cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

መፅሐፍቶችን በpdf

"እንኳን ደህና መጣችሁ"Welcome! በpdf(በሶፍት ኮፒ) ለማንበብ ራሳችንን እናስለምድ! ፨ተራ ነገር በመስራት የሚባክነውን ጊዜያችንን በንባብ ላይ ስናውለው ከራሳችን አልፈን ለብዙዎች የመለወጥ ምክንያት እንሆናለን፡የንባብ ባህላችንን እናዳብር! ባለንበት ራሳችንን በእውቀት እንገንባ! ፨በዚህ ቻናል የተለያዩ መፅሐፎች፣ጠቃሚ ሀሳቦች፣አፕልኬሽኖች፣አነቃቂ ምስሎች ቀርቦላችኋል አውርደው ይጠቀሙ።

Show more
Advertising posts
2 355Subscribers
+1124 hours
+507 days
+34430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ናፍቆት የሚለው መጽሀፌ ቶፕ 5 መግባቱን ሰማሁ አዲስ አበባ ያላችሁ ወዳጆቼ በዚህ ሊንክ ገብታችሁ የወደዳችሁትን ምረጡ https://kibershilemat.com/
Show all...
Wishing #You Inner Strength ,When Nothing Goes Right and Things work Against you , No one Bothers to Uplift you and Help comes from no way , It's the Time to Reignite your own Energies and Strike with more Force but Silently . No can Face your Battles so Win Your Battles Valiantly , Stay Winning #winning#You#love#inner strength#work#God#Battles of Life #your strength #Time#
Show all...
ልጅነት/በዘነበ ወላ፥ እጅግ በጣም ምርጥ መፅሐፍ ነው፣ ልጅነትን ያስታውሳል፣ የልጅነት ትዝታን ይቀሰቅሳል፣ ልጅነት ማለት የዋኅነት፣ ቅንነት፣ መልካምነት እንደሆነም ያስተምራል የዘነበ ወላ መፅሐፍ፣ ልጅነት። ዘነበ በተፈጥሮው ነጮች humble ብለው በሚመድቧቸው ሰዎች ተርታ የሚመደብ ነው፣ ክፋትን አልፈጠረበትም፣ ሁሉን አክባሪ ነው፣ ለስራና፣ ለመፃፍ ብሎም ለማሳወቅ የተፈጠረ ሠው ነው። ልጅነት መፅሐፉ በምናባችን ወደ ልጅነት እንድንሄድ የሚጋብዝ ነው። የማያነሳው ትዝታ የለም፣ የቄስ ትምሕርት ቤት መምህር፣ ተማሩ የሚል ትዕዛዝ የሚሰጥ፣ ብሎም ጭልጥ ብሎ በሃሳብ የሚኮበልል፣ የሠው ልጅ ሃሳብን ለማስተናገድ የተፈጠረ ይሆን ያሰኛል። ዘነበ የሠውን ስነ ልቦና ያውቃል ቢባል አጥርቶ የሚያውቀው የጋሽ ስብሀትን ስነ ልቦና ነው። ማስታወሻ መፅሐፉን ሲፅፍ ከስብሐት ጋር ሃሳቡ እስከተሳካለት ድረስ ኖሯል ለማለት ይቻላል፣ ጋሽ ስብሃት የሚወደውን ነገር በደንብ ያውቃል፣ ያቀርብለታል፣ ትልቁ ስብሃት የሚወደው መጠጥ የሃገር ቤቱን ለብ የሚያረግና እንደ ምርቃና ሆኖ የሚያነሳሳ የሃገር ተወላጁን የአበሻ አረቂ ነው። ዘነበ የስብሐትን ማስታወሻ ከ እስክ ለመፃፍ ባማረው ግዜ ይህን ለስብሐት ያቀርብለታል፣ ከዚያ አእምሮው በውቀት የታጨቀው ስብሐት ፈሰስ ያደርግለታል፣ ማስታወሻ ስብሐትን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ረዥም ባዮግራፊ ነው፣ በዚህም ዘነበ ታላቅ ዕውቅናን አግኝቷል። ልጅነቴ ልጅነቴ ማርና ወተቴ እባካችሁ ልጆች እንጫወት በጣም ክእንግዲህ ልጅነት ተመልሶ አይመጣም ይላሉ ልጆች ስለ ልጅነት በወቅቱ መጣፈጥ፣ ካለፈም አለመገኘት ሲዘክሩ። አወን ዘነበ በሚጣፍጡ ቃላት፣ አግራሞትን በሚጭሩና አንባቢን በሚስቡ ሁሉ ነገሮች አስውቦ ፅፏል ምስጋና ይቸረውና። እንግዲህ አንብባችሁ ፍረዱ። ዘነበ እንወድሃለን። መልካሙ ሠው ብዕርህ አይንጠፍብን።
Show all...
