cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

መጨረሻው መጨረሻ 📖📢

ይህ ቻናል የተከፈተው ስለ መጨረሻው ዘመን ለማስተማር እና ዘመኑን አውቀን ከጌታ ጋር እየኖርን በጌታ ቀን ጌታን አየር ላይ ለመቀበል ሰዎችን ለማንቃት ነው:: 👉 ስለ የዓለም ፍፃሜ እና ምልክቶቹ 👉 ስለ አርተፍሻል ኢንተለጀንስ እና ሲንጉላርት 👉 ስለ 666 እና ማይክሮቺፕ 👉 ስለ የጌታ ቀን እና ታላቁ ፍርድ ቀን 👉 ስለ አዲስቷ እየሩሳሌም ሮሜ 13:11-12

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
4 007Subscribers
No data24 hours
-17 days
-130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ብዙ ሰዎች የዓለም ሁኔታ በጣም ያስጨንቃቸዋል። ማኅበረሰቡ ራሱ ወደ ከፋ ዝቅጠት እያመራ እንደሆነ ይሰማቸዋል። እንዲያውም አንዳንዶች የሰው ልጅ እርስ በርሱ እንዳይጠፋፋ ይሰጋሉ።  ከዚህ በተቃራኒ ግን ሌሎች በዓለም ላይ ስላሉት ሁኔታዎች መጨነቃቸው ባይቀርም ስለ ወደፊቱ ጊዜ ሲያስቡ መልካም ነገር ይታያቸዋል። የአምላክ መንግሥት በቅርቡ በዓለም ላይ ያሉትን ችግሮች በሙሉ እንደሚያስወግድ ይተማመናሉ። (ዳንኤል 2:44፤ ራእይ 21:3, 4) አምላክ ቃሉን የሚፈጽምበትን ጊዜ በትዕግሥት ይጠባበቃሉ፤ እስከዚያው ግን ኢየሱስ “እስከ መጨረሻው የጸና . . . ይድናል” በማለት የተናገራቸው ቃላት ያጽናኗቸዋል።—ማቴዎስ 24:13፤ ሚክያስ 7:7
Show all...
 ሰዎች ለአምላክ ያላቸው ፍቅር ይቀዘቅዛል። ኢየሱስ “የብዙዎች ፍቅር ይቀዘቅዛል” በማለት አስቀድሞ ተናግሯል። (ማቴዎስ 24:12) አብዛኞቹ ሰዎች ለአምላክ ያላቸው ፍቅር እንደሚቀዘቅዝ መናገሩ ነበር። በ2 ጢሞቴዎስ 3:4 ላይ የሚገኘው ተመሳሳይ ትንቢት ሰዎች በመጨረሻዎቹ ቀናት “ከአምላክ ይልቅ ሥጋዊ ደስታን [እንደሚወዱ]” ይናገራል።  ሃይማኖተኞች ግብዞች ይሆናሉ። በ2 ጢሞቴዎስ 3:5 ላይ የሚገኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት እንደሚናገረው ሰዎች ለታይታ ያህል ለአምላክ ያደሩ መስለው ቢታዩም በሕይወታቸው ውስጥ የእሱን ሕጎች አይከተሉም።  ሰዎች ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ያላቸው ግንዛቤ ይጨምራል። የዳንኤል መጽሐፍ አስቀድሞ እንደተናገረው ‘በፍጻሜው ዘመን’ የሚኖሩ ብዙዎች ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እውነት ያላቸው እውቀት ይጨምራል፤ ለምሳሌ ስለ መጨረሻው ዘመን ትንቢቶች ትክክለኛ ግንዛቤ ይኖራቸዋል።—ዳንኤል 12:4  ዓለም አቀፍ የስብከት ሥራ ይኖራል። ኢየሱስ “ይህ የመንግሥቱ ምሥራች . . . በመላው ምድር ይሰበካል” ብሏል።—ማቴዎስ 24:14  ብዙዎች ግድየለሽና ዘባች ይሆናሉ። ኢየሱስ በትንቢት በተናገረው መሠረት በአብዛኛው ሰዎች መጨረሻው እየቀረበ መምጣቱን የሚጠቁመውን ማስረጃ ችላ ይላሉ። (ማቴዎስ 24:37-39) ከዚህም አልፎ አንዳንዶች 2 ጴጥሮስ 3:3, 4 እንደሚናገረው ማስረጃ ሲቀርብላቸው ያፌዛሉ፤ ጨርሶ ሊቀበሉትም አይፈልጉም።  ሁሉም ትንቢቶች ይፈጸማሉ። ኢየሱስ እንደተናገረው የመጨረሻው ዘመን መድረሱ የሚታወቀው ስለዚያ ጊዜ የተነገሩት ክስተቶች በሙሉ በተመሳሳይ ጊዜ ላይ ሲፈጸሙ ነው፤ ትንቢቶቹ በከፊል ወይም በአብዛኛው ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ሊፈጸሙ ይገባል።—ማቴዎስ 24:33
Show all...
    ‘የመጨረሻዎቹ ቀናት’ ወይም ‘የመጨረሻው ዘመን’ ምልክት ምንድን ነው? ‘የመጨረሻዎቹ ቀናት’ ወይም ‘የመጨረሻው ዘመን’ ምልክት ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?  “የዚህ [አሁን ያለንበት] ሥርዓት መደምደሚያ” ወይም “የዓለም መጨረሻ” ተለይቶ የሚታወቅባቸው ክንውኖችና ሁኔታዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተገልጸዋል፤ በሰዎች ባሕርይ ላይ የሚታየውን ለውጥም መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። (ማቴዎስ 24:3 አዲሱ መደበኛ ትርጉም) መጽሐፍ ቅዱስ ይህን ጊዜ ‘የመጨረሻዎቹ ቀናት’ እንዲሁም “የፍጻሜ ዘመን” ወይም ‘የመጨረሻው ዘመን’ ብሎ ይጠራዋል።—2 ጢሞቴዎስ 3:1፤ ዳንኤል 8:19 አዲሱ መደበኛ ትርጉም ስለ “መጨረሻዎቹ ቀናት” የተነገሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች  መጽሐፍ ቅዱስ የመጨረሻዎቹን ቀናት ለይቶ የሚያሳውቀውን “ምልክት” አስቀድሞ ነግሮናል፤ ይህ ምልክት በተመሳሳይ ጊዜ የሚፈጸሙ ብዙ ክስተቶችን ያካተተ ነው። (ሉቃስ 21:7) ከእነዚህ ክንውኖች አንዳንዶቹን እስቲ እንመልከት፦  በብዙ ቦታዎች ጦርነት ይነሳል። ኢየሱስ “ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሳል” ሲል አስቀድሞ ተናግሯል። (ማቴዎስ 24:7) በተመሳሳይም ራእይ 6:4 ምሳሌያዊ ትርጉም ስላለው አንድ ጋላቢ ይናገራል፤ ይህ ጋላቢ ጦርነትን የሚያመለክት ሲሆን “ሰላምን ከምድር [እንደሚወስድ]” ተነግሯል።  ረሃብ ይከሰታል። ኢየሱስ “የምግብ እጥረት . . . ይከሰታል” ሲል ተናግሯል። (ማቴዎስ 24:7) በራእይ መጽሐፍ ላይ ከተገለጹት ምሳሌያዊ ትርጉም ያላቸው ጋላቢዎች አንዱ ረሃብን ያመለክታል። ይህም በብዙ ቦታዎች ረሃብ እንደሚከሰት ይጠቁማል።—ራእይ 6:5, 6  ታላላቅ የምድር ነውጦች ይከሰታሉ። ኢየሱስ “በተለያየ ስፍራ . . . የምድር ነውጥ ይከሰታል” ብሏል። (ማቴዎስ 24:7፤ ሉቃስ 21:11) በዓለም ዙሪያ የሚከሰቱት እነዚህ ታላላቅ የምድር ነውጦች ታይቶ በማይታወቅ መጠን ብዙዎችን ለመከራና ለሞት ይዳርጋሉ።  ወረርሽኝ ይቀሰቀሳል። ኢየሱስ “ቸነፈር” እንደሚኖር አስቀድሞ ተናግሯል፤ በሌላ አባባል ‘በበሽታ ብዙ ሕዝብ ያልቃል።’—ሉቃስ 21:11 ሕያው ቃል  ወንጀል ይበዛል። እርግጥ ነው፣ ወንጀል ከጥንትም ጀምሮ ነበር። ሆኖም ኢየሱስ እንደተናገረው በመጨረሻዎቹ ቀናት “ክፋት እየበዛ [ይሄዳል]።”—ማቴዎስ 24:12  ሰዎች ምድርን ያበላሻሉ። ራእይ 11:18 የሰው ልጆች ‘ምድርን እንደሚያጠፏት’ ይናገራል። ይህን የሚያደርጉት በተለያዩ መንገዶች ነው፤ አንዳቸው በሌላው ላይ የሚፈጽሙት ግፍና ዓመፅ አንድ ነገር ሆኖ ሳለ በተፈጥሮ ላይም ውድመት ያደርሳሉ።  የሰዎች ባሕርይ ይበላሻል። መጽሐፍ ቅዱስ በ2 ጢሞቴዎስ 3:1-4 ላይ እንደሚናገረው ሰዎች በጥቅሉ ሲታይ “የማያመሰግኑ፣ ታማኝ ያልሆኑ፣ . . . ለመስማማት ፈቃደኞች ያልሆኑ፣ ስም አጥፊዎች፣ ራሳቸውን የማይገዙ፣ ጨካኞች፣ ጥሩ ነገር የማይወዱ፣ ከዳተኞች፣ ግትሮች፣ በኩራት የተወጠሩ” ይሆናሉ። የሰዎች የባሕርይ ዝቅጠት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከመድረሱ የተነሳ ይህ ጊዜ “ለመቋቋም የሚያስቸግር በዓይነቱ ልዩ የሆነ ዘመን” ተብሏል።  የቤተሰብ ዝምድና ይሸረሸራል። በ2 ጢሞቴዎስ 3:2, 3 ላይ የሚገኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት እንደሚናገረው ብዙ ሰዎች ለቤተሰባቸው “ተፈጥሯዊ ፍቅር” አይኖራቸውም፤ ልጆችም ‘ለወላጆቻቸው አይታዘዙም።’
Show all...
#የዓለም_ፍፃሜ_እና_እኛ " የዘለዓለም ሕይወት ወይንም የዘለዓለም ሞት ምርጫው በእጅህ ነው ምን አይነት ሕይወት ውስጥ እየኖርክ ነው? " ድንገት ጌታ አሁን ቢመጣስ? በቻናላችን👇 #መጨረሻው_መጨረሻ_የቀረበ @getayimetal 🙏 ሁሉም ሰው መስማት የሚገባው መልዕክት በጌታ ፍቅር ለሌሎችም አካፍሉት(share) #ክፍል 3
Show all...
#የዓለም_ፍፃሜ_እና_እኛ " የዘለዓለም ሕይወት ወይንም የዘለዓለም ሞት ምርጫው በእጅህ ነው ምን አይነት ሕይወት ውስጥ እየኖርክ ነው? " ድንገት ጌታ አሁን ቢመጣስ? በቻናላችን👇 #መጨረሻው_መጨረሻ_የቀረበ @getayimetal 🙏 ሁሉም ሰው መስማት የሚገባው መልዕክት በጌታ ፍቅር ለሌሎችም አካፍሉት(share) #ክፍል 1
Show all...
#የዓለም_ፍፃሜ_እና_እኛ " የዘለዓለም ሕይወት ወይንም የዘለዓለም ሞት ምርጫው በእጅህ ነው ምን አይነት ሕይወት ውስጥ እየኖርክ ነው? " ድንገት ጌታ አሁን ቢመጣስ? በቻናላችን👇 #መጨረሻው_መጨረሻ_የቀረበ @getayimetal 🙏 ሁሉም ሰው መስማት የሚገባው መልዕክት በጌታ ፍቅር ለሌሎችም አካፍሉት(share) #ክፍል 2
Show all...
መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፥ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም። 🌺 2ኛ ጢሞቴዎስ 4:7-8 💐 𝙇 𝙚 𝙬 𝙞 🥀
Show all...
🙌
1፤ እንግዲህ፥ ልጄ ሆይ፥ አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ። 2፤ ብዙ ሰዎች የመሰከሩለትን ከእኔም የሰማኸውን ሌሎችን ደግሞ ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ። 3፤ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ ወታደር ሆነህ፥ አብረኸኝ መከራ ተቀበል። 4፤ የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያጠላልፍም። 5፤ ደግሞም በጨዋታ የሚታገል ማንም ቢሆን፥ እንደሚገባ አድርጎ ባይታገል፥ የድሉን አክሊል አያገኝም። 6፤ የሚደክመው ገበሬ ፍሬውን ከሚበሉት መጀመሪያ እንዲሆን ይገባዋል። 7፤ የምለውን ተመልከት፤ ጌታም በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጥህ። 8፤ በወንጌል እንደምሰብከው፥ ከሙታን የተነሣውን፥ ከዳዊት ዘርም የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን አስብ፤ ✝ 2ኛ ወደ ጢሞ 2:1-8 ✝ 𝙇 𝙚 𝙬 𝙞 🥀
Show all...
🙌
የመንፈስ ቅዱስ ሙላት
ተከታታይ ትምህርት ለማግኘት
ስለ ፀጋ ስጦታ ትምህርት
አስተማሪ ጥቅሶችን ለማግኘት
የዘመን መጨረሻ ምልክት (666)
ቆየት ያሉት መዝሙሮች ለማግኘት
የተለያየ ታርኮችን ለማወቅ
የአገልግሎት ትምህርት ለማግኘት
ፀሎት እና ምክር የምትፈልጉት
ሁሉንም በአንድ ላይ ለማግኘት