cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Finota Loza orthodox

Orthodox

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
205Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

" አዕሩግ አመ በከዩ ብካየ ረከቡ ወለተ ዘታሥተሰሪ ጌጋየ ለወንጌላውያን ኩልነ ዘኮነተነ ምጉያየ ኢያቄም ወሀና ወለዱ ሰማየ ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ ምስራቀ ምስራቃት ሙፃዕ ፀሐይ እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ " አረጋውያኑ ― በእጅጉ ቢያለቅሱ፣ በደል በምታርቅ ― በሴት ልጅ ተካሱ፤ ለወንጌልም ልጆች ― መሸሻቸው ካለም ፣ ሰማይን ወለዱ ― ሃናና ኢያቄም ፣ ሰማይዋም (ሰማዯም) ፀሐይን ― አውጥታለች ለዓለም፤ የምሥራቃት ምሥራቅ ― መውጫዋ ለፀሐይ ፣ የፍጥረት እመቤት ― የመናዋ ሙዳይ ፣ ዛሬ ተወለደች ― ዳግማዊቷ ሰማይ ። እንኳን "ለልደታችን ቀን" አደረሳችሁ! 🍂🌿🍂🌿🍂🌿🍂🌿🍂🌿🍂 @MENFESAWItsufoche 🍂🌿🍂🌿🍂🌿🍂🌿🍂🌿🍂
Show all...
#ኮነ_ዮም ኮነ ዮም ኮነ ዮም በእንተ ልደታ ለማርያም ከመትቤዙ ነቢያተ ወጻድቃነ ነቢያተ ከመ ትቤዙ #ትርጉም፡፦ ብዙዎች ነቢያት እና ጻድቃን እንደተናገሩት በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ፡፡ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Show all...
✞ክርስቶስ ሕያው ነው✞ ክርስቶስ ሕያው ነው ሞት ይዞ ያላስቀረው የለም ከመቃብር ተነሰቷል በክብር (፪) በገዛ ፈቃዱ ነፍሱን ስለሰጠ የጨለመው ዓለም በብርሃን ተዋጠ ሲኦል ድል መንሳቱ መውጊያውም ታጠፈ የሞት ስልጣን በሞት ስለተሸነፈ አዝ= = = = = የጥሉ ግድግዳ በሞቱ ፈረሰ የነፍሳችን ቁስል በእርሱ ተፈወሰ ከቶ አላስቀረውም የመቃብር ድንጋይ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና ኤልሻዳይ አዝ= = = = = ዓለሙን እንዲሁ እግዚአብሔር ወዶ የሰው ልጅ ከበረ ዲያብሎስ ተዋርዶ ይገዛን ይነዳን ያስጨንቀን ነበር በሞት ላይ ተራመድን አምላካችን ይክበር አዝ= = = = = ሕይወት ይሰጠን ዘንድ ስለኛ የሞተው ቤዛችን ክርስቶስ ሞትን ድል አረገው የሞተው ተነስቶአል በመቃብር የለም ዳግመኛም ይመጣል ሊፈርድ በዓለም መዝሙር ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ ሉቃ፳፬፥፭ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Show all...
#ፋሲካ_ብሂል ፋሲካ ብሂል ማዕዶት(፫) ብሂል #ትርጉም:- ፋሲካ ማለት መሸጋገሪያ ማለት ነው ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Show all...
* ያልፋል ** አሁን የምንገኝበት ጊዜ ኦርቶዶክሳዊነት እንደወርቅ በመከራ እሳት የሚፈተንበት ማንጠሪያ ወቅት ነው። በረከታቸው ይደርብንና ታላቁ አባት፥ ፈዋሴ ዱያን ወሰዳዴ አጋንንት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ (አባ ወልደ ትንሣዔ ግዛው) ዘ ወሊሶ "ከፊታችን ማን አልፎሽ የምትባል የጭንቅና የመከራ ጊዜ አለች የኀዘንና የሰቆቃ ጊዜ ነች። እርሷን ያለፈ ወይም የተሻገረ ከማን ጠግቦሽ ዘመን ይደርሳል የተድላና የፍስሐ ዘመን ነች። ስለዚህ፡- ዕንቅብ ተሰፍቷል መስፈሪያ ሰፌድ ተሰፍቷል ማበጠሪያ የሰው ልጅ ሁሉ ይጠንቀቅ ቆሚያለሁኝ ሲል እንዳይወድቅ።" ይሉ ነበር፡- ተዋህዶ እግዚአብሔር ያፅናሽም ይሉ ነበር። ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስም፡- “በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ።” (2ኛ ቆሮ 13፥5) ሰላለን ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ ቆም ብሎ በማስተዋል ሕይወቱን እንዲመረምርና ራሱን ፈትኖ ከወዴት እንደቆመ እንዲለይ የተጠየቀበት ጊዜ ነው። አሁን እየሆነ ያለው ነገር፡- + የተኛን እንድንነቃ፣ + የወደቅን እንድንነሳ፣ + የራቅን እንድንቀርብ፣ + የተዳደፍን እንድንነጻ፣ + የወጣን እንድንገባ፣ + የሄድን እንድንመለስ፣ + ተዘልለን የተቀመጥን እንድንሰበሰብ፣ + የተጣላን እንድንታረቅ፣ + የበደልን እንድንክስ፣ + ከሥጋ ሀሳብ እንድንርቅ፣ + በምድራዊ ጥበብ እንዳንስት፣ + በእግዚአብሔር ብቻ እንድንመካ፣ + በእውነተኛ ፀፀት ንሥሃ እንድንገባ፣ + ከቅዱስ ሥጋውና ከክቡር ደሙ እንድንሳተፍ ለማድረግ፣ + በባሕርዩ አንድ የሆነን አምላክ የምናመልክ ኦርቶዶክሳውያን ከመለያየት ወጥተን በፊቱ አንድ ልብ፥ አንድ ሀሳብ፥ አንድ መንፈስ ሆነን እንድንቆም ለመጥራት ነው። ከእግዚአብሔር የሆነ፤ ወደ አማናዊው ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት በእውነትና ከልቡ ለመመለስ የማንቂያና የጥሪ ደወል የንሥሃ አዋጅ ነው። ነገር ግን አሁንም ሰው እያስተዋለ አይመስልም። እግዚአብሔር ግን ይጣራል፤ የሚሰማም የሚመልስም የለም። እግዚአብሔር አምላክ በቤተክርስቲያን ውስጥና በሀገራችን ላይ ታላቅ ሥራ እየሠራ ነው እየተረዳው ያለው ግን ጥቂት ነው።ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል፦ "አቤቱ፥ ሥራህ እጅግ ትልቅ ነው፥ አሳብህም እጅግ ጥልቅ ነው። ሰነፍ ሰው አያውቅም፥ ልብ የሌለውም ይህን አያስተውለውም። (መዝሙር 92፥5-6) “እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።”(ኢዮብ 33፥14) አሁን የምናየውና የምንሰማው ሁሉ በጊዜው ያልፋል፣ ጊዜውን የማያልፉ ብዙዎች ግን አሉ። ቤተ ክርስቲያናችን ከነ ሙሉ ክብሯና ሞገሷ ትቀጥላለች፤ በሥራ ላይ ያለው ባለመንሹ እህሉን ሲያበራይ ገለባ ሆነው ስለሚገኙ ከፍሬው ተለይተው የሚቀሩ ብዙዎች ግን አሉ። ሀገራችን አንድነቷ ተጠብቆ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች ይህን ጊዜ ተሻግረው ክብሯን የማያዩ ብዙዎች ግን አሉ። ማንም ኦርቶዶክስ ነኝ ስላለ ሊሆን አይችልም፤ በኦርቶዶክሳዊነት ስም መነገድም አይቻልም፤ ከዚህ በኋላ በስም ኦርቶዶክስ መዝለቅም አይቻልም። ኦርቶዶክስ ነኝ የሚል ሰው በኦርቶዶክሳውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን እምነት መጽናት፥ የኑሯቸውን ፍሬ መመልከት፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል የኖሩበትን ሕይወት መምሰል፥ በኦርቶዶክሳዊ ባህርይ መኖርና መመላለስ አለበት። ኦርቶዶክሳዊነት ክርስትናን መኖር ነው እንጂ ነኝ ማለት አይደለም።(ዕብ.13፥7) ኦርቶዶክሳዊነት፣ በአምሥቱ አዕማደ ምሥጢራት አምኖ በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ተወስኖ መኖር ነው፤ በስም ወይም ነኝ ስላሉ አይደለም። እንግዲህ አስተውሉ፣ የሃዋርያውንም ቃል ስሙ፦ ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ።”(ገላትያ 5፥15) ወገኖቼ እንግዲህ ስንሰፈር ቀለን፣ ስንበጠርም ገለባ ወይም እንክርዳድ ሆነን እንዳንገኝ ይሁን። እግዚአብሔር አምላክ የመከራውን ጊዜ በቸርነቱ አሻግሮ ከፍቅር፥ ከሰላምና ከበረከቱ ዘመን ያድርሰን፤ በከንቱ ከሚጠፉት ወገን አያድርገን።
Show all...
ክርስቶስ ተንስዓ ክርስቶስ ተንስአ እሙታን በአቢይ ሀይል ወስልጣን አሰሮ ለሰይጣን አጋዞ ለአዳም ሰላም (3) እምይእዜሰ ይኩን ሰላም ትርጉም: ክርስቶስ ተነሳ ከሙታን በታላቅ ሀይልና ስልጣን ሰይጣንን አስሮ ነጻ አወጣው አዳምን ሰላም (3) ከንግዲህ ሰላም ይሁን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 👉👉👉@mezmurzhohte 👈👈👈 👉👉 👉@mezmurzhohte 👈👈👈 👉 👉 👉@mezmurzhohte 👈👈👈 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Show all...
ወምድርኒ ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሀፂባ በደመ ክርስቶስ ትርጉም: ምድር ጸዳች ሀሴት አደረገች በክርስቶስ ደም በእውነት ታጠበች 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 👉👉👉@mezmurzhohte 👈👈👈 👉👉 👉@mezmurzhohte 👈👈👈 👉 👉 👉@mezmurzhohte 👈👈👈 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Show all...