cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የኦርቶዶክስ መዝሙሮች እና ጥቅሶች (pp)🙏🙏

የ ኦርቶዶክስ ጥቅሶች ብቻ⛪💒💒 እየሱስም። አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አይውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተከፋፍለው እጣ ተጣጣሉበት።😭 🙏🙏🙏 የሉቃስ ወንጌ. 23:34

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
364Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ወቀሳ ከብዶህ ባቆምስ ብለሀል? በጣም ለፍተህ እየሰራህ ባለህበት ሁኔታ ውስጥ ባለማወቅ ትንሽ ስህተት ብትፈጠርና በሷ ምክንያት ከፍተኛ ወቀሳ ቢደርስብህ ወቀሳው በጣም ያማል አይደል? ምክንያቱም አውቀህ አይደለም ያጠፋኸው ፣ ጥፋቱ በመከናወኑ አንተ ራስህ ከፍቶሀል በዚያ ላይ ደግሞ በጣም ወጥረህ ከልብህ እየሰራህ ነው ስለዚህ መወቀስ አይገባህም አይደል? ግን ሰው ነህና ሁሌ ትክክል አትሆንም ትሳሳታለህ፣ ሰዋች ይናደዱብሀል የደከምክበት ሁሉ ባዶ እንደሆነ አስኪሰማህ ድረስ ትደርሳለህ እነዚህን ሁሉ ነገሮች ልትቆጣጠራቸው አትችልም ስለዚህ ወደምትቆጣጠረው አተኩር ስህተትህ ስላስተማረህ ነገር በልፋትህ ያገኘኸውን ውጤት ጥፋቶችኽን የምታስተካክልበትን ጥበብ ለማስተዋል ሞክር! ለምን እንዲህ ሆነብኝ አይገባኝም እኮ በሚል ጥቅም የለሽ ሀሳብ ጊዜህን አታባክን ወንድሜ አንተ ብቻ አይደለህም አለም ላይ ያለ ሰው በሙሉ ይሄ ነገር ያጋጥመዋል ታድያ ግን ልዩነቱ ሁሉም የሚቀበሉበት መንገድ ነው! መልካም ቀን ተመኘን 🙏 @Inspire_Ethiopia የእናንተው ምርጥ ጓደኛ ☺️
Show all...
Show all...
የዘማሪ አብርሃም ተገኔ/Zemari Abraham Tegene የጉዞ ላይ አስደናቂ ዝማሪዎች ከከተማው ወጣጣቶች ጋር: Timeket/Ketera/ kanazegelila

ዛሬም ሌላ ልዩ ቀን በባሌ ጎባ ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም የእግዚአብሔር አብን የቃል ኪዳን ታቦት ስናስገባ የነበረውን ልዩ ደስታ ተመልከቱልኝ።በእውነት ገና ትደመማላችሁ እናንተ ብቻ ሰብስክራይብ ላይክና ሼር እያደረጋችሁ መከታተሉን አትዘንጉ።

እንዳሰብነው ባይ ሆን እንኻን እንዳሰበልን አኑሮናል ከዘመን ዘመን አድርሶናል መጪውንም እሱ አብሮን ይሁን 😍 ፈጣሪ 🙇🏽 ይህቺ የጳግሜ ቀናት የይቅርታ እና የምስጋና ቀናት ናቸው ስለሆነም ❣ሳላውቅ በስህተት❤ 💙አውቄ በእህል💔 አስቀይሜ አሳዝኜ አስከፍቼ 💜ከሆነ ከጉልበቴ በርከክ ብዬ💗 💞ይ 💞ቅ 💞ር 💞ታ ጠይቃለው💕 🖤በችግሬ በሃዘኔ ስከፋ ተከፋታችው ሳዝን አዝናችው💘 💖በደስታዬ ተደስታችው ሃሳቤን በመካፈል መፍትሄ ለሰጣችውኝ❣ 💚ስሜታዊ ሆኜም 💙መታግስትን ላስተማራችውኝ💜💗 💖💕💞በዙሪያየ 💓💗💖ያላችው 💙💜❤ሁሉ 💝አ 💝መ 💝ሰ 💝ግ 💝ና 💝ለ 💝ው ❣💝💕💞💓💗 መልካም አዲስ አመት 🌻🌻🌻🌻💐💐💐🌼🌼🌼ላንተ/ቺ ይሁንላችሁ ለጓደኞቻቹ ኣድርሱ እኔም🙋🙌 ከነዛ ውስጥ ከሆንኩ forward ኣድሩጉልኝ😙💕💕💕💕💕💕💕💕💕
Show all...
"እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ" ዕብ 11:13 ዛሬ ማለዳ ወደ ፌስ ቡክ መንደር ጎራ ስል መጀመሪያ ያየሁት የወንድሜን የመምህሬን የትጉሁን አገልጋይ የመጋቤ ሐዲስ አስራት አያንሳ ዜና እረፍትን ነበር። በእውነት ካለው የአገልግሎት ፍቅር ከነበረው ትጋት በተለይ ክፍለ ሀገር ላይ ከከተማ እስከ ገጠሪቱ አንዲት ቤተክርስቲያን የነበረው ወንጌልን ለሕዝብ ሁሉ የማድረስን ተልዕኮ ስለማውቅ ቤተክርስቲያን ድምጿ ሚሰማበት ወንጌልን የምታዳርስበት አንዱንና ምርጡን የክርስቶስ አገልጋይ ማጣቷን ስረዳ አዘንኩ። ሆኖም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አምነውና አገልግለው ስላለፉት ቅዱሳን ምስክርነት በሰጠበት ኃይለ ቃል "እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ" ያለውን እያሰብኩ ተጽናናው። ወንድሜ አስራት እንዳመነ : ክርስቶስን እንደገለጠ : እንዳገለገለ ሞተ!!! ምን መታደል ነው እንዳመኑ እንዳገለገሉ መሞት??? እንዴ እየሰረቁም መሞት እየገደሉም መሞት እንደካዱም መሞት አለ እኮ ጎበዝ! ስንቱ ከነኃጢአቱ ከነበደሉ ሊሞት ወረፋ እየተጠባበቀ ይሆን? ስንቱ እንደካደ ሊሞት ተራውን እየጠበቀ ይሆን? ቸሩ መድኃኔዓለም የወንድሜንስ ሞት ተመኘሁት ለንስሐ ሞት በቅቼ እንዳመንኩህ እያገለገልኩህ እየሰበኩህ ልሙት!!! ነፍስ ይማርልን! ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ ሁሉ መጽናናትን ተመኘሁ! ለቤተክርስቲያንም ተተኪዎችን ያብዛልሽ አልሁ!!! ዲያቆን መሰለ ሞላ ከባሌ ጎባ
Show all...
ታዲያ ለሁሉም ሰው መርሐ ግብር  ይመራሉ። ይህንን ጉባኤ የሚለውን መዝሙር አስመርጠው አብረው ይዘምሩና አሁን ወደ መመህራችን …. እገሌ ብለው ማይክ ይሰጣሉ። (ፕሮግራም መሪ) ይሆናሉ።አንድ ቀን በአጋጣሚ መጣሁ። ማታ አስተምር አሉኝ። በሰዓቱ ተገኘሁ። አላሰብኩትም አባታችን መጡ። ዲያቆኑ ማይክ ፣ ክብ በዳንቴል የተሸፈነች አትሮንስ አወጣ ፡ ጉባኤውን ከፍተው ራሳቸው መዝሙር ዘመሩ እንዳስተምር እሰጠን የቆጡን የባጡን ብዬ ወረድኩ። የእርሳቸው ሥራ መጠቅለል ነው። እንዲህ ብለው ይነሳሉ ..” ግሩም ነው፣ ግሩም ነው ወንድማችን ዛሬ ያስተማረን ብለው…… 10 ደቂቃ ያላልከውን ፣ ያልተከሰተልህን፣ ብለህ ሰምተህ የማትውቀውን፣ ምስጢር ብጥር አድርገው ከልሰው ልክ አንተ እንዳስተማርከው አድርገው “ወንድማችን ያስተማረን ቁም ነገር ይህ ነው” ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥራ ነው የሰራው። ብለው ይዘጉታል። ዛሬ ላይ ሳስበው ምንም ሳይነግሩን ለካ ስብከት ዘዴ ነበር የሚስያስተምሩን። ለካ ተተኪ ነበር የሚያፈሩት። ያኔ እሳቸውን አስቀምጠን ስናስተምር ምንም አይመስለንም ነበር። ዛሬ ላይ ውስጤ ገብቶ ያሸማቅቀኛል ትኅትናቸው። ሳስበው ዕንባዬ ይመጣል። የእሳት ልጅ ዐመድ መሆናችንን ሳስብ። በስም እንደ ፎከርን እንኖራለን። ወይ ነዶ። ምንም ይሁን ምን ፍቅራቸው እጥንቱ ያልገባ ትውልደ ባሌያዊ አለ ማለት ግን አልችልም። ይኽንንም እመለስበታለሁ።