የማይቀርበተ ታላቅ ታሪካዊ ዐውደ ርእይ "ንጹህ ምንጭ ኢትዮጵያ" በሚል ርእስ የተዘጋጀውና በበርካታ ሰዎች በልዩ አድናቆት እየተጎበኘ የሚገኘው የጥንታዊ የብራና ዝግጅትና ጽሑፍ በአካል የሚያዩበት፤ ጥንታውያን ሥዕላት ከእነ አሳሳላቸው የሚመለከቱበት፤ የጥበባተ እድ ሥራዎች እርሶም የሚሳተፉበት ፤ምን አለፋዎ የኢትዮጵያን ንጹህ ምንጭነት በትክክል የሚቀምሱበት ኹነት ነው። በመምጣቶ እጅግ የሚደነቁበት አበርክተው የሚያተርፉበት ቢቀሩ በእጅጉ የሚጎድልብዎ ዐውደ ርእይ እና ኪናዊ ኹነት ነው። #አዘጋጅ-ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት ።#ቦታ-በግዮን ሆቴል #ቀናት -ከሚያዚያ 4/2016 - ሚያዝያ 13/2016 ዓ.ም. #የመግቢያ ዋጋ-ለአዋቂ 200 ብር -የልጆች መግቢያ 50 ብር ❤ማስታወሻ 1---በተለይ ሚያዚያ 12 እና 13 ምሽት 11ሰአት ጀምሮ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የኪነጥበብ ምሽት ከዐውደ ርእዩ ጋር በጥምረት ይቀርባል። ❤ማስታወሻ 2---በተለየ መንገድ ቅዳሜ ሚያዚያ 12/2016ዓ.ም. የልጆች ልዩ የመዝናኛ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች ከ7 ሰአት ጀምሮ እስከ 10 ሰአት ይካሄዳል። በዕለቱ የሚገኙ የክብር እንግዶች ዲስኩር ግጥምና የተለያዩ ኪናዊ ሥራዎች ለማቅረብ መጋቤሐዲስ እሸቱ አለማየሁ መ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ ዲያቆን ቴዎድሮስ በለጠ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ሠርጸ ፍሬስብሐት አርቲስት አለማየሁ ታደሰ አርቲስት ይገረም ደጀኔ አርቲስት ንብረት ገላው አርቲስት ናርዶስ አዳነ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም ገጣሚ አስታውሰኸኝ ረጋሳ ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን … በሥፍራው ይገኛሉ በእነዚህ መርሐ ግብሮች ላይ እንዲገኙ ለሌሎችም እንዲያጋሩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዛችኋለን። ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት!!!
Show all...
📘 መጠየቅና ማወቅ:ምክንያታዊነትን ማስቀደም:ጠይቆ መልስ መፈለግ:ማነጻጸር:ማወዳደር እንዲሁም የማያውቋቸውን ጉዳዮች ለሌላ አጥኝ መተው የድርሰቶቹ መለያ ናቸው። 👉 ቅንጭብ 👇👇 "ድራጎን በኢትዮጵያ ሰማይ" 👇👇 📘 ከንግግሩ ፋታ ሲወስድ መሪጌታ አይነኩሉ አባ ተውቦ ሰናይን በትክሻቸው ጉስም አደረጉና‹‹ ኧረ የኔታ ይህን ልጅ ምንድን ነው ያቀመሱት፤ኧረ የወላዲት አምላክ ያለህ…..ምን አይነት እውቀት ነው?” አሉ፡፡ 📘 አባ ተውቦ ሰናይም ፈገግ ብለው‹‹ ምን ነው ቀኑ እንዴት? ብዙ ነገር እያወቁ ለምን እንዲህ ይሉኛል፡፡ እንዴት ነው ነገሩ ይተው እንጅ! ጥበብ ከሰው ልጅ ብቻ የምትገኝ አስመሰሏትሳ…..”