cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ኢትዮ ቲቪ ( መረጃ ) 🇪🇹

Show more
Advertising posts
80 046Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ጠዋት ጀምሮ ከጋቲራ እና ዞብል ከአካባቢው ከሚኖሩ ነዋሪዎች ትጥቅ ካስፈቱ በኋላ በገደመዩ በኩል ወደ ቆቦ የባቡሩን መስመር ይዞ ወደ አቧሬና ሮቢት አቅጣጫ እንቅስቃሴ ማድረጉ ታውቋል። @ethio_tv
Show all...
ወገን ወዴት እየሄድን ነው ⁉️ ስራተኛዋ ህፃኑን ፍሪጅ ውስጥ ጨምራው በህይወት ተገኘ!! ሰራተኛዋ በፍሪጅ ውስጥ የዘጋችበት ህፃን ከነ ህይወቱ መገኘቱ ፖሊስ ገለፀ። በሀረሪ ክልል ሀረር ከተማ ቀበሌ 05 ቡዳ በር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስተሰራ የነበረች አንዲት ሴት በሞግዚትነት የምታሳድገዉን የ11ወር ህፃን በፍሪጅ ውስጥ ከታው መገኘቱን የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሴቶችና ህፃናት ምርመራ አስተባባሪ ኮማንደር አበበች ሸዋረጋ አስታውቀዋል ። ህፃኑ በፍሪጅ ውስጥ እንደተዘጋበት የታወቀው የህፃኑ አክስት ወደ ቤት ስትገባ ህፃኑ የታለ ብላ ሰራተኛዋን ስትጠይቅ ሻወር ቤት ነው ብላ ትመልሳለች አክስት፣ ተጠራጥራ ሻወር ቤት ገብታ ስትመለከት የለም መጨረሻ አክስት የታፈነ ድምፅ ትሰማለች ፍሪጅ ስትከፍት ህፃኑ በቲማቲም ማስቀመጫ ፖላስቲክ ውስጥ ተቀምጦ ፍሪጅ ውስጥ ተዘግቶበት እንደተገኘ ኮማንደር አበበች ምርመራው ያመለክታል ብለዋል። ሀላፊዋ እንደገለፁት የህፃኑ እናትና አባት ወደ ስራ በሄዱበት ወቅት አሳዳጊዋ ሰራተኛ ህፃኑ ሁል ግዜ ፍሪጅ እየከፈተ በማስቸገሩ ለማስፈራራት ብላ ፍሪጅ ውስጥ ከታው እንደነበር በወቅቱ ለደረሰችው የህፃኑ አክስት ለምን እንዲህ እንዳደረገች ስትጠይቃት መናገሯን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት እንደምትገኝና ህፃኑ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ታውቋል። ቤተሰብ ህፃኑ ለ2 ሰአት በፍሪጅ ውስጥ ተቀምጦ እንደነበረ ግምታቸውን ይናገራሉ በማለት ኮማንደር አበበች አክለው ገልፀዋል። 🟩🟩🟩➥ @ethio_tv 🟩🟩🟩 🟨✡️🟨➥ @ethio_tv 🟨✡️🟨 🟥🟥🟥➥ @ethio_tv 🟥🟥🟥
Show all...
አሸባሪው ትህነግ ሰሞኑንን በይፋ ሶስተኛውን ወረራ መጀመሩን ተከትሎ በሱዳን የሽብር ስለጠና ሲወስድ የነበረውን በርካታ ሽብርተኛ በሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በሚገኙት በበረከትና ልጉዲ ግንባር አሰልፎ ጦርነት ከፍቶ ሰንብቷል። ይሁን እንጂ ጀግናው የኢትዮጵያ ጥምር ጦር የመጣውን አሸባሪ በዕርሳስ አረር ቆልቶ፣ በቦምብ አንድዶ፣ በመድፍ አዳፍኖ፣ በብሬንን ረፍርፎ፣ በስናይፐር ነድሎ...ወደ አፈርነት ቀላቅሎታል። አመድ አድርጎ በትኖታል። ምሽጉ ተደርምሷል። 🟩🟩🟩➥ @ethio_tv 🟩🟩🟩 🟨✡️🟨➥ @ethio_tv 🟨✡️🟨 🟥🟥🟥➥ @ethio_tv 🟥🟥🟥
Show all...
