈውስ ተሰጥቷቸውል። በአንድ ቀን እልፍ እውራንን እና እልፍ አንካሳ ፈውሰዋል። በዋላ ግን ኤጲስ ቆጶሳትና ካህናቱ ዝናቸውን ሰምተው እየመጡ ግብር የሚያስፈቱአቸው ቢሆን ቅዱስ ገብርኤል ነጥቆ ከጌታ ፊት አቀረባቸው። በገድለህ : በትሩፋትህ : ከሞት ነፍስ ክርደት ገሀነም የሚድኑ ብዙ አሉና ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ ግባ። ኑሮህም ከስልሳ አናብስትና ከስልሳ አናብርት ጋር ይሁን አለው። ጌታዬ ምን ተመግበው ይኖራሉ አሉት ? "ዘኬድከ ጸበለ - እግረከ ይልህሱ ወበ ውእቱ ይጽግቡ ... የረገጥከውን ትቢያ ልሰው ያ ምግብ ሆኗቸው ይኖራሉ። ብሏቸው ውሳጤ ገዳም ገብተው : ከአናብስትና ከአናብርት ጋር ይኖሩ ጀመሩ። ዳንኤል ከአናብስት ጉድጉዋድ በተጣለ ጊዜ አናብስቱ እንደ ድመት ከእግሩ በታች ሆነው እንደተገኙ : አባታችን የረገጡትን ትቢያ እየላሱ እየታዘዙዋቸው ይኖሩ ነበር። በዚህ መልኩ 30 አመት ከቆዩ ቡሐላ ጌታ በአንድነት በሶስትነት ተገልጾ ምን ላደርግልህ ትሻለህ ? አላቸው። መጀመሪያ ላሉበት መጸለይ ይገባልና የምድር ገቦታን ሰዎች ማርልኝ አሉት። 3000 ሐጥአንን ከሲኦል አውጥቶ ገነት አግብቶላቸዋል። ከዚህ ቡሐላ ሁር ምድረ ኢትዮጵያ ወበህኒ አልውከ ነፍሳት ወታወጽኦሙ .... ወደ ኢትዮጵያ ሂድ አላቸው። ቅዱስ ገብርኤል በሰረገላ ነፍስ ጭኖ ምድረ ከብድ አድርሷቸዋል። ዳግመኛም ወደ ዝቁዋላ (ደብረቅዱስ ) ወስዷቸው ከዚያ ሆነው በንጹሀ ልቦና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሐጢያት ከባህሩ ውስጥ ራሳቸውን ዘቅዝቀው ለ 100 አመት ይጽልዩ ነበር። 40 ቀን ሲሆናቸው መልአኩ መጥቶ ዘገብረ ተዝካርከ ወዘጽውአ ስምከ እምህር ለከ ብሎሀል አላቸው። እሳቸው ግን መላ ኢትዮጵያን ካልማረልኝ ከባህሩ አልወጣም ብለው 100 አመት በባህሩ ውስጥ በጭንቅላታቸው ተዘቅዝቀው ሲጸልዩ ኖረዋል። ከ 100 አመት ቡሐላ ጌታ ተንስእ ወጽእ መሀርኩ ለከ ኩሎ ኢትዮጵያ ... ምሬልሀለው ውጣ ብሏቸው ወጥተዋል። ከዚህ ቡሐላ ምድረ ከብድ ወርደው ከምድር በላይ ከሰማይ በታች ሆነው 7አመት እንደ ትኩል አምድ ሆነው አይናቸውን ሳይከድኑ 7 አመት ሙሉ አይናቸውን ሳይከድኑ ቆመው ጸልየዋል። ሰይጣን ግን ለምቀኝነት አያርፍምና ቁራ መስሎ መጥቶ አይናቸውን አንቁሮ አሳወራቸው። 2 ሱባኤ ሲፈጽሙ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል መጥተው እፍፍ ብለው አድነዋቸዋል። ከዚያ ተነስተው ወደ ዝቁዋላ ሲሄዱ ስላሴን በአምሳሌ አረጋውያን ከጥላው ስር አርፈው አገኙዋቸው። በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጽነንሀል አዝለክ አንድ አንድ ምህራፍ ሸኘን አሉዋቸው። አዝለው ከሸኙዋቸው ቡሐላ በአንድነት በሶስትነት ሆኖ ታያቸው። ድንግጠው ወደቁ : እግዚአብሔር ግን አንስቷቸው ሂድ ዝቁዋላ ሄደህ ጠላቶችህን ተበቀላቸው አላቸው :: በዛበነ መብረቅ ደርሰው 7 ቱን ሊቃነ መላእክት አጋዥ አድርገው እልፍ አእላፍ አጋንንትን አጭደዋል። ጻድቁ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍታቸው መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ ስለዚህም ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር የመጋቢት 27 ስቅለት ደግሞ ጥቅምት 27 ቀን እንዲከበር ተደረገ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ይህ ስርዓት ሆነ። #ምንጭ - ገድለ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ተአምር 14  @hameranohh
Show all...
👍 8
Hiwot በገና ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ 🔵በገና ክራር እና መሰንቆ በሚያምር ዲዛይን እና በተመጣጣኝ ዋጋ ተሰርተው  ይደርሶታል። 🔵ከእርሶ እሚጠበቀው  ማዘዝ ብቻ ነው።በሚፈልጉት ቅርጽ አይነት እና ብዛት እንደ ፍላጎቶ በጥራት እንሰራለን። 👉ለማከፋፈል ብዛት ለሚገዙ ታላቅ ቅናሽ እናደርጋለን። ውጭ ሀገር ለምትኖሩ ወገኖቻችንም እንልካን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ዉጭ ላላቸው በ 24ሰዓት ውስጥ እናደርሳለን። በገና 5000 10000 እና 12000 ክራር 3500እና 4000 መሰንቆ 2500እና3500              በጥራት አንደራደርም!!!!! ✍️+251934841025 ይደውሉ @hameranohh💚 @hameranohh💛 @hameranohh❤️
Show all...