cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ግጥምን ለወንጌል

እናውራው ወንጌሉን ባለንበት ሁሉ በትልቅ ትንሹ ይሰበክ ቃሉ በሁሉ ይሰማ ይታወቅ ወንጌሉ

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
385Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
# ሽቶ ሰባሪዋ# ፈሪሳዊው ቤትን ተጋብዛ በማታ እራት እንዲመገብ ተጠራና ጌታ ከእራት ግብዣው ሰፈር ሳትጠራ መታ ቀን ላይ ማያውቋት ሚጠሯት ለማታ አብረዋት ቆሽሸው ሚሏት ጋለሞታ ሳትጠራ መታ ውዷን አከበረች ውድ ምትለውን ከእግሩ አፈሰሰች የደስታዋን እንባ በፀጉሯ አበሰች በነሱ እይታ ቆሽሻ ያደፈች ከሰው ሚዛን ወርዳ ርካሽ የሆነች ለእለት ጉርሷ ብላ የምትኖር በሀፍረት ወዳው እንኳ ባይሆን ተዘፍቃ በሀጢአት ይች ሴት ምናልባት ባትገኝ ባትመጣ ከግብዣው ያንን አልባስጥሮስ ከእግሩ ባታፈሰው አክብረው ከጠሩት ክብር ካላገኘ እግሩን የሚያጥብ አንድም ካልተገኘ ከስሮ ይሆን ጌታ ባትሰብር አምጥታ ለሀጢአቷ ስርየት ፍለጋ ባትመጣ ትምህርት ሳያፅፍ ነበር ወይ ሊወጣ? እንደው ከስሮ ይሆን ? ሀጢአቷ ባይሻር ለሷ መዳን ባይሆን ይከስር ይሆን እንዴ ቦታውን ባትቀይር ተከስታ በአንዴ ከስሮ ይሆን ውዴ? ከስሮ ይሆን እንዴ??? ሰባሪዋ ባትደርስ እላለው አንዳንዴ ...... ገጣሚ:-በስዬ
Show all...
.... .. .........ትዝብት-1........... በሱ ገና ሰበብ ንግድ ተጧጡፏል ስጦታም ይሰጣል የገና ዛፍ ብለው ደግሞ ያቆሙታል ታስቦ ሚውለው santa claus ሆኗል አረ ምን ይሻላል ልደትህ ተዛብቷል ሰው ቀኑን እንጂ አንተን ማክበር ትቷል .......... ትዝብት-2......... ብዙዎች ይላሉ የአንድ ሰው ልደት ነው በቀኑ መብላት ነው ጠጥቶ መርካ..ት ሌሎችም ጨምረው ብዙ ነው ሚሉት .......................................... ሌሎች ብቻ አይደሉም እኔም ደግሞ እላለው ሁሉም ሲጨርሱ የሚሉትን ብለው እኔም ቀጠልኩና ድርሻዬን ስናገር አንድ የገባኝ ሚስጥር አንድ የገባኝ ነገር ዳግም ተወልጄ ዳግም ብፈጠር አንተ ሰው ባትሆን ሰው አልሆን ነበር ................ ትዝብት-2............. ሌሎች ደግሞ አሉ አልመጣም የሚሉ ደግሞ እኮ በኩራት አይሁድ ነን ይላሉ ስለ ሙሴ አብርሀም እየተናገሩ እንደምትወለድ ይጠባበቃሉ .................................. . እንደው ባገኛቸው እንዲህ ነው ምለቸው ሙሴና አብርሀም ለማየት የጓጉለት በራዕይ ትንቢታቸው የተናገሩለት ሰባ ሰገል ወድቀው የሰገዱለት ከዘመናት በፊት ነብያት ያዩት ድንቅ መካር ሀያል ብርቱ ነው ያሉት በግርግም ተኝቶ እረኞች ያዩት በማሪያም ክንዶች ታቅፎ ያገኙት የርህራሄ አባት የፍቅር ንጉስ ወደ አለም መቷል ተወልዷል እየሱስ ✍በበሲ ግጥምን ለወንጌል እናውራው ወንጌሉን ባለንበት ሁሉ በትልቅ ትንሹ ይሰበክ ቃሉ በሁሉ ይሰማ ይታወቅ ወንጌሉ https://t.me/besufikad123
Show all...
#የግጥም_ጊዜ 👉ሳይፀልዩ ማደር🙏😴 የተራበ ነብር 🐆 ከሩቅ ተመልክታ ሚዳቆ 🦌 ፀለየች "አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ ነብሩም 🐆 ተርቦ ወደ አምላኩ ቀርቦ አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ🙏 የሁላችን ሰሪ ፀሎታቸውንም ሰማቸው ፈጣሪ አምላክም በድምጹ 🗣 ሚዳቆዋን 🦌 አላት "እሩጠሽ አምልጪ ከበረታው ጠላት።"🦌 🐆ነብሩንም አለው 🗣 "እሩጥ ተከተላት ምግብ 🍖🍗 አድርገህም ብላት" ሚዳቆዋ ስትሮጥ 🦌 ከነብር ለማምለጥ 🐆 ነብሩም ሲከተላት ሆዱን ሊሞላባት ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ ሆዱን ብትረግጠው የተኛ ከርከሮ ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር አውጣኝ ያለው ወጥቶ አብላኝ ያለው በላ ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ 🐿 ተበላ!🙈 መልካም ጊዜ 🙏 ከግጥም ጊዜ የተወሰደ አቅረቢ ግጥምን ለወንጌል እናውራው ወንጌሉን ባለንበት ሁሉ በትልቅ ትንሹ ይሰበክ ቃሉ በሁሉ ይሰማ ይታወቅ ወንጌሉ https://t.me/besufikad123
Show all...
#ሰውነት ተረሳ-2# ሰው ተረሳ ከሚለው ልነሳ የልቤን ቅሬታ ስሞታዬን ላንሳ ሆነን ቢሆን ኖሮ ኖሮን ቢሆን ኖሮ ትንሽ ሰዋዊነት በኖርን ነበረ ሁላችን ባንድነት በደል - በደል - በደል ሆንን ፍርደ ገምደል ተበዳይ ሲያነባ ሁኖ ጉልበት አልባ በዳዩ ያጋሳል በተበዳይ እንባ በዳዩን መናገር ተበዳይ ቢያቅተው በዳዩ ተበዳይ ሆኖልን አረፈው ከፍርዱ ሸንጎ ፊት ለፍርድ ሊፋጠጡ ከሳሽም ተከሳሽ አብረው ተቀመጡ ተበዳይ ሲያነባ ሲያረገው እንደ እብድ ተበዳይ ሲሳቀቅ በስቃዩ ሲነድ እሚረዱት መስሎት ለሱ ሚፈርዱለት በዳዩ ሳይናገር አንድ እንኳ ከአፉ ዳኛው ወደ ፍርዱ በቶሎ አለፉ ''እሰይ የኔ ጌታ አለ ተበዳዩ ተንሰፈሰፈና ሊሰማ ቀጣዩን'' ዳኛውም ቀጠሉ እኽ - እኽ -እኽ አሉ ''በዛሬው ፍርዳችን በዳይ ከተበዳይ አሁን ለይተናል አሁን በመቀጠል ውሳኔው ይሰማል'' በዚህ ሁሉ መሀል በዳዩም ራሱ የተበዳይ ጨቋኝ ተበዳይም ራሱ ምስኪኑ ተጨቋኝ እስኪሰማ ድረስ የዳኛው ውሳኔ ተሰምቶት ነበረ ተበዳዩ ወኔ ዳኛው ቀጠሉ........ እንደለመደባቸው እኽ - እኽ አሉ ''ተከሳሽ በዳይ ነህ ተባዩ ከሱ ዘንዳ ጥፋት ስላልተገኘበት ይሄ ሸንጎ ሰቶታል ነፃነት'' ''ከሳሽም ተበደልኩኝ ባዩ ያለምንም ጥፋት በሀሰት በመክሰስ ጥፋት ስላጠፋ ራሱ ይከሰስ መዝገቡ ተዘግቶአል መዝገብ ቤት ይመለስ'' በተበዳይ ሁከት እሱ ሚረጋጋ በስቃይ ውጅንብር ተበዳይ ሲጣጋ ስጋው ሲገረፍ በጠኔ አለንጋ ለስጋው ሲዳክር መንፈሱን ሲረሳ በዳዩ...በዳዩ በምቾት ሲያጋሳ ተበዳይ ሲደቅ በአበሳ በበቀል እሳት ለበቀል ሲነሳ . . ክቡሩ ማንነት ሰውነት ተረሳ!!! ✍by:-besi(Ŝőņ ōf ķĩŋğ) ግጥምን ለወንጌል እናውራው ወንጌሉን ባለንበት ሁሉ በትልቅ ትንሹ ይሰበክ ቃሉ በሁሉ ይሰማ ይታወቅ ወንጌሉ https://t.me/besufikad123
Show all...
# እመለሳለው# ሉቃስ 15 አባቴ እያለኝ እባክህን ልጄ ጥዬ ኮበለልኩኝ ድርሻዬን ወስጄ የውጭውን ኑሮ አለምን ወድጄ ከቤቱ ስወጣ ደስታ ማገኝ መስሎኝ ማሰብ አቅቶኝ ማስተዋል ተስኖኝ መቼ ተጠቀምኩኝ ሁሉ ነገር ጎዳኝ ሀብቴን ጨረስኩኝ ክብሩንም ጣልኩና እርያን መረጥኩኝ ደስታን ለመቃረም ከቤቱ ወጥቼ እንዲሁ ተመለስኩ ሀብቴንም አጥፍቼ አሁን ይሻለኛል ወዳንተ ልመለስ አንተ ጋር ነው እንጂ ሌላው ልብ አያደርስ አንተ ሰላም አለህ እንደወንዝ የሚፈስ አንተ እረፍት አለህ መንፈስን የሚያድስ አባ ይሻለኛል በቤትህ ውስጥ ማደግ ካንተ ሌላ የለም ጌታ የሚታደግ ይቅርታን መጠየቅ ሰልችቶኝ ስታክት እሱ ማይሰለቸው እኔን ይቅር ማለት ለእኔ ለአንዱ እጅጉን ሚጨነቅ በኔ መጎሳቀል እሱ የሚሳቀቅ ሚያስብ ሚጨነቅ ለእኔ ለልጁ ሁሌ እሚጠብቅ መምጣቴን ከደጁ ስመለስ አይቶ ሂድ ብሎ ያልገፋኝ ልጄ ብሎ ያለኝ መቼም የማይተወኝ ከልቡ ሚወደኝ እኔስ አባት አለኝ ቀለበት አምጡለት ልብሱን ቀይሩለት ከጠቦቱም ሁሉ የሰባውን እረዱለት ልጄ መቷልና ሙሉ ነው ደስታዬ አለና አባዬ በፍቅር ተቀበለኝ ፍቅር አሳይቶ ልጄ አይደለህም አላለኝም ከቶ አቅፎ ተቀበለኝ እኔነቴን ናፍቆ ስህተቴን ሳይቆጥር ይቅር የሚለኝ በዘላለም መውደድ አንዴ የወደደኝ ስርቀው ማይርቀኝ ጠልቼው ማይጠላኝ ማይሰለች እማይተው እኔስ አባት አለኝ ከቤቱ ለራቅን መመለስ ይሁንልን ✍by:-besu(ŝőņ ŏf ķĩŋğ) ግጥምን ለወንጌል እናውራው ወንጌሉን ባለንበት ሁሉ በትልቅ ትንሹ ይሰበክ ቃሉ በሁሉ ይሰማ ይታወቅ ወንጌሉ https://t.me/besufikad123
Show all...
#የሴይጣን ስሞታ# ሴጣን;- ይግባኝ አለኝ ሰው ሚባል ፍጥረት በተንኮል በለጠኝ ክፋቱ በዛና በሁሉ አስናቀኝ የልቡን ስሞታ ሲናገር ሴጣኑ ያሳብቅበታል ከልቡ መሆኑ በሰው ልጅ ተግባሮች እጁጉን ተማሮ ሲያስማ ሮሮ አይ ሰው እእ..... እያለ ቆይ እኔን ሊስተካከል ታዲያ ምን ጎደለ አወይ የሰው ክፋት በተንኮል በሴራ ሆኖልኛል አባት በሀሜት በቅናት ማን ሊደርስበት? ከፍርዱ ወንበር ላይ ራሴን አስቀመጥኩ ከዚያም እንዲህ አልኩ :-አረ ተው ሴጣኑ ክሱን ተወዉና አንተው ቀጥልበት በክፋት ጎዳና ሰውን ለቀቅ አርገው ይመለሳልና ዳኛ ስለነበርኩ;- ሴጣን ሆይ ክስህ ውድቅ ተደርጎአልህ እስኪ አሰማን ስሞታ ካለህ ;-የኔ ክቡር ዳኛ ስለሰጡኝ እድል አመሰግናለው ያለኝንም ይግባኝ ቀጥዬ አቀርባለው ቀጥል ቀጥል;- እናም አቀርባለው ከልቤ ስሞታ ስለ ቀናሁበት ይስጠኝ የሱን ቦታ ለምን እኔ ብቻ ወንጀለኛ ልባል አረ የሰው ተንኮል ይኸው ከኔ ልቋል ;-እኔም ሰማውና የሴጣኑን ይግባኝ ቆርጦ ለመወሰን በጣም ግራ ገባኝ ከዛም እንዲህ አልኩኝ ሰዎች በሚሰሩት ሴጣን ተሳቀቀ አወይ የሰው ክፋት ሴጣንን አስናቀ ✍by:-besye(śőņ ŏf ķĩŋğ) ግጥምን ለወንጌል እናውራው ወንጌሉን ባለንበት ሁሉ በትልቅ ትንሹ ይሰበክ ቃሉ በሁሉ ይሰማ ይታወቅ ወንጌሉ https://t.me/besufikad123
Show all...
........#ሰውነት ተረሳ#......... ፈጣሪ ፈጠረ ልክ እንደ አምሳሉ ከአፈር ተሰርተው ቆመው ሰው ተባሉ ልዩነት ሳይኖር ለዘመናት ኖሩ በሚሰሩት ሁሉ አብረው እያበሩ ሲኖሩ... ሳለ ከእለታት በአንዱ ቀን አንድ ሀሳብ ተነሳ የቀደመው ህብረት ሰውነት ተረሳ ፍቅርም ተረሳ አንድነት ተረሳ እንደው ምን ሊነሳ ??? ብዙም ጊዜ ሳይሰጥ መጣ ጥል አበሳ ሰው ሰው ላይ በክፋት ተነሳ ሰውነት ተረሳ!! አንድነት ተረሳ!! ደግሞም ተፈጠረ መጣ ዘረኝነት ሰውን እሚለየው በዘርና ሀይማኖት በቀለም በእምነት ደግሞም ተፈጠረ መጣ ጎሰኝነት ሌላውን አርቆ አንዱን የኔ ማለት ተረሳ ሰውነት!! ተረሳ አንድነት!! አንዱን ነጭ ሌላውን ጥቁር አንዱን አርክሶ ሌላውን ሚያከብር እስኪ የትኛው ነው ማይገባው ከአፈር?? ገረመኝ የነጩ ጥቁር ቦሎ ሲንቅ አዋቂው በቂሉ ተገርሞ ሲሳለቅ ከአንድ ወንዝ ጠጥቶ ባንድ ሀገር ኑሮ ዘሬ አይደለህም ብሎ የሚይዝ ጉሮሮ ኦሮሞው ለአማራ አማራው ለትግሬ ትግሬውም ላማራ ሲሆንበት ጠላት በእውነት ያስብላል ተረሳ ሰውነት " " " " " አንድነት ስሙኝ ልንገራቹ የሰውነት ትርጉም አሁንም ያልገባቹ ሰውነት በራሱ ህብረት ነው አንድነት የፍቅር መሰረት የሁሉ መቀነት የፀና ከአለት አንድ እንኳ ጥላቻ ውስጡ የሌለበት ያ ነው ሰውነት!! እስኪ ትዝ ይበለን ሰው መሆናችን ደረጃ አንመድብ ለሚያልፍ አካላችን አይረሳም ሰውነት አንድ ነን ሁላችን!!!! ......ተፃፈ:በበሱ ....join @besufikad123 join...
Show all...
🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼   🌻 🌻🌻🌻   🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻   🌻🌻🌻🌻🌻🌻   🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼🌼   🌼🌼 🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻   🌼 🌼🌼🌼   🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼   🌼🌼🌼🌼🌼🌼   🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 From besye
Show all...
በፈጣሪህ ተደገፍ! ህይወትህን የሚቀይረው ከሰው ጠብቀህ የምታገኘው ነገር አይደለም፤ ፀጋው፣ ስጦታው፣ ቸርነቱ ከማያልቀው ከፈጣሪህ ከምታገኘው በረከት ነው ህይወትህ የሚቀየረው። ወዳጄ በጭራሽ ከሰው እንዳጠብቅ፤ ሰው ማለት ሸንበቆ ነው የሆነ ቀን መቀንጠሱ አይቀርም! ከፈጣሪ ቀጥሎ ራስህን እመነው! ©inspire in Ethiopia @marsilchannel ❇️
Show all...
#ነኝ ኢትዮጲያዊ# የሰው ዘር መገኛ የክብር መናኛ የስልጣኔ ጀማሪ የነበረች መሪ ወጃጇን አክባሪ ጠላቷን ሰባሪ ታላቆች መካሪ ታናሾቿ ተማሪ በሳይንስ በሂሳብ ቀድማ ያስከተለች አፍሪካን በሙሉ በስሟ ያስጠራች የጠላቶቿ ቁጣ ከላይ ቢዘንብባት እሷ ግን የፀናች በሀብቷ ተማርከው ቋምጠው ቢነሱባት እሷ ያልተገዛች በትነው ሊያፈርሷት ብዙ ቢሞክሩ እስከ ዛሬ ያለች እሷ ኢትዮጲያ ነች የግዮን መገኛ አክሱም የቆመባት የቆመው ሲደንቀኝ ላሊበላም ያላት የተፈጥሮ ሀብቱን ፈጣሪ ያደላት ህዝቦቿ የሆኑ አምላክን አዋቂ ናቸው መንፈሳዊ ከነሱ አንደኛው ነኝ ኢትዮጲያዊ እኔ ብሆን እንኳ ዘሬ ሰማያዊ በምድር እስካለው ነኝ ኢትዮጲያዊ ✍✍by:-besu(son of king) Join👇 Join👉 @besufikad123 👈join Join👆
Show all...
#እግዚአብሄር አለላት# በሏት በሏት በሏት በምስራቅም ውጓት በምዕራብም ውጓት ደቡቡ ከብዶባት ሰሜኑ ከፋባት ትከሻዋ ጎብጦ ችግር ቢበዛባት እግ/ር አለላት ተማክረው ሊያፈርሷት አቅደው ሊሰብሯት ጠላቶች አብረው እንደው ቢነሱባት እግ/ር አለላት ፈተናው በርክቶ ረሀብ በዝቶባት ችግሩ አይሎ ቢለው ባናት ባናት እግ/ር አለላት ሚጠብቃት አምላክ የት ሄደና እሱ አባቶች ሲያነቡ እናቶች ሲያለቅሱ ሲጮኹ ወደሱ ሰምቷቸዋል እሱ በአባቶች ምልጃ በእናቶች ፀሎት አለም ሁሉ ይወቅ ለናቃት ኢትዮጲያ እግ/ር አለላት በአባቶች ምልጃ በእናቶች ፀሎት ወጣት ሆይ እወቀው ለሀገርህ ኢትዮጲያ እግ/ር አለላት ✍✍by;-besu(son of king) Join join @besufikad123 join Join
Show all...
#ማንነት# ማንነት ነው ህይወት ህይወትም እኔነት ግን እኔነት አይገልፅም ሙሉውን ማንነት እኔ እኔ እያልኩኝ ለሰዎች ባወራ ህይወቴን ብተርክ ለሌሎች ባጋራ የራሴን ስራ የራሴን መከራ ራሴን ባወራ ማንነቴ አይደል እኔ ያልኩት ስለኔ ያሉኝም አይደለም የሚሆነው በኔ ማንነት ማለት እኔነት ማለት መገኛው ነው ምንጩ ሰው የተገኘበት ማንነት ማለት እኔነት ማለት የተገኘ ነው በእየሱስ ሞት ያ ነው ማንነት እውነተኛ ህይወት የግጥሜ ቁም ነገር የርዕሴ አንድምታ ማንነቴ ነው የፈጠረኝ ጌታ የግጥሜ ቁም ነገር የርዕሴ አንድምታ ማንነቴ ነው የሞተልኝ ጌታ ማንነቴ ነዉ ህይወቱን የሰጠው ለማይገባኝ ለኔ የሞተው መድህኔ ማንነት የለኝም ከሱ ሌላ እኔ ✍✍by son of king(besu) Join 👇 Join👉 @besufikad123 👈join 👆 Join
Show all...
#መልካም ወጣት# መልካም ወጣት የክርስቶስ ቃል የሆነው መሰረት ለአለም የሞተ ለጌታ የኖረ ወንድሙን እሚወድ ለመልካም ያበረ ከመከራ እንኳ ደስታን የሚያይ ችግሩን ለጌታ በፀሎት እሚያዋይ እንደሚፈስ ወንዝ ድንበር የሌለው በገባበት ሁሉ አንድ ሁኖ ሚኖረው መጠቀም ሳይሆን መጥቀም ሚታየው ማያቋርጥ ደግነት ባለቤት ህይወቱ የሆነ ለሌሎች ትምህርት ለጠላት ሀሳብ ሚሆን እንደ አለት ለመልካም ሀሳብ የሚቆም ባንድነት ማህበራዊነት ሚስማማው ፍቅር ደግነትን አመሉ ያረገው በዘርና ጎሳ ከቶ ያልተቧደነ ዘሰው ዘር አንድነት በፍቅር ያመነ ነው መልካም ወጣት ወንጌሉን ለመስበክ ቆርጦ የጀገነ ነው መልካም ወጣት የመልካም ስዕብየና ባለቤት ልቡም የተሞላ በፍፁም ምህረት ነው መልካም ወጣት ቂም የማይቋጥር የሚያደርግ ቸርነት ይቅር ባይ ሰው ይቅር ባይ ማንነት ያ ነው ለእኔ መልካም ወጣት ማለት ደግ የሆነ ሰው ደግ አድራጊ ማንነት ያ ነው ለእኔ መልካም ወጣት ማለት . . . . ቅን ሰው ባለ ቅን ማንነት ያ ነው ለእኔ መልካም ወጣት ማለት ተፃፈ:-በበሱ
Show all...
ቃሉ እና እኔ ቃሉ ወደቀኝ እኔ ወደግራ እድሜዬን በሙሉ በራሴ ስመራ አማኝ የምማስል ቤተክርስቲያ ሄጄ በመምጣቴ ኑሮዬ የአለም ነው ባዶ ነው ህይወቴ ጌታን የተቀበልኩ አማኝ ነኝ እላለው ስሙንም ጠርቼ ከአለም ድኛለው በልቤ አምኜ በአፌ መስክሬአለው የዘላለም ህይወት ከአምላክ አግኝቻለው ከባርነት ህይወት ነፃ ወጥቻለሁ ብዬ አወራለሁ ቃሉን ሳላስተውል ምንም ሳልረዳው የተተከልኩ ግን ፍሬ ማላፈራ ክርስቲያን መስላልው ግን የሌለኝ ስፍራ ለሚያየኝ የመሰልኩ የእየሱስ ተከታይ ቃሉን አንብቤ ግን ወደራሴ ሳይ በማስተዋል ሆኜ መጽሐፉን ሳነበው ለካ ነበርኩ እኔ በፈቃዴ መኖር ፍቃዱን ሳላውቀው በቤቱ እየኖርኩ ለአለም የተጋው ብዙ አመት የኖርኩኝ ተከታይ ነኝ ብዬ ህይወቴን የኖርኩት በአለም ተታልዬ ለካ ገና ነበርኩ ያልበሰልኩኝ ጥሬ ምንም ያላወኩኝ ቃሉንም መርምሬ ገና እምቦቀቅላ እንጭጭ ያላደኩኝ በፈቃዴ ስኖር ፍቃዱን የትውኩኝ ለካ ለካ አማኝ ማለት እርሱን የሚከተል ከሌሎች ሰዎች ጋር የማይመሳሰል የራሱ አርማ ያለው ጌታን የሚመስል ፍቅር❤️ የቅርታና🙏 ቅድስናን ለብሶ የሚገኝ የጌታን ትእዛዝ በልቡ ፈፅሞ የተገኘ ሰውን ሲወድ እርሱ እንደ ጌታ እየሱስ ፍቅርና ❤️ ይቅርታ🙏 የሆነበት ሱስ ሰውን የማይጠላ ፈፅሞ ማይገፋ ጠላትን ረግጦ ጥላቻን ሚገፋ ቂም እና በቀልን ከህይወቱ አባሮ ሰውን ወዶ ማይጠግብ ከነፍሱ አምርሮ ለሚወዱት ወዳጅ ለሚጠሉት አፍቃሪ ጥላቻ የሚሉት ውስጡ የለው ቀሪ ሁሉን ሰው የሚያይ ነው በፈቅር ፍቅርን በቃል ሳይሆን በተግባር የሚገልፅ አማኝ ማለት ለኔ የህንን ተግብሮ በህይወቱ ያኖረ ነው አማኝ ማለት ለኔ የህይወቱን ምሳሌ ጌታን ያረገ ነው አማኝ ማለት ለኔ ይህ ብቻ አይደለም ገና ሌላም አለው 🙏🙏 ተፃፈ በያቡ
Show all...
ሽቶ ሰባሪውዋ ከራት ግብዣው ሰፈር ሳትጠራ መታ ከማኽሪዋ እግር ስር በእምባ ተደፍታ ቀን ላይ ማትታወቅ ማታ ግን ተጠርታ አብረዋት ቆሽሸው ሚሏት ጋለሞታ ሳትጠራ መታ ውዷን አከበረች ውድ ምትለውን እግሩ ላይ አፈሰሰች የደስታ እምባዋን በፀጉሯ አበሰች በነሱ እይታ ከንፃት ያደፈች ከሰው ሚዛን ወርዳ እርካሽ የሆነች ለለት ጉርሷ ብላ በአፍረቷ ምትኖር ነብሷ ፅድቅ ሸሽቶ በምድር የሚቀር ይቺ ሴት ምናልባት ባትገኝ ባትመጣ ከግብዣው የከበረውን ሽቶ ከግሩ ባታፈሰው አክብረው ከጠሩት ክብር ካላገኘ እግሮቹን የሚያጥብ አድም ካልተገኘ ከስሮ ይሆን ጌታ? አምጥታ ባትሰብር እራት ተጋበዝኩኝ ብሎ ያልፍ ነበር🤔🤔🤔 ከስሮ ይሆን ጌታ? ያቺ ሴት ባትመጣ ትምርትን ሳያፅፍ ነበር ወይ ይወጣ 🤔🤔🤔 ይከስር ይሆን እንዴ ቦታውን ባትቀይር ተከስታ ባንዴ ከስሮ ይሆን ውዴ🤔🤔 ሰባሪዋ ባትደርስ እላለው አንዳንዴ??????? ✍✍✍✍beti yohans😍😍
Show all...
ማነው??? ማነው? ማነው? ማነው? የጠላትን ግብዣ አልቀበል ያለው አረ ማነው ጀግና? ለስጋው ያልኖረ ላምላኩ የቀና አረ ማነው ጎበዝ? ወንጌሉን ይዞ የሚፈስ እንደወንዝ ቆሞም ተቀምጦ ቃሉን የሚያወራ የወንጌልን ዘር በምድር ሚዘራ ደፋ ቀና የሚል ላምላኩ አደራ እንደው እስኪ ማነው? የወንጌልን ችቦ በልቡ ያኖረው አደራ ያልበላ ላደራው ሚኖረው እንደው እስኪ ማነው? ማነው ያ ሰው አንድ አላማ ኖሮት ለአምላኩ ኖሮ ለአምላኩ ሚሞት ማነው ማነው የካደ ራሱን ለመከተል እሱን ለሱ ሰቶ ነፍሱን ያ ነው አርበኛ ዘማች ለወንጌሉ የወንጌሉን ዝና የሚያደርስ ለሁሉ ታዲያ እሱ ማነው?? ጥያቄው ላንተ ነው! እኮ ታዲያ ማነው?? ጥያቄው ላንቺ ነው! እኔ ግን ለራሴ እኔ ነኝ ብያለው የወንጌሉን ዝና ላለም አወራለው ተፃፈ:-በበሱ ከላይ ነው ከእሱ
Show all...
🙏 ይቅርታ🙏 ስለ ይቅርታ ተማርኩኝ ከጌታ ሶስቴ ለካደው ሰው ዳግም ይቅር ካለው ያቺን ሀጢአተኛ ከፊቱ አመጧት በልባቸው ቋምጠው በድንጋይ ሊወግሯት መስሏቸው ነበረ ጌታ ሚፈርድባት መሬት ላይ ፃፈና ካምስቱ በአንዱ ጣት ሀጢአት የሌለበት አላቸው ይውገራት ሞትን ስትጠብቅ ምህረት ሆነላት ሀጢአት እማያውቀው ሀጢአት የሌለበት ፃድቁ ጌታችን እሷን ይቅር ካላት ምረትን ሳይሰስት ይቅርታን ከሰጣት እኛ በደለኞች የሀጢአት ጎተራዎች እኛም ራሳችን ይቅር የተባልን የምረት ስሪቶች በእርሱ ቤዛነት በህይወት የኖርን የደሙ ውጤቶች ይቅርታን መለገስ ካቃተን ለሌሎች አናውቅም ማለት ነው ጌታ እየሱስን ምናመልከውን አምላክ አናውቅማ እሱን የለም የለም የለም እኔ አውቀዋለው ልክ እንደዚህ ነው ሁሉ ሰው የሚለው እና ካወቃቹት ይቅር ባዩን አምላክ ወገን ከሆናቹ የእግ/ር አብራክ እናንተ ሆናቹ የይቅርታ ውጤቶች እንዴት አትለግሱም ይቅታን ለሌሎች ተፃፈ:-በበሱ ክብሩ ግን ለእሱ ይሁን ለንጉሱ
Show all...
#ተገልጋይ ሆነዋል# ይገለገል ነበር ጌታ በባሮቹ ስለሱ ተርከው በማይሰለቹ ይወራ ነበረ ጌታ በየቸርቹ እና ይኸውላቹ ሁሉም ሳይሆኑ በጣም ጥቂቶቹ ተቀባን ባዮቹ ለነሱ ተብሎ አለ የምቾት ወንበር ደግሞ አይመቻቸው ላስቲክ እንጨት ነገር ወተው መድረክ ላይ እንደዚ ይላሉ እስኪ ለጌታ ቤት ብር አለኝ ምትሉ ለጌታ ስትሉ ወጣ ወጣ በሉ እንደዚ እያሉ እንደዚያ እያሉ እኔ የምለው ግን ታዲያ የታል ቃሉ ቆይ ቆይ ሰባኪው ምን አሉ መፅሀፉን ከፍተው እንዲህ ይሉሀል የስብከቴ ርዕስ መስጠት ይባላል ለእኔ ስትሰጥ ጌታ ይሰጥሀል አሜን ይባላል ይሉናል ይሉናል ይሉናል ይብላኝ ለቀደሙት የአሁኖቹማ ተገልጋይ ሆነዋል የዛሬው ስብከቴ በዚህ ተጠናቋል ይሉናል -ይሉናል -ይሉናል አገልጋይ የተባሉት ተገልጋይ ሆነዋል ተፃፈ:-በበሱ(son of king)
Show all...
#ኢትዮጲያ ተስፋ አላት# መከራው በዛ ሰቆቃውም በዛ ህይወታችን አጣ የሰላምን ለዛ ስደቱ በርክቶ ስቃዩም በዛና የችግሩ እንጂ የመፍትሄው አካል ሚሆን ሰው ጠፋና የለም አስባለን ለሀገራችን ተስፋ መሰለን ሁላችን ፍዳችን በርክቶ ሰላም የጠፋ ይኸው ስማኝ እንካ የምፅፈው ግጥም አይደል ፖለቲካ ኋላ እንዳልነካካ ሰላምን ሚነሱ አሉን ጠላቶች ለሀገሬ ህዝብ ለሀገሬ ዜጎች የእግር እሳቶች ዋናዎቹ ግብፆች አለች ደግሞ ሱዳን አጎብዳጅ ለሌሎች ይኸው ስማኝ እንካ የምፅፈው ግጥም አይደል ፖለቲካ ኋላ እንዳልነካካ እኔስ የሚገርሙኝ የኛዎቹ ባንዳ ሸኔና ህወሀት አሉ በኛ ዘንዳ ለሀገር ለህዝቡ የሆኑ ዱብ እዳ ግርምትን ያጫረኝ አፌን ያሲያዘኝ አቋሙ ማይገባኝ የሀገሬው ወጣት ልክ እንደ ፔስታል የሚሄድ የሚጓዝ ወደ ነፈሰበት እኔ ግን እላለው ሀገሬ ተስፋ አላት ችግሩ ቢጨምር ቢለው ባናት ባናት ሀገሬ ተስፋ አላት ላገሩ እሚያስብ ተስፋ የሚሆናት ሚረከባት ትውልድ ቢጠፋም ወጣት ሀገሬ ተስፋ አላት የሌለ ቢመስልም ነገ የሚመራት ሀገሬ ተስፋ አላት ብዙዎች ቢሉንም "አይ ይቺ ሀገር ምንም ተስፋ የላት" እኔ ግን እላለው ሀገሬ ተስፋ አላት!!! ተፃፈ:-በበሱ(son of king)
Show all...
Tebarekilgn
Show all...
" ሌላ አለው❤️❤️❤️" ዘምረው ቢያልፋ ብዙ ዘማሪዎች ሰብከው ኖረውት ወንጌላዊዎች ለንሰሀ ሚሆን መዝሙር ብናጣም ለወንጌል ልዝብ መሪ ቢመጣም ከልቡ አፍቃሪው ምህረት ስላለው ለልጁ ሚሆን እሱ ሌላ አለው 🙏🙏🙏🙏 ጭንቅ ቢበዛ ሀዘን በቤቴ አቅሜን ባጣ ቢዝል ጉልበቴ በራሴ ሀሳብ በችግር ብዋጥ አባ ሌላ አለው ቤቴን ሚለውጥ አብርሃም ገባው በድሜ እዳመሸ ጌታም የረሳው መስሎት የዋሸ ትንቢቱን ሲያጣ ዳግም ሲነቃ በራሱ ቢያምን ሁሉ እዳበቃ መቼ በሱ ሀሳብ በአህምሮው ግምት መች በጠበቀው ባተኮረበት በተገለጠው በሚያየው ነገር የታመነለት ፅኑ አይበገር ተስፋ ሲቆርጥ እምነቱ ሲደክም የዘር ድምሩን ቆጥሮ እንዲያልም ሌት ይጠራዋ ማንም ሳይሰማ የልብ ውጥኑን ለሱ ሊያሰማ በቃ አልቋል ብዬ እኔ ብደክምም ተስፈኛው ልቤ ሊወድቅ ቢያዘምም ጌታ ሌላ አለው ሰው ማያስበው አባ ሌላ አለው እራሱ ያሰበው😍😍😍😊😊😊 ሌላም አለህ አሜን🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ✍✍✍✍ቤቲ ዮሐንስ
Show all...
#አፈር አፈር አይንካኝ አለ# ታዘብኩኝ ታዘብኩኝ ደግሞም ገረመኝ የሰውን ልቦና ሀሳቡን ሳየው የልቡን መሻት ስሜቱን ሳጤነው አፈረ ሆኖ ሳለ አፈር አይንካኝ የሚል ነው የሞላው አፈር አፈር አይንካኝ ብሎ በሚያየው ተታሎ ዘላቂውን ጥሎ አፈር አፈር አይንካኝ ብሎ ዙሪያውን በድንጋይ አጥሮና ከልሎ እንዲያው ላይቀርለት ወዳአፈር መመለስ ምነው ላጭር ህይወት የሰው እንባ ማፈሰስ ዘላለም እያለ ለጠፊው መልከስከስ በአካል ተደስቶ በህሊና መከሰስ አፈር አፈር አይንካኝ አለ አለኝ ጓደኛዬ እኔም ፃፍኩለታ ለዛኛው ሰውዬ አይነካኝም ላለው ስጋዬን አፈር ለፈለገው ሰው የሰማይን ሳይሆን የምድርን ክብር አንተ ብትል እንኳ አይሆን ስጋዬ አፈር ዘላለምን ትተህ ለስጋህ ብትኖር የኖርክለት ስጋ አፈር መሆኑ አይቀር!!!!!!! ምክንያቱ ምን መሰለ ከለታት ባንዱ ቀን እግዜሩ እንዲህ አለ አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለ!!! መበደል እንዳለ መበደል እንዳለ መኖርም እንዳለ መሞትም እንዳለ እግዜሩ እንዲህ አለ አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለ!!! በምድራዊው ህይወት በስጋህ ተታለ አትርሳ አምላክን ባክህን አትባክን ባጭሯ ህይወትህ በዝች በትንሿ ጌታ ቢከብርበት አምላክ ቢነግስበት እስከመጨረሻ ስጋህ አፈር ቢሆን ነፍስህ ትድናለች ዘላለም የመኖር እድል ታገኛለች ጌታን የተጠጋች እሱን እሱን ያለች ነፍስ እንዴት ታድላለች
Show all...
ይሄን ግጥም የፃፈችልን ቤቲ ነች ጌታ ይባርበካት እናንተም ተባረኩበት
Show all...
" እልውና🙇‍♀🙇‍♀" በምድረ በዳ አዲት ጠብታ ብላ ብትመኝ ነብሴ ተጠምታ ምኞቷ ደርሶ ጠብ.ሲልላት ተድላና ሀሴት ደስታ ሆነላት በውሃ ጠብታ የረካች ነብሴ ደስታ እረፍቷ ገርሞኝ ለራሴ ውሃ ና በርሀን እያመዛዘንኩ ስለ እልውና እራሴን ጠየኩ ያንተ መገኘት ያንተ እልውና ዙሪያዬን ከቦ ክብረ ገናና ውጪውን አላይ ጎኔን አልሰማ ከእልውና ልቤ ሲስማማ መኖር ቢከፋም ኑሮን ሚያስወድድ ከግርግሩ አብ😍ጋር ሚወስድ ሀሳብ ጥያቄን ጭንቅን ሚያስረሳ ምድርን አላውቅ የሷን ሀበሳ ሁሉን ረስቼ በብዙ ደስታ ነብሴ ስታመክ ያለ ይሉኝታ የበራውን ታምር ኑሮዬ አስናቀኝ ደስታዬ በዝቶ ሀዘን ሲርቀኝ ስለዚ_ _ _ ሁሌም እሻለው መንፈስ እዲኖር ከአሉ ባልታው ርቄ ለመኖር በቃኝም አልል ከቶም አልሰለች ሰላሜ እግር ስር ስለተገኘች አሜን🙏🙏🙏 ✍✍✍✍ቤቲ ዮሐንስ
Show all...
#የፍቅር ንጉስ አክሊሉ እሾህ ነው# በአናታቸው አለ ብዙ ነገስታቶች የወርቅና የብር የእንቁ አክሊሎች ገለው ያገኟቸው ካልሆነም ወርሰውት አንዳንዶች በፍትህ አንዳንዶች በጉልበት ዋጋ ከፍለውበት ዋጋ ለማስከፈል ላያቸው የጫኑት ንጉስ ሆኖ ሳለ የፅድቅ አክሊል ጭኖ የፍጥረታት ሁሉ ንጉስ እንኳንም ሆኖ ለሀጢአተኛው ታሞ መከራ ላይ ቆሞ እንዲያ የተዋረደ አላየን ፈፅሞ ንጉስ ሆኖ ሳለ የሰማይ የምድር በኔ በሀጢአተኛው ተይዞ በፍቅር ውርደት ሳይገባው ውርደትን ያየዉ ለኔ የተሰቃየው አፉን ያልከፈተው ስልጣን እያለው ራሱን የሰጠው ጌታ እየሱስ ነው ንጉስ ነህ ባይሉትም ንጉስ የሆነው የወርቅና የእቁ አክሊል ያልፈለገው የፍቅር ንጉስ አክሊሉ እሾህ ነው --------------------------------------- ተፃፈ:-በበሱ(የሱ)
Show all...
ሀሳብ አስተያየት ካላቹ በdiscussion group ላይ መስጠት ትችላላቹ
Show all...
"ግራ የገባው ቀኔ🙆" ቀኑን ለመጋበዝ ንጋት ሲሰናዳ ከንቅልፌ ነቃሁኝ እኔም በማለዳ እራሴን ስዘጋጅ ለለት ጉድጉዴ ማለዳው ተረስቶ ቀትር ሆነ ባንዴ ምኑንም ሳልነካ …አንድንም ሳልይዘው😳 ድካም ቤቴ ገባ ማንም ሳይጋብዘው😔 መንፈሴን አሳስሮ ውሎዬን ሲያለዝብ😒 አንዳች አጣው ከልካይ የሚቆምልኝ ዘብ😏 አሁን ሲበራልኝ ግራ መጋባቴ ገና ባሳብ ብቻ እዲ መደበቴ🤔 ሲገባኝ መገኛው የቀን ማጣፈጫ 😍😍😍 ጥፍጥናን ሚሰጠው ለሆነው አልጫ😘😘😘 ገና ከጅምሩ ከንቅልፌ ስነቃ የለሊት እረፍቴ በሰላም ሲያበቃ ተመስገን ነበረ ከሁሉ ሚቀድመው ማለፍን ከልክሎ መኖር ላደረገው ኸረኔስ ተረዳው ከቀን ውዝግቤ ውሎ ያስተማረኝን ለኑሮ መዝግቤ ስገባ ስወጣ ሳገኝና ሳጣ አንደኛው ተረስቶ ሌላኛው ቢመጣ ሀሳቤ ተወስዶ ቢሰነብት እሩቅ የልቤ ምስጋና ቦታውንም አይለቅ❤️❤️❤️❤️ ማመስገንን ያስለምደን አሜን🙏🙏🙏🙏 ✍✍✍✍"ቤቲ ዮሐንስ"
Show all...
"ውዴ ሊሰቀል ሲል"😭😭 ኃጢያት የሌለበት ፍፁም እውነተኛ ከዙፋኑ ወርዶ ቢገረፍ ቢሰደብ ቢጠላም ስለኛ ክብር ሚገባውን ዕርቃኑን ቢሰቅሉት እዳሻቸው ፈርደው ገርፈው ቢተፋበት ንግስናውን ክደው ንጉሱን ሲንቁት ለንግስናው ክብር እሾ ሲደፉበት ስላልቻለ አይደል ጉልበት ሁሉ የርሱ ልቡ አስቦጂ ሞቶ እዲመለሱ " ታዲያ_ _ _ _ ባይሰቀል"🤔🤔 መዳን ባይሆንልን በመስቀል ላይ ስራ ፅድቀትን ባንለብስ ከልቡ ባይራራ ተገርፎ ተጠምቶ ሕይወትን ባይሰጠን ፍቅር አስጨንቆት ሞቶ ባያኖረን "ውዴ _ _ _ ባይሰቀል"😶😶 ፅድቅን ለመላበስ እጅግ ስንጨነቅ ፅድቃችን ተገኝቶ ሲሆን የመርገም ጨርቅ በማይጠፋው እሳት ባስፈሪው ጋአነም በተማገድን ነበር እስከ ለዘላለም "አባ_ _ _ ባይሰቀል"😯😯 መቼ ይባላል ዓመተ ምህረት ለነብሳችን ደርሶ ጌታ ባይምራት ውዴ በመስቀሉ ስራውን ባይሰራ ዓመተ ምህረት ባላልን ባልተጠራ " ግን_ _ _ ስለተሰቀለ"😊😍 ስራቹ የታል አሳዮ ሳንባል ከእምነታች ውጪ ሳያሻን በመሀል ኃጢያተኛም ብንሆን ፍፁም የተጣልን በ1ዲያው ኢየሱስ በእምነት ፀደቅን አሜን🙏🙏🙏🙏 ተፃፈ በ""ቤቲ ዮሐንስ""
Show all...
በርባንን ነበርን እኔም አንቺም አንተም በርባንን ነበርን በስራችን ፃድቅ መሆን የተሳነን በሀጢአት ቆሽሸን በአመፃ ረክሰን በደል ያኮሰሰን ሞት የሚገባን እኛም በርባን ነበርን በወይኒ ታስሬ ሞቴን ስጠባበቅ አይደለም የነገን የዛሬን እማላውቅ በሀጢአቴ ብዛት በርባንን የሆንኩኝ በእውነትም ለእኔ ሞት የሚገባኝ የሀጢአት ጎተራ አዎ በርባንን ነበርኩኝ ግን ግን ግን አለ አንድ የእኔ መጨነቅ የሚሰጠው ግድ ግን-ግን አለን እሱ ለማይገባን ለኛ የሰጠን ነፍሱን ለኔ ሲል ከፈለ ሆነ መስዋዕት ለኔ ለሀጢአተኛው ተቀጣ በሞት ከሞትም በኋላ ቀጥሏል ህይወት እየሱስ ተነሰቷል ሞት ሞቷል በሞት ተፃፈ በበሱ(የሱ)
Show all...
ለኔ ነው ሚገባው ለኔ ነው ሚገባው እሱ ያየው ስቃይ ከቤቱ ርቄ ለሆንኩኝ አታላይ ለኔ ነው ሚገባው የእርሱ ውርደት ከበደሌ ብዛት የሚገባኝ ሞት ለኔ ነው ሚገባው የእርሱ ግርፋት በሀጢአት የኖርኩኝ ለብዙ ዘመናት ድነት አላገኘው ዞሬ በአድባራት መዳን አልሆነልኝ ከርሜ ገዳማት ፅድቅን ለማግኘት አልሰራሁኝ ስራ ቤዛ ሆነልኝ እሱ በኔ ተራ እኔስ ይደንቀኛል የወልድ ቤዛነቱ በፍቅር ጥልቀቱ ከፍሎልኝ ህይወቱ ለኔ መመታቱ መቁሰል መድማቱ ወልዶኝ በሞቱ እኔን በምህረቱ ገዛኝ በህይወቱ የነበርኩኝ ከንቱ የተባልኩኝ ---- ከእኔ ሀጢአት በልጦ ቸርነቱ አቆመኝ በቤቱ ሆነልኝ ትንቢቱ ያሉት ነብያቱ ለመዳን ምክንያቱ ነው መዳኒቱ ልክ እንዳወሩት ሞት ሞተ በሞቱ እሱ ብቻ ብርቱ እየሱስ ብቻ ነው የሞት መዳኒቱ በቃ ጨርሻለው ዝም ብሎ ጀምሮ በ1 ቃል ጨረሰው ተፈፀመ። ------ብሎ ህይወቴን ጀመረው ተፃፈ በበሱ(የሱ)
Show all...
--------ይበለን-------- በ በሱ(የሱ) አረ ተዉ በያቸው እማማ ኢትዮጵያ ልጆችሽ ርቀው ከፍቅርሽ ጉያ ጭካኔን ተምረው አረመኔ ሆነው በዘር ተቧድነው አንድነትን ገለው ፍቅርን አንገላተው ካንቺ እንዳልተወለዱ ላንቺ ባዳ ሆነው ይናቆሩልሻል በዘር ተከፋፍለው ጎሳ ለይተው ይጋደሉልሻል ሊተራረዱልሽ ስለታቸው ሾሏል ሰው ያሰቃዩበት እጃቸው ዝሏል ለምለሙ መሬትሽ አኬልዳማ ሆኗል!!! እኛማ እኛማ እኛማ እጁጉን ፈርተናል መድረሻ አተናል የአለም ህይወት እሳት ሆኖብናል ወዴት እንሂድ ማንስ ይዳኘናል???!! የእናቶች እንባ የህፃናት ለቅሶ እንደው መች ነው ሚያበቃው ጨርሶ?? እንባዎችም ደርቀው ፍትህ ስትቀር ኦና ከዚህ የሚያወጣን ማንም የለም እና የሁሉ ፈጣሪ አምላክ ሆይ አንተ ና!!!!!
Show all...
--- የሀበሻ ሽንጎ ----- በካሌብ ሁሴን (ሀምሌት) . ........... ሽቅብ ሳንቀመጥ ብርሀን ሳይወጣ ቀረጥ ሳይቀረጥ የፈራጁ ዳኛ ከ ዋርካው ሳይቀመጥ አንድ ነገር አለ ዝምታ -አኮሰሰን ....!! ዝምታ - አዘመመን...!! በይቁምታ ጣራ በረሀብ ኮሰምን መባቻችን ጠፋን በይሉኝታ ቀጠልን ------- ለካ ለካ-------- ለካ የወንዙ ዳር የእርሻ ጫጫታ ምስ ይፈልጋል የሀበሻ ዕልልታ ----- ቢሆንም ባይሆንም ----- የጨነቀ ለ'ታ የዝምታ ገምቦ ላይፈርድ ላሰቀመጠው ለዚያ ክፉ ሸንጎ!! እውነታን ደብቆ ከፈጣሪ ልቆ ሊፈርደኝ ላኖረው ሊጥለኝ አርቆ ዝም ማለት ንቆ ዝም ማለት ልቆ የቀማኛን ስድብ የቀማኛን ሀሜት ለማሳፈር ዞሮ በሸንጎ ከንቱነት ባሉባልታ ሰበብ ልቤ ሲወድቅ ግዞት ---- አዎ ----- ሸምግዬም ከሆነ ሰለሆንኩ በሳል ልዳኛቹ ብዬ ከወህኒ ዳር ብጣል ይሄ ፍርድ አልባ ነው ይሄ ፍረደ ገምድል አሰተማሪን ሳይሆን ተማሪን መበደል!!! ጨቅላን አሰተኝቶ ነብሰ'ጡሯንመግደል!!! ባህል ነው እያሉ ሳይገደሉ መፎከር ልማድ ነው እያሉ ጠላት ፊት መዘመር ኋላ የምን ዕሪታ ኋላ የምን ዋይታ አልተገዛሁ ብሎ የምንስበው ቃታ አልተሸጥሁም እያለን የቀለጠው ሁካታ ኋላ ኋላ ኋላ የለም የድል ድምፅ የሰነፍ ድንፋታ ታዲያ ምን ያደርጋል ሆኖስ በማን ያደጋል!! በአንደበት ሰይፍ ከመንበር ይርቃል በእዝነተ ታሪክ ላይ ሲያሻው የጋደላል! ሲያሻው ይናቆራል ኤሎሄ ሲዳኘን ያህዌ በፍቅሩ ዳግመኛ ሲቃኘን የሀበሻ ሳይሆን የመሰቀሉ ታየን ----- ከ ፍርድ መልስ -------- ካሌብ ሁሴን (ሀምሌት)
Show all...
ዋጋ የማያስከፍል ጊዜ የማይጠይቅ ከተቀመጥኩበት ቦታ የማያነቃንቀኝ ከሆነ እሱ ራዕይ አይደለም ቅዠት ነው ke 6300 yetewesede
Show all...
አገልጋይ vs ቃሉ 👍👍👍👎👎👎 አገልጋይ ተብሎ የተሰየመ ነው በራሱ ቤት ግን አራስ አንበሳ ነው በትንሽ ትልቁ ቡጢ ሚሰነዝር ከተናደደማ ሚስቱን እንኳን ማይምር በቤቱ ሚያረገው ልክ እንደ ነብር ሰውየው ምን ነበር?? በእሁድ ፕሮግራም ስብከት ተሰቶት የስብከቱን ርዕስ ፍቅርን አርጎት በሚገርም ሁኔታ ፍቅርን ገለፀው በመድረክ ላይ ሰብኮት እሱ ግን ያልኖረው ሚስቱም አይታው ቆሞ ከመድረክ ላይ እያለ ሲሰብክ ፍቅር ነው የበላይ ከዚያም እንደዚህ አለች ይሄ ሰውዬ ቸርች ቸርች ሲሆን መልካም ነው ሚሆነው እቤት ልሂድና እቃዬን ልጫነው ባሌ ፍቅርን ቸርች ነው ሚኖረው ብላ አለችና ሚስቱ ተነሳች እቤቷ ሄዳ እቃዋን ጫነች ከቤቷ ተነስታ ወደ ቸርች መጣች መሪዎች ተገርመው ደንግጠው ጠየቋት ምን አጋጠመሽ ምን አገኘሽ አሏት ባሌ እቤት ሌላ እዚ ደግሞ ሌላ ሲሰብክ ሲያስተምር ሲናገር ስሰማ ፍቅርን ሲሰብክ ፍቅርን ሲያስተምር ተነስቼ መጣው እኔም እዚህ ልኖር ከአገልጋይ እስከ ምዕመን ለየ ቅል ነው ኑሮው ክርስትናን በህይወቱ በተግባር ካልኖረው ይሄ አገልጋይ ምኑን ክርስቲያን ነው! by besu
Show all...
እኔ ማለት ቁ-2 እነሆ ቅዱሳን እደምን አላቹ እስቲ ራሴን ላስተዋውቃቹ አንተ የማን ነህ ከየት ነህ ካላቹ እኔ የእግ/ር አድራሻዬ እላይ እዚህ አለው እንጂ ሀገሬ በሰማይ እኔ ማለት ከማስመሰል ህይወት ወደ መምሰል እውነት በፍቅር ያደኩኝ እሱን ያገኘው እለት በህይወት የኖርኩኝ በእሱ ቤዛነት በነፃ የተሰጠኝ የዘላለም ህይወት ለፍቼበት ሳይሆን አግኝቼው በእምነት ይኸውና የእኔ ማንነት ሌላ ማንም ሳይሆን እሱ ይክበርበት ተፃፈ በ በሱፍቃድ
Show all...