ዛሬ በሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ በረከት ፊት...ለፊት ግዴማ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ልዩ ስሙ ሸረሪማ ወይም ነጭ ድንጋይ እየተባለ በሚጠራው ቦታ አሸባሪው ትህነግ በከፍተኛ ሁኔታ ገንብቶት የነበረው ጠንካራ ምሽግ በጀግናው የኢትዮጵያ ጥምሮ ጦር ክንድ ተደርምሷል። የአሸባሪው ተወጊ ከምሽጉ ጋር አብሮ ተደምስሷል። የሸረሪማው ወይም የነጩ ዲንጋይ ምሽግ የአሸባሪው ትህነግ በግንባሩ ጠንካራውና የመጨረሻው ምሽግ እንደነበር ታውቋል። 🟩🟩🟩➥ @ethio_tv 🟩🟩🟩 🟨✡️🟨➥ @ethio_tv 🟨✡️🟨 🟥🟥🟥➥ @ethio_tv 🟥🟥🟥
Show all...
❗️ሰበር የድል ዜና ጠንካራውና የመጨረሻው የሸረሪማ ምሽግ ተሰበረ!! ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም ሳምረ የተባለው የትህነግ አሸባሪው ቡድን በማይካድራ ይኖሩ የነበሩ ወደ 2000 የሚጠጉ ንጹሃን የአማራ ተወላጆችን በአማራነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ጨፍጭፎ፣ የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ሲደርስበት ወደ ሱዳን መፈርጠጡ አይዘነጋም። ከዚያም የአሸባሪው ቡድን ታጣቂ በሱዳን የሽብር ስልጠና ሲወድ መቆየቱ ይታወቃል። ሽብርተኛው ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በማበርና ተልኮ በመቀበል የወልቃይት ጠገዴን ኮሊደር ለማስከፈት በተደጋጋሚ ትንኮሳ ሲፈጽም ቆይቶል። ቢሆንም ግን በእየ ጊዜው የጀግኖቹን ክንድ እየቀመሰ ተመልሷል። 🟩🟩🟩➥ @ethio_tv 🟩🟩🟩 🟨✡️🟨➥ @ethio_tv 🟨✡️🟨 🟥🟥🟥➥ @ethio_tv 🟥🟥🟥
Show all...
መረጃ‼️ በወልድያ አቅጣጫ በቃሊም በኩል በላጎ ላይ የነበረው የህውሃትን ምሽግ መከላከያ ተቆጣጥሮታል። @ethio_tv
Show all...
የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ... አሸባሪው ህወሓት ሀገርን የሚያፈርስበትና የኢትዮጵያን ህዝብ በመበቀል ለመከራ የሚዳርግበት አዲስ ሰነድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ገብቷል። አሁን እያካሄደ ያለው ውጊያም የዚሁ አካል ነው። ፅሁፉ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በማሳጠርና መታየት ያለባቸው ነጥቦች ብቻ ቀርቧል። ከሰነዱ የተወሰዱ ዋና ወና ሃሳቦች # ስለ ሰላም አማራጮች ያላቸው አቋም: • የሰላም አማራጭ በሚል ስትራቴጂው፣ በአንድ በኩል ጊዜ ወስዶ ለአጠቃላይ ዘመቻ ለመዘጋጀት በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት ሰላም ፈላጊ አይደለም ብሎ ለዓለም ማህበረሰብ ጥላቻ ለማሰተጋባት እንዲያግዘው በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የጀመረው አካሄድ በፍፁም የማያዋጣና የትግራይ ህዝብን ጥቅም የማያስከብር መሆኑን ያስቀምጣል። • የውስጥ ትግላችን በማገዝ የሚንቀሳቀሱ እንደ ኦነግ የመሳሰሉ አጋሮቻችን እንዲሁም በተለያዬ የዓለም