cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

[<ምስጢረ ኢትዮጵያ ወ ተዋህዶ>]

ታሪክን ማወቅ እና መጠበቅ ታሪክን ከመስራት በላይ ነው ። ይህ ቻናል ስለ -ቀደምት አባቶች ስራ -ባህረ ሀሳብ -ስነ ፈለግ -ምክረ አበው እንዲሁም ለ እናንተ ጠቃሚ ናቸው ያልናቸውን ነገሮች የሚለቀቅበት ቻናል ነው ። ግሩኘ @misxerethiopia #ምስጢረኢትዮጵያ መልካም ቆይታ። ለማንኛውም ጥያቄ http//t.me/zera_Yaeqob

Show more
Advertising posts
195Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

✍ ልብ በሉ! እኔ በበኩሌ በጣም የማከብራቸው ባሕታዊ አባ ኪዳነ ማርያም ስለ መስቀሉ ሲናገሩ መስማት ሰላምን ይሰጣል። የእርሳቸውን ስብከት ፈልጋችሁ በደንብ ተረዱ። ችግሩ እንደ እነ ባሕታዊ አባ ኪዳነ ማርያም አይነት የእውነት መምህር አይደመጡም ለካ። እውነተኛ ሰው ተጠልቷል ለካ። የክርስቶስ መስቀልም የተቀበረው እውነትን ስለያዘ ነበር። ዳሩ ግን እውነት ተቀብሮ አይቀርም የሚባለው ብሂል ትክክል ነበር። ይህንን ደግሞ በመስቀሉ አረጋግጠናል። በቃ እንግዲህ ብዕሬን ከዚህች ላይ ያዝ ላድርጋት መሰለኝ። ✍ ሃሳብ አስተያየት ጥያቄም ጭምር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ። ✍🏾 ትላንት የአባቶችህ ነው። ✍🏾 ✍🏾 ነገም የልጆችህ ነወ። ✍🏾 ✍🏾 የአንተ ቀን ዛሬ ነው። ✍🏾 ✥┈┈┈┈••● ◉❖◉●••┈┈┈✥ ✍ ጸሐፊ የእናንተው ብላቴና እብነ ሜሌክ ዘኢትዮጵያ (ዓምደ ብርሃን ) 𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ ϵ 🅐𐌼ⓓϵ 𐌱ι℞Ⴙⓐ𐌽ϵ ♡┈┈••✦ ✦••┈┈┈♡
Show all...
የሰንበት ማለዳ መረጃ ሰማእትነት "…በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ለበርካታ ዓመታት የጊዳ አያና ወረዳ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤትን በሥራ አስኪያጅነት እና የአንገር ጉትን ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን በአስተዳዳሪነት ሲመሩ የነበሩት መልአከ ኃይል ቀሲስ ሀብቱ ደመቀ  በጽንፈኞች የኦነግ ሸኔዎች መገደላቸው ታውቋል። የሰማእቱ አባታችን የመልአከ ኃይል ቀሲስ ሀብቱ ደመቀ ድል የማትነሳ ሃይማኖታቸው ጥርጥር የሌለበት እምነታቸው ይጠብቀን በረከታቸውም ትድረሰን። ዜና አሰቦት ሥላሴ "…ደብረ ወገግ አሰቦት ሥላሴ ወአባ ሳሙኤል ገዳምም ደውያለሁ። ኦነግ ሸኔ ገዳሙ ዙሪያ ሠፍሯል። በገዳሙ እንዲጠበቅ በመንግሥት "የመለስ ዜናዊ ፓርክ" ተብሎ የተሰየመውን ደን እሳት ለቀውበታል። ከገዳሙ ስር ይኖሩ የነበሩት የተዋሕዶ ልጆች በሙሉ ወደ ገዳሙ በመግባት