ጉባኤ ካለቀ ወደ ቤት ሲገቡ በመንገዳቸው ያገኙትን ሁሉ “ና እራት ብላ” ከአንደበታቸው አትለይም፡ “ና ሻይ ጠጣ” በቃ ሰው ይወዳሉ። ሰላማ ካህናትን፣ ዲያቆናትን፣ ሰንበት ተማሪዎችን ብቻ ሳይሆን ሐዋርያ የሚያደርጉት ሴቶችንም ጭምር ነበር። ዛሬ ላይ “እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው” የሚል ትምህርት ያስተማረችውን ጡርዬን አልረሳም። ይኽ ያየሁትን ምስክርነት ስለሆነ የጻፍኩት። አፈሯ ላይ ቁጭ ብዬ ተምሬያለሁ። (ጎባዎች ምስክር ናቸው) አቡነ ሰላማ ለወንጌል ካላቸው ፍቅር የተነሳ ከዶዶላ፣ አዳባ፣ ሮቤ፣ ሲናና፣ ጋሰራ፣ ደሎ መና፣ ደሎ ሰብሮ፣ ጃራ፣ ጊኒር፣ ከጎሮ፣ አጋርፋ…… ወጣት መሰብሰብ ነው ሥራቸው።ወንጌል የሚያስተምር ይወዳሉ፤ ክህነት ይሰጣሉ። እኛ ሙት ብንሆን እንኳ ስለ ሃይማኖት እሳት ጭረውብን ሄዱ። አምዬ ተዋሕዶ ብረሳሽ የሰላማ አጽም ይወጋኛል። ሁሌም ሲያስተምሩ “የተዋህዶ ልጅ” ይሉ ነበርና። ++ የሰውን ስህተተን የሚይዙበት (የሚያርሙበት) ጥበብ ይኽ የታሪክ ትውስታ የራሴን ነው። ብዙዎች የየራሳቸው ትዝታ እንዳላቸው አውቃለሁ። በተለይ በቅርበት የነበሩ። በእኔ አካባቢ ተመድቤ ሥሰራ (በልጅነት ሊቀ ካህናትም) ያደረጉኝ እርሳችው ነበሩ። እንኳን ያኔ ዛሬ እንኳ ለምንም የማልበቃውን። በመሠረቱ አባታችን ሐዋርያ እንጅ የአስተዳደር ሰው አልነበሩም። ችግሮችን የሚፈቱበት መንገድ ግን በመንፈሳዊ መንገድ ነው።በተለያዩ ጊዜያት ስለተፈጸሙ ችግሮችና የአቡነ ሰላማ ችግር አፈታትን እንይ፦ በ1984 ዓ.ም ከጊኒር መድኅኔ ዓለም ቤ/ክ ጽላት ይሰወራል(ይጠፋል)። ወቅቱ መንግስት የተቀየረበት ወቅት ነበር። ሁለቱ ቀዳሽ ካህናት በጥርጣሬ ይያዛሉ። እስር ቤት ገቡ። ጉዳዩን ካላሳጠርኩ ብቻውን ሌላ ረጅም ታሪክ ነው። ታቦት “ሰረቁ” ተብለው ታሙ ተያዙ። ካህናቱ በመደበኛ ፍርድ ቤት ሳይሆን በየወቅቱ ሕዝቡ እየተሰበሰበ በሚደረግ ውይይት ወታደሮቹ ይዘዋቸው እየመጡ በዐደባባይ ነበር የሚሞገቱት። በአንድ ወቅት በሕዝብ ፊት ይገደሉ ሁሉ ተብሎ ነበር። እጅግ ያን ቀን ሳስበው ይዘገንነኛል። እጅግ ትንንሾች በመሆናችን የምናውቃቸው ካህናት ሲሞቱ ማየት ከባድ ነበር። ጉዳዩ ወደ አቡነ ሰላማ ሲደርስ ጉዳዩ የሃይማኖት፤ የቤተ ክርስቲያን ስለሆነ እራሴ እመጣለሁ ብለው ወደ እኛ ከተማ ጊኒር ይዘልቃሉ። ሁለት ቀን የፈጀ ውይይት ከከተማው ሽማግሌች ጋር አድርገው አሳማኝ መረጃ ይጠፋል። ከዚያም ካህናቱ ከእስር እንዲፈቱ፣ ቤተሰባቸውን ይምሩ፣ ቅዳሴ እንዳይቀድሱ ብለው ይወስናሉ። በቃ ምንም ማስረጃ ስላልነበረ ተለቀቁ። ሰላማዬ ባይገቡበት ኖሮ ምን ሊሆን እንደሚችል አስቡት። ካህናቱ ሁለቱም እጅግ ጎበዝ ጎበዝ ነበሩ። ካህናቱ በሁኔታው በስነ ልቡና ተጎድተው ስለ ነበረ ወደ ቤተ ክርስቲያን መምጣትን እንቢ አሉ። መድኃኔ ዓለም ካልፈረደልን ወደ ግቢው አንገባም ብለው ቀሩ ቀሩ። ከ 8 -10 ዓመት በኋላ በቦታው ካህናት እጥረት ያጋጥማልና። ሁለት ቤተ ክርስቲያናት ካህን በማጣት ይዘጋል። ጫንጮ ሥላሴ እና ኤቢሳ ባለወልድ። ታዲያ አባታችንን አማከርኳቸው። “ዲ/ን ግሩም ኅሳብ ነው አሉ። እነዚህ ሰዎች እኮ ምንም ማስረጃ ሳይኖር ነው የተሰቃዩት ሕዝብ እንዳይቆጣ ነው እንጂ ከሆነማ ጥሩ ነው” ይሉኛል።