አሉ ፈራ ተባ እያሉ፡፡ 📘 መሪጌታ አይነኩሉም‹‹ አዛኝቱን፤ገና በአስራ አምስት አመቱ እንደዚህ ያለ ሊቅ ሊገኝ አይችልም፡፡ ይልቅ እውነታውን ቢነግሩኝና ቀጣይም የሚመጡ ሀገር ተረካቢ ሳይንቲስት ህጻናት አሉ፡፡ የተነገሩትን የማይረሱ፤የያዙትን የማይጥሉ፤የጣሉትን የማያነሱ፤የሚጥሉትን የሚይመርጡ….እንዲሆኑ እናድርጋቸው፡፡ ደግሞም ከዚህ በጥቁር አስማት ከሚደዘደዘው ዘያገድፍና አብሾ የተለየ እውነተኛ ጥበብ እንዳለ ለሁላችንም ግልጽ ነው፡፡ እርስዎ ለምን ምስጢር ማድረግ ፈለጉ?››አሏቸውና ወደ መክብብ አፍጥጠው እየተመለከቱ፡፡ 📘 ‹‹ አይ አባታችን ነው ብለው ነው ሃሃሃሃ…” በማለት ለማዘናጋት ሞከሩ፡፡ መሪጌታ አይነኩሉ ግን በቀላሉ ሊተዋቸው አልቻሉም፡፡‹‹ አዛኝቱን፤ይህ ልጅ ሲፀነስ እርስዎ የት ነበሩ? ከዚህ ልጅ ቤተሰቦች ጋርስ ያለዎት ግንኙነት ምን ነበር? እርግጠኛ ነኝ እንደዚህ አይነት ጭምት አዋቂ የሆነው በማህጸን ውስጥ ሳለ ለእናቲቱ የተሰጣት የጥበብ ነገር ይሆን?” በማለት ጥያቄቸውን የበለጠ አከረሩት፡፡ 📘 ‹‹ አባቴ ለምን አይተውኝም፡፡ ጥበብ በዚያ በማስተዋል በኩል አለ፡፡ ጥበብ በዚያ በሄኖክ በኩል ነበረ፡፡ ያ ጥበብም፡ በማስተዋልና በማመን ነበረ፡፡ ከማስተዋልና ከማመን በተጨማሪ የሰው ልጅ አእምሮውን ሙሉ በሙሉ ለመልካም ነገር አውለዋለሁ ብሎ ካሰበ ማድረግ ይችላል፡፡ የመክብብ ታሪክ ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን አባቴ ልክ የሄኖክ አእምሮ ካለ ድዝዳዝና ኮተት ድግምት የመብቃት ሃይል እንደተገኘ ሁሉ በዚህ ወጣት ላይም የማስተውለው የማስተዋልን ጥበብ ነው፡፡ ምንጭ፡- ድራጎን በኢትዮጵያ ሰማይ ገጽ 122 ✍️ በዝጋለ አያሌው
Show all...
ኢጎ የዘመናችን የሰዎች ማንነት ኢጎ ማለት ከሀሳባዊ ፣ አካላዊ እና ስሜታዊ ቅርፆች ጋር የሚደረግ ቁርኝት ነው። በዘወትር አጠቃቀማችን "እኔ" ቀዳሚ ስህተትን ፣ ስለ ራስ የተሳሳተ አረዳድንና ሐሳዊ ማንነትን ያነገበ ነው። ይሄ ታዲያ ኢጎ ይባላል። ኢጎ ሁልጊዜ ከቅርፅ ጋር ቁርኝት ሲሆን ፣ እራስን በሆነ ቅርፅ መፈለግ ፣ ፈልጎም ማጣት ነው። ብዙዎች አሁን ድረስ ከማያቋርጥ ፣ ተደጋጋሚና እርባና ቢስ የሀሳብ ጅረት ጋር ሙሉ በሙሉ የተቆራኙ ናቸው። ከሀሳባቸዉና ተከትሎ ከሚመጣዉ ስሜት ዉጪ እኔ የሚባል ነገር የላቸዉም። በመንፈሳዊነት አለመንቃት ትርጉሙም ይኸዉ ነው። በአእምሮአቸው ውስጥ የማያቋርጥ ድምፅ እንደሚመላለስ ስትነግራቸው ፣ ላለመቀበል ብስጭት ብለው "የምን ድምፅ?" ይሉሀል። በርግጥ ድምፁ የማይመለከቱትና የሚያስበው አእምሮአቸው ነው ፤ ሙሉ በሙሉ እንደተቆጣጠራቸው አንድ አካል አድርገህ ልትወስደው ትችላለህ። ❖ የኢጎ ይዘትና መዋቅር ፦ የኢጎ መነሻ አእምሮአችን ሲሆን ኢጎአዊ አእምሮአችን ሙሉ በሙሉ በትናንትናችን የተቃኘ ነው። ቅኝቱም በሁለት የተገመደ ሲሆን ይዘትንና መዋቅርን ያጠቃልላል። መጫወቻው ስለተወሰደበት በጥልቅ ስቃይ የሚያለቅሰውን ህፃን ጉዳይ ብንመለከት ፣ መጫወቻው ይዘትን ያመለክታል። በሌላ ይዘት ፣ በሌላ መጫወቻ ወይም እቃ ሊተካ ይችላል። የምትቆራኝበት ይዘት ፣ በአካባቢህ ፣ በአስተዳደግህ እና በዙሪያህ ባለው ባህል የተቃኘ ነው። የአንድን ሰው ማንነት ለማጠናከር ሲባል ከነገሮች ጋር