መአዘናት የሚገኙ የትግራይ ዲያስፖራና ዓለም አቀፍ አጋዦቻችንና አጋሮቻችን በዚህ ጊዜ የተሳካ ጥምረት በማድረግ ወደ አዲስ አበባ በምናደርገው እንቅስቃሴና ዘመቻ ከጎናችን መሆናቸውን የሚያረጋግጥ መሆኑን የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ጋር በዝግ ባደረገው ውይይት አረጋግጧል። የአማራ ሃይል የተመለከተ • ይሄ ፅንፈኛ የአማራ ተስፋፊ ሃይል በትግራይ ላይ ካሳየው ጫፍ የወጣ ጥላቻ በላይ፣ በክልሉ ያገኘውን ሕዝባዊ ተቀባይነት ሽፋን በማድረግ እና ጠንካራ ቅንጅት በመፍጠር ከአማራ ክልል መንግሥት የሚስተካከል አቅም መፍጠር በመጀመሩ የዐቢይ አስተዳድር በወሰደው ርምጃ በተወሰነ መልኩ መዳከም ታይቶበታል። አሁንም ግን የዚህ ሃይል አመራሮች በህዝብ ጉያ ተደብቀው ስለሚገኙ ምቹ ሁኔታ ካገኙ ዳግም ሃይል አግኝተው መነሳታቸው አይቀርም። ይህ ሁኔታ የትግራይ ሰራዊት እንደ ጥሩ አጋጣሚ ሊጠቀምበት የሚገባ ሲሆን፣ ይሄ ሃይል ራሱን “ፋኖ” ብሎ በመጥራቱ የተወሰደበት ርምጃ በርከት ያሉ የአማራ ታጋይ ሃይሎች ከዐቢይ ጎን ተሰልፈው ለመንቀሳቀስ ያላቸውን እንዲቀንስ አድርጎታል። ይህንን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት የተፈጠረውን መሻከርና ክፍተት የበለጠ እንዲከር ማድረግ ይገባል። አፋር ክልልን በተመለከተ • የዓፋር መንግሥት የእርዳታ ተደራሽነት በመቆጣጠር በየጊዜው ምክንያት የሌለው ግጭቶች በመፍጠር በአዋሳኝ አከባቢዎች በዘላቂነት ሰላም እንዳይሰፍን በማድረግ በአከባቢው የሚኖሩ ተጋሩ በስጋት ውስጥ እንዲሆኑ አድርጓል። በአወል አርባ የሚመራ ግጭት ቀስቃሽ ቡድን ከዐቢይ አስተዳድር በሚሰጠው አድናቆትና ቁጥር የሌለው የትጥቅ እገዛ አይኑ የታወረ፣ ጆሮው የተደፈነ በመሆኑ፣ ትግላችን በሚያግዙ የዓፋር የነፃነት ታጋዮችና ቤተሰቦቻቸው አፈናና ግድያ እየፈፀመባቸው ይገኛል። ኤርትራን በተመለከተ • ይሄ ፍፁም አምባገነን የሆነ የኤርትራ መንግሥት፣ አሁንም እንደ ትላንት ዋነኛ የሰላምና የትግራይ ህዝብ ነፃነት ጠላት መሆኑ ዳግም እያሳየ ይገኛል። ይሄ ጨቋኝ መንግሥት ባጭር ጊዜ መፍትሄ ካላገኘ ሕዝባችንን ወደ ማያቋርጥ ጦርነትና መከራ ዳግም ለማስገባት የሚችል ስጋት በውስጡ የያዘ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ የዐቢይ ታማኝ አመራሮችና ደጋፊዎች በክልላቸው ውስጥ በምናደርገው እንቅስቃሴ የሚያግዙንን የውስጥ አካላት እያደኑ ማጥቃት ቀጥለዋል። ከኦነግ ጋር ያለን ግንኙነት • ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራር ጃል ሚልኬሳ ጋር በሚስጢር ባደረግነው ውይይት፣ ባጭር ጊዜ አመራራቸው ወደሚመች አከባቢ ወይም ወደ አጎራባች ሃገሮች ስልታዊ ማፈግፈግ የሚያደርጉበት ሁኔታ እንዲመቻች፣ እንዲሁም የመከላከል አቅምና ዝግጁነት የሌላቸው የሰራዊቱ አባላት ከተቻለ ዩኒፎርማቸውን ጥለው ወደ ሕዝባቸው እንዲቀላቀሉና እንዲደበቁ ካልተቻለም ለመንግሥት ሃይሎች እጃቸውን መስጠት የተሻለ አማራጭ እንደሆነ አንስቶ ነበር። • በወለጋ ያለው ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራር መካከል ጃል ራሣና ጃል ቃንቄ በፋሺስት ዐቢይ ከተከፈተባቸው ከበባ ለመውጣት አስቸኳይ ዘዴ ዘይደው መመርያ በመስጠት ወደሚመች ምስጢራዊ ቦታዎች እንዲንቀሳቀሱ የተደረገው ሙከራ የተሳካ ነው። በዚህ አግባብ በአንዳንድ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራሮች መካከል የትግል ስልት ልዩነት ቢኖርም በአስቸጋሪ ሁኔታ ሁነንም የመረጃ ልውውጣችን እና መተጋገዛችን የሚቀጥል ይሆናል። የዚህ ግንኙነት ዋነኛ መሰረት፣ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ለአዲስ አበባ ካላቸው ቅርበትና ለሚታሰበው ዘመቻ ከፍተኛ ትግል በማድረግ ድል ሊያስመዘግቡ የሚችሉ በመሆናቸው ላይ ካለን መተማመን የሚመነጭ ነው። • ይሁን እንጂ አሁንም የፋሺስት ዐቢይ አህመድና ሽመልስ አብዲሳን አገዛዝ ሽባ በማድረግ ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው የመጨረሻ የትግል ምዕራፍ ላይ የቅርብ አጋዦች እነዚህ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በመሆናቸው ሊስተካከሉ የሚገባቸው እና ባለፈው ግምገማ የታዩ ክፍተቶች ታርመው ወደ መጨረሻው ምዕራፍ እንዲዘጋጁ ማድረግ አስፈላጊ ነው። ምንጭ፣ የኢትዮጵያ መከላክያ ሰራዊት 🟩🟩🟩➥ @ethio_tv 🟩🟩🟩 🟨✡️🟨➥ @ethio_tv 🟨✡️🟨 🟥🟥🟥➥ @ethio_tv 🟥🟥🟥
Show all...
ህውሀት‼️ ህወሓት እንደ ሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚጠላው ተቋመ የለም!! ይህ ደግሞ ለሕወሃትን ሃገር የማፍረስ ፍላጎት የሚያመክን ክንደ ነበልባል ጀግኖችን ያቀፈ ከዘመኑ ጋር የዘመነ እና የማድረግ አቅሙ ወደር የለሽ ተቋም በመሆኑ ነው። ለዚህ ነው የመከላከያን ሰራዊትን የሞራል ከፍታ ለማውረድ ተደጋጋሚ ጥቃት የሞከረው። - ለማስታወስ ያህል ሕወሃት ኢትዮጵያን መውጋት የጀመረው የትግራይ ህዝብን ለ20 ዓመተ ሲጠብቅ የነበረውን የሰሜን ዕዝን በማጥቃት ነበር ። - ይህ አልበቃ ብሎ የሰራዊቱን አስከሬን ለቀናት በፀሃይ አስጥቶ በአስከሬኑ ላይ ሲጨፍር የነበረ የአረመኔዎች ስብስብ ነው። የተማረኩትን ከማዋረድ ባለፈ አስፓልት ላይ ሂዱ ብሎ ለቆ በጨለመ በኃላቸው ሲኖ ትራከ የነዳባቸው መሆኑ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። - የሰራዊቱን ክብር ለማዋረድ ሰራዊት ያልሆኑትን የሰራዊቱን ልብስ አልብሶ መንገድ ለመንገድ በአሸንፊያለሁ ጭፈራ ስነልቦናቸውን ለመስበር ያላደረገው የለም። - ከሽብር ቡድኑ በሚወጡ ሰነዶች በግልፅ እንደሚታዪት ሰራዊቱን ለመከፋፈል፣ ለማዋረድ እና ክበሩን ለማዋረድ ከሌሎች ቅጥረኞች ጋር ተናቦ መስራት እንዳለበት ደጋግሞ እና አፅዕኖት ሰጥቶ አስቀምጧል። ስለሆነም የሽብር ቡድኑ የመጨረሻ የቀቢጠ ተስፋ እርምጃ የሰራዊቱን አንድነት እና ስነልቦና ላይ ጥቃት ለማድረግ በመንቀሳቀስ ላይ ነው። ስለሆነም ከሰራዊታችን ጎን በመቆም የጠላትን ሴራ በማክሸፍ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የበኩላችን እንወጣ!! 🟩🟩🟩➥ @ethio_tv 🟩🟩🟩 🟨✡️🟨➥ @ethio_tv 🟨✡️🟨 🟥🟥🟥➥ @ethio_tv 🟥🟥🟥
Show all...