ባይሆን ከተማው ላይ ሊከብድ ይችላል። ሕዝብ እንዳይቆጣ ተጠንቀቅ ይላሉ። ሁለቱንም ገጠር የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ሕዝቡም ተስማምቶ ተቀጠሩ። እጅግ ደስ በሚል ፍቅርና ትጋት ሁለቱም ከ 18 ዓመት በላይ አገለገሉ።ዛሬ ላይ አንዱ ካህን በሕይወት የሉም (መምሬ ተሰማ በቅጽል ስማቸው (መብረቁ) የድምጻቸው ማማርና ከሩቅ መሰማቱ ነው ስሙን ያሰጣቸው ። አንዱም አረጋዊ አባ ተክለ ማርያም በእድሜ ብዛት ደክመው ቤት ቢውሉም። ወገኖቼ እስቲ እኛ ብንሆን እንዴት እናልፍ ይሆን? ዛሬ ምንም ሳናይ ሳንሰማ የገደልነው ብዙ አይደል??? ለራሳችሁ አስቡት … ብንማርበት ይበጃል። ++ ሌላው ትዝታዬ፦ በ “ዝሙት” ተያዙ ስለተባሉ አባት ነው ስምና ቦታ ለመጥቀስ ሕግም፣ ሞራልም፣ ክርስትናም ይከለክላል። ገመና ድራማ እንጂ ገመና በፌስቡክ አይሰለቅም (የማይቀየር አቋሜ ነው)። ወደ ጉዳዬ ልሂድ፦መነኩሴው ድቀት እገኛቸው ተብሎ ሐሜት ተሰማች። ወሬዋ ተናፈሰች፣ ተራገበች፣ ቡና መጠጫ ሆነች። ጉዳዩ ሰላማ ጆሮ ገባች። ጉዳዩ ጠንከር እያለ መጣ። ማስረጃ አምጡ ቢባል። እገሌ እገሊት ብቻ መባባል ሆነ። እርሳቸውም መነኩሴውን ጠርተው “አባታችን ጉዳዩ ምንድን ነው የምሰማው” ብለው ይጠይቃሉ። የተነጋገሩትን አላውቅም። በማግስቱ “አባታችን ልብን እና ኩላሊትን የሚፈትን እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሕዝብ ካልወደደ መሰናከያ ነው የሚሆነው። ለርስዎም በረከት አይሆንም። የቅዱሳን አምላክ ይከተልዎ። እንዳይራቡ እንዳይጠሙ እኔ የትራንስፖርት እሰጥዎታለሁ። ለእረፍትም እንዲሆንዎ ገዳም ይሂዱ መቼስ መነኩሴ ሌላ ቤት የለውም። እኔስ ማነኝ የምፈርደው” በማለት ሸኟቸው።መነኩሴው በኋላ ላይ ለብፁእነታቸው ጃንደረባ እንደሆኑ ነግረዋቸዋል የሚል ወሬ ሰምቻለሁ። ሰላማን የሚያህል ከባቴ አበሳ አላየሁም። በተለይ ካህንን የሚይዙበት ጥበብ። ++ሁለት አስቂኝ ገጠመኞቼን ላውጋችሁ         ከካህናትን ማሰልጠኛ እንደተመለስኩ ትምህርተ አበ ነፍስ ስልጠና ሰጠሁና ሪፖርት አቀረብኩ “አባታችን ካህናቱን አሰለጠንኩ አስተማርኩ” አልኳቸው እርሳቸውም ምን አልካቸው? አሉኝ ቀለል አድርገው። ድርሻቸው ምን እንደሆነ፣ ምን እንደሚያስነቅፍ፣ ካሕናቱ በምን እየተተቸን እንዳለን፣ ጠበል ሲረጩ አብረው ወንጌል እንዲያስተምሩና፣ መስበክ እንዲያውቁ ነገርኳቸው ስላቸው በአንድ ቃል ” ካናትን እመኑ እንጂ እወቁ አትበላቸው ካልሆነ ይናደዱብሐል አንተ ልጅ ስለሆንክ ” አሉኝ። እንተ የምትለውን አኮ ያውቁታል የካህናት ችግር የሚያውቁትን አምነው አይተገብሩም አሉኝ። እርፍ አልኩት። ይሕው በዚህ ቃል እራሴው ስሟገት እኖራለሁ። የማውቀውን ለማመን በመጣር ውስጥ። “የምታውቀውን እመነው፤ ካመንከው ታደርገዋለህና። ያወከውን ካላደረከው አላመንክም ማለት ነው”
Show all...
በመ/ር ንዋይ ካሳሁን      (አሜሪካ) ብፁዕ አቡነ ሰላማ ሰኔ 18 ቀን 1996 ዓ.ም.  ዕለት የእረፍታቸው  ነው። ማሳሰቢያ (ጳጳሳት በየትኛውም ቀን ይረፉ እንደ ሌላው ሙት አመት ቀናቸው በእለቱ አይታሰብም። ይልቁንም የሁሉም ያረፉ ጳጳሳት መታሰቢያ በመዝገበ ሙታን ተጽፎ በጥቅምት ወር ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ከመጀመሩ ቀድሞ ያለው እሁድ የመታሰቢያ ስማቸው እየተጠራ ይታሰባሉ) ይኽንን ቀን ልጆቻቸው እናዘክረው በማለት ብቻ ነው። ብፁዕነታቸው ከጵጵስና በፊት መሪጌታ ሐዋዝ ወይም አባ ሐዋዝ ይባሉ ነበር።ሰሜን ሸዋ ሰላሌ አውራጃ ጎሐ ጽዮን ወረዳ በ1931 ዓ.ም. ተወለዱ። በአቅራቢያቸው ንባብን ዜማን ተማሩ። ከብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ዲቁናን ተቀበሉ። ከዚያም ቅኔን ከመምህር ጥበቡ ገሜ ተማሩ። የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ትልቅ ፍላጎት ስለነበራቸው ወደ ጎንደር አቅንተው ፋርጣና ጋይንት አካባቢዎች በመዘዋወር ቁም ዜማን አቋቋምን ተማሩ። በዚያው ጎንደር አቋቋምን አስመሰከሩ።ዐቢየ እግዚእ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ ብሉይን ተማሩ። በ1961 ዓ.ም በመሔድ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ሔደው ምንከስናን ፈጸሙ። በ1964 ዓ.ም ቅስናን ተቀበሉ። በወቅቱ ወደ አዲስ አበባ ኮርስ እንዲወስዱ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ተልከው ሳሉ በየአድባራቱ እየተዘዋወሩ ወንጌል ሲሰብኩ የብዙዎችን ቀልብ ይስቡ ጀመር። (አቤት የሰላማ አንደበት) ማር ይፈልቅበት ነበር። ታድያ ቅድስት ማርያም አካባቢ ሰው እየሰበሰቡ ያስተምሩ ነበር። ድምጻቸው ቀጭን በጣም የምትስብ ናት። ታድያ ወዲያው ገነተ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሆነው ተመደቡ። ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንም አገልግለዋል። በዚያው ተያይዞ መናኝ መሆናቸውን ያዩ የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ለኤጲስ ቆጶስነት በ1971 እጩ ሆነው በ1971 ብፁዕ አቡነ ሰላማ የባሌ ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ ተብለው በሶስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ ተሾሙ። “ሰላማ እና ባሌ” ለኦርቶዶክሶች ሰላማ ማለት ባሌ፤ባሌ ማለት ሰላማ ማለት እስኪመስለን ድረስ አንነጣጥልም። ብዙ ቢጻፍ አያልቅም። ወደባሌ የመጡበት ወቅት አደገኛ የደርግ ዘመን ነበር ቢሆንም ሐዋርያ ሰው ይወዳሉ። ቄስ ጌጡን፣ መጋቤ ትፍስህት አንዳርጌ ዘውዴን ፣ ሊቀ ኅሩያን ሰርፀ አበበን የመሰሉ ትንታግ ሰባኬ ወንጌል ሥራ አስኪያጆችን አስይዘው ወጣቱን ያስተምሩ ጀመር። አቡነ ሰላማ ቢሮ የሚውሉበት ቀን ውሱን ነው። ገጠር ለገጠር እንደ ዞሩ ነው ያሳለፋት። እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋቸው ጊንር ከተማዋን ሊባርኩ ሲመጡ በታህሳስ ወር 1985 ሲሆን በዚያንው ጊዜ ዲቁናን ከእርሳቸው ተቀበልኩ። ሰላማ የሁሉም ሰው የሙስሊሙም የክርስቲያኑም አባት መሆናቸውን በቃልም በተግባርም የገለጡ የተራራ ላይ መቅረዝ ነበሩ። ማንንም በደረጃው ሳይንቁ አክብረው ማናገር ይችላሉ። በጣም ለካህን የሚያዝኑ አባት ነበሩ። ትምህርታቸው የማይስበው የማይማርከው ፍጥረት አልነበረም። ሰላማ የሰውን ጸጋ የመለየት ስጦታም አላቸው። ለምግብ ቅባት ነገር በአፋቸው አትዞርም። ዳቦና በደረቅ እንጀራ በበርበሬ፣ ጥሬ ሽንብራ ምግባቸው ሲሆን አጋንንት ገና ከቤት ሳይወጡ በያሉበት ይርድ ነበር። የመሠረቱትን ጎለ ብህንሳ ት የጻድቁን የተክለ ሃይማኖት ገዳሙን እጅግ ከመውደዳቸው የተነሳ ሁሌም ያዘወትራሉ። አዲስ አበባ እንኳ መጥተው ቤት ሳይገቡ ደብረ ሊባኖስ ሔደው ያድራሉ። ሰላማ ሌሊት እንቅልፍ የላቸውም የስግደቱ ምልክት የእጃቸው ጣት መጅ አውጥቶ እግራቸው እንደ እንጨት ደድሮ እንደነበር ለማጠብ ጎንበስ ስንል እናይ ነበር። ሁሌም የማልረሳው ምክራቸው ለክፉው ቀን ስንቅ ሆኖናል። ብፁዕ አቡነ ሰላማ ጎንደር ተዛውረው ለተወሰነ ጊዜ ሰርተው ወደ እንግሊዝ ተቀየሩ። እዚያም በሐዋርያነት አገልግለዋል። በኋላም በፅኑ ህመም ደዌ ዘእሴት ታመው በሕክምና እየተረዱ ቆይተው ወደ ኢየሩሳሌም ሔደው እንዲታከሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ሲወሰን ወንድም የሚሏቸው ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ ተቀብለዋቸው አስታመዋል። ነገር ግን ሕክምናው መፍትሔ ስላልነበረው ወደ ሀገር ቤት ተመልሰው በሐያት ሆስፒታል እየተረዱ ቆይተው  ሰኔ 19 ቀን 1996 ዓ.ም.ዐርፈው በሚወዱት ገዳም በደብረ ሊባኖስ ተቀበሩ።ሰላማ ከጽሑፍ በላይ ናቸው። ስለ እርሳቸው ለመናገር የሚችሉ ብዙ ልጆች አሏቸው። ሰላማ እንደ ጸሐይ ለድሃውም ለሐብታሙም፣ ለመስሊሙ ለክርስቲያኑም፣ ለትንሹም ለትልቁም እኩል የሚደርስ ፍቅር ሰጪ ናቸው። በተለይ ጎባ ከተማው ላደጉ ልጆች ትውስታው ቀላል አይደለም። ባሌ እኔ እስከምገነዘብ ድረስ ሕዝብ በሚወዳቸው ጳጳሳት እድለኛ ነው። ከሁሉም አባቶች ግን ረጅሙን ዘመን ያገለገሉት አቡነ ሰላማ ናቸው። እንደ ልጆቻቸው ጥሪ “ሰላማ” ሰላምችን፣ ሰላማዬ ይባላሉ። ከጊኒር ለሥራ መጥቼ ስለ ሥራና ቦታው ሁኔታ ሳወራቸው። “እኔ እኮ እናንተ ሳትወለዱ ነው ባሌ የመጣሁት” ይሉኝ ነበር። ለማንኛውም ሁሉም ትዝታውን ቢጽፍ እንዴት ደስ ባለኝ ነበር። ስሜቴ ወደ ብዙ ጉዳዮች እየገባብኝ ብዙ ማንነታቸውን እያሰብኩ ለመጻፍ እየተቸገርኩ መከተቤን ያዝኩት……..  ብፁዕ አቡነ ሰላማ + ብኅትውና የብፁዕነታቸው ብኅትውና የጻድቁን የተክለ ሃይማኖትን ዐሠረ ፍኖት እንደተከተሉ የኖሩት ሕይወት ይናገራል። ከወገባቸው ቅንዓተ ዮሐንስን አልፈቱም። አልጋ ላይ አልተኙም። መኝታ ቤታቸው ሰው አይገባም። ለመጀመሪያ ጊዜ እርሳቸው ሔደው አቡነ ዜና ማርቆስ ሲመጡ ቤቱ ሊጸዳ ሲገባ የሚተኙት ቁርበት ላይ መሆኑን ታወቀ። አቡነ ዜና ማርቆስ “እኔ የጻድቁ ሰላማ ያህል ትጉህ አይደለሁም አልጋ አስገቡልኝ” ብለው ነበር ይባላል። ማታ ላይ ውዳሴ ማርያም የሚዘልቁት በዜማ ነበር። ይህንን እርሳቸውን ለማነጋገር ወደ ቤት ስሔድ በር ላይ ሆኜ በተደጋጋሚ ሰምቻለሁ። ወዳሴ ከንቱ እጅግ ከሚጸየፏት ነገር አንዷ ናት። ቅኔ ሲደረግ ሙገሳው ሲጀመር ተው ተው ይላሉ። ምግብ መመገብ መቼ ትዝ እንደሚላቸው አላውቅም። አንድ ጊዜ እንዲህ ሆነ:- ለአገልግሎት ወደ ሲናና ወረዳ የካቲት አጋማሽ ላይ በሔድን ቀን ከቅዳሴ ወጥተን ቀድመን እኛ አስተማርን፣ ከዚያም ቄስ ከተማ የተባሉ ትንታግ የኦሮምኛ ሳበኪ አስተማሩ። መጨረሻ ብፁዕነታቸው ቀጠሉ። በቦታው ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ ነበረችና “አካ ሰሎሜ ኦቶታኔ “ (እንደ ሰሎሜ በሆን ጌታ ሲወለድ ባየን ) የሚለውን መዝሙር ዘመረች። ማንም ከቦታው ሳይነሳ ጉባዔው ሳይበተን ምሽቱ መጣ። ምንም አልበላንም አልጠጣንም እኛ ረሃብ ሊጨርሰን ሆነ። መሽቷል እራት ብሉ ሲባል መንገዱ አመቺ አይደለም እንሄድ ብለው ስንነሳ የኛ አለመብላታችን ትዝ ብሏቸው “ልጆች ምን በላችሁ” አሉን። ሹፌራቸው መዝገቡ “እረ አባታችን ምንም አልበላንም” ቢላቸው። “ልጆች ዛሬ ሞታችሁ” ብለው ዳቦ እንድንይዝ ተደረገ።ከሰላማ ጋር መኖር ሆነ ማገልገል በቃ ከምግብ ተራራቅህ ማለት ነው። ደክሞኛል ልረፍ፣ ርቦኛል ልብላ የለም። ሹፌር አንኳ ይርበዋል አይሉም። ለዚኽ ነው መመገብ እንኳ ትዝ የማይላቸውን ያነሳሁት። (አንጋፋዋ ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ ለጎለ ብኅንሳ ገዳሙ የቁጥር 6 ካሴቷን አበርክታለች። በዚያም ላይ ባሌን ከወር በላይ ከእርሳቸው ጋር ገጠር ለገጠር እየዞረች አገልግላለች። ትልቅ አገልግሎት ነው። እንደውም አቡነ ቀሲስ አይበረክትላቸውም ይባላል። አይበሉ አይጠጡ። በቃ ባኅታዊ ካልሆንክ አልያ ቆራጥ መነኩሴ ካልሆነ አይቻልም።
Show all...
ብጹዕ አቡነ ሰላማ ዘባሌ በረከታቸው አይለየን!!!
Show all...
++መጨራሻ አካባቢ አንድ ሸምገል ያሉ የቀድሞ ሰራዊት ወታደር የነበሩ ሰው ሹፌር ነበሯቸው። በጣም ቀልጣፋ ናቸው። በጣም ታዛዥ ናቸው። እሺ አባታችን ብሎ መታዘዝ ብቻ ነው የሚያውቁት። ጠዋት ቀድመው መጥተው መኪና አዘጋጅተው ይጠብቃሉ። መቋሚያ ተቀብለው ቦታ ያመቻቻሉ። አንድ ቀን ጠዋት ላይ ወደ አዲስ አበባ ልንሸኝ ቆመናል። የሰውየውን መዘጋጀት አይተው። ሊሸኙ ለተሰበሰቡትን ካህናት “አንድ ካህን ከመምራት መቶ ወታደር መምራት ይቀላል” አሉ። ካህናቱ ሳቁ። አይደል እንዴ አባቶች አሉ። ካህናቱም በራሳቸው አዝነው አዎን አባታችን ትክክል ነው አሉ። ሰላማ ማብራሪያ ጨመሩበት ቆም ብለው። ወታደር ወደፊት ሲባል ወደፊት ነው። ተቀመጥ ሲባል ተቀመጥ ነው፤ ሩጥ ሲባል ሩጥ ነው። እኛኮ ስንታዘዝ እንደ ግመል ሽንት ግራ ነን። ብለው በር ዘጉ። ታዲያ ይህ አይነት ተግሳጽ እንዴት ከአዕምሮ ይጠፋል። ሁሌም የሚገርመኝ አባባል ይናገራሉ “አንድ ተራ መነኩሴ ነኝ አኮ” ሰላማን የሚያህል ተጫዋችም አላየሁም። ትልቅ፤ ትንሽ፣ ተማረ፣ አልተማረ የለም ከኔቢጤው ጋር ቆመው ነው የሚያወሩት። እንደ ዮሐንስ አፈወርቅ የድሃ ጠበቃ ነበሩ። ጊንር ላይ ሲያስተምሩ “እግዚአብሔር በሐብታም አድሮ ይሰጣል፤ በደሃ አድሮ ይቀበላል” “ለድሆች መመጽወት በሰማይ ቤት ባንክ መክፈት ነው” ብለው አስተማሩን። ዛሬ ላይ የድሆች መርጃ ማኅበር በሰንበት ትምህርት ቤቱ ከተቋቋመ 218 ዓመቱን አስቆጥሯል። ++ሰላማና ንባብ አቡነ ሰላማን እኔ ለማየት እንደታደልኩት ትልቁ መጽሐፏቸው አዘውትረው የሚመረምሩት መጽሐፍ ቅዱስ እና ሃይማኖተ አበው ነው። ምንም ቢሆን ለንባብ አይቦዝኑም። ++ሰላማና መታሰቢያቸው * መታሰቢያ አንድ ብፁዕነታቸው ብዙ ወዳጅ እንዳላቸው አውቃለሁ። መታሰቢያም ለማድረግ ብዙ የተጣረ ይመስለኛል። በተለይም ባቋቋሙት ገዳም አካባቢ። ወደ ገዳሙ ከሔድኩ ከ 14 ዓመት በላይ ስለሆነኝ ምንም መረጃ የለኝም። ከዚህ ጽሑፍ በኋላ የማገኝ ከሆነ እጠብቃለሁ። ነገር ግን እጅግ ደስ የሚለኝ ቆራጥ መንፈሰ ጠንካራ ትጉህ ባህታዊ፣ ገዳማዊው አባት ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የደብረ ሊባኖሱ መናኝ። ዛሬ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ናቸው። ወደ ሀገረ ስብከቱ እንደመጡ ምንም የልማት ሥራ እንዳልተሰራ ሲያዩ በማዘናቸው ለመስራት ወጠኑ። እኔም እንደተመደቡ ቡራኬ ልቀበል ቤታቸው ስሄድ መስራት እንደሚፈልጉ ነገሩኝ። ደስ አለኝ እኛም እናስተባብራለን አልኳቸው። በቃ የሰላማን ልጆች ያዙ። ከአቡነ ባስልዮስ ጀምሮ ምንም ያልተለወጠውን ያረጀ መንበረ ጵጵስና ለመስራት አሰቡ። በተለይም ታላላቆቹ አባቶች የኖሩበት ቤት እንዲህ ሆኖ ማየት አልሻም በማለት ቁጭት ፈጠሩ። ጎባ ላይ የቢሮ ሰራተኛውን አዘጋጁ። ሥራ አስኪያጁን ሊቀ ስዮማን ንጋቱ ዘውዴ፣ ቀሲስ ፍቃዱ ለገሰ፣ መ/ር ወጋየሁን በተርታ አሰለፉ… (ሁሉም የሰላማ ልጆች የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምሩቃን ናቸው ፣የሀገረ ስብከቱ ሰራተኞች ናቸው)። ወደ ወረዳ ዘመቱ፣ አዲስ አበባ ሊቀ ትጉሃን ኃይለ ጊዮርጊስ ዳኜ፣ እኔ አሰተባባሪ ሆንን። ሰላማ መታሰቢያ መንበረ ጵጵስና ተገነባላቸው። የሰላማ መታሰቢያ ክፍል ይሰየማል። ያገለገሉበት ንዋያተ ቅድሳት፣ ልብስ፣ መስቀል ይቀመጣል። አሁን ሥራው ተጠናቋል። አቡነ ዮሴፍ የስራ አባት ናቸው። ሁለቱም የደብረ ሊባኖስ ፍሬ ናቸው። (ባሌ ጎባ) * መታሰቢያ ሁለት ሁሌም ለአቡነ ሰላማ መታሰቢያ አመታዊ ጉባኤ በጎባ መድኅኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ይደረጋል። ይዘከራሉ። ደስ ሲል። ዘንድሮ በኮቪድ ምክንያት የሚኖር አይመስለኝም። * መታሰቢያ ሦስት የጎባ መድኅኔ ዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት እጅግ ዘመናዊና ትልቅ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ አሰርቷል። ይህ የስብከተ ወንጌልም መታሰቢያነቱ ለአቡነ ሰላማ ነው። *መታሰቢያ አራት በእረፍታቸው ዕለት አዲስ አበባ ያሉ ልጆቻቸው በቦታው እንደሚሄዱና እንደሚዘክሯቸው አውቃለሁ። ዘንድሮን ባላውቅም። በቀጣይ ጽሑፍ ሰላማና የሕመማቸው ወቅት፣ ሞትና ቀብራቸው በተለይም ከአቡነ ጳውሎስ ጋር የነበራቻው ጉዳይን እንዳስሳለን። በረከታቸው አይለየን!!!
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!