የሚደረግ ያልተስተዋለ ቁርኝት ፣ በኢጎአዊ አእምሮአችን መዋቅር ላይ የተመሰረተ ነው። ኢጎን ህያው የሚያደርገው መሰረታዊ የአእምሮአችን መዋቅር 'መቆራኘት' ነው። ለምሳሌ 👉 ከቁሶች ጋር ቁርኝት ፦ በዚህ ቁሳዊ አለም አካላዊ ማንነታችን ይኖራልና እቃዎች አስፈላጊና ሊተዉ የማይችሉ የሕይወታችን ክፍሎች ናቸው። ነገር ግን ቁሶችን ለማንነታችን ማጠናከሪያ አልያም እራሳችንን በእነርሱ ውስጥ ለማግኘት ከሞከርን በእርግጥ ልናወድሳቸው አይቻለንም። የዘመናችን አንዱ በሽታ ንብረትን ማባዛት የሆነው ለዚህ ነው። የሆንከውን ህይወት ማጣጣም ሳትችል ስትቀር ፣ ህይወትህን በነገሮች ለመሙላት ትባክናለህ። የተወሰኑ የያዝካቸው ንብረቶችህ የተፈላጊነት ወይም የታላቅነት ስሜትን በጥቂቱም ቢሆን ይጭሩብሀል? እነዚያን ነገሮች ስታጣ ነገሮቹ ካላቸው ሰዎች አንፃር ትንሽነት ይሰማሀል? ለማንነትህ ያለህን ዋጋ ለመጨመር ስትል ያሉህን ንብረቶች በየአጋጣሚው አውጥተህ ለማሳየት ትሞክራለህ? 👉 ከአካልህ ጋር ቁርኝት ፦ ከቁሶች ውጭ ያለው ሌላው መሰረታዊ ቁርኝት ከ "የእኔ "አካል ጋር የምታደርገው ቁርኝት ነው። አካል ወንድ ወይም ሴት ነው። ስለዚህ ወንድ ወይም ሴት መሆን የብዙዎችን የማንነት ስሜት ለመፍጠር ጉልህ ድርሻ ይወስዳል። በምዕራቡ አለም ደግሞ ማንነቴ ነው ብለህ ለምታስበው ስሜት ጉልህ ድርሻ የሚወስደው የአካልህ ሁኔታ ነው። ጥንካሬው ወይም ደካማነቱ ፣ ከሌሎች አንፃር ያለው ውበት ወይም አስቀያሚነት ነው። ለብዙዎች ለማንነታቸው ዋጋ ያለው ስሜት ፣ ካላቸው አካላዊ ጥንካሬ ፣ መልካም ገፅታ እና ውጫዊ ገፅታ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው። ብዙዎች አካላቸው አስቀያሚ ወይም ጎዶሎ መስሎ ስለሚታያቸው የኮሰሰ የማንነት ስሜት ይሰማቸዋል። ምንጭ ፦ አዲስ ምድር (ኤክሀርት ቶሌ) FuFuad At Moon ✍ይቀጥላል
Show all...
👍 1
አባት ዐልባ ሕልሞች በኡትረክት ከተማ ሊመረቅ ነው። አሁን ይኼ ዐረፍተ ነገር ዜና ነው ማስታወቂያ? ለሁለቱም ያገለግላል። የአባት ዐልባ ሕልሞች ነገር "አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው" እየኾነብኝ ነው። ለነገሩ ለማስታወቂያ የምትከፍለው ከሌለህ በየጊዜው እየመጣህ "ሰው ማሰልቸት" ሥራህ ኾኖ ቁጭ ይላል። ለማንኛውም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 21 ቀን 2024 ዶክተር አዜብ አምኃ እና መስፍን አማን መጽሐፏን ያበጥሯታል። ታዳሚዎችን ዘና ለማድረግ ግጥሞች ከመድረክ ይንፎለፎላሉ። በቅንጭብ ትረካ ጆሮዎች ይረሰርሳሉ። በመነባንብ ታዳሚያን ፈታ ዘና ይላሉ። ይህ ሁሉ የሚኾነው በደረቁ አይደለም። እንግዶቼን በባዶ ሆድ አልሸኝም ብዬ 15 ኪሎ ሽንኩርት ብቻዬን ልጬ ለኤልሲ አስረክቤያለሁ። ክሽን ባለው የፆም በያይነቱ አፋችሁን አብሳችሁ የተዋበ እሁድ ለማሳለፍ የምትናፍቁ በኔዘርላንድ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ወደ ኡትሬክት ብቅ በሉ። ብትቀሩ........ ማርያምን እቀየማችኋለሁ።
Show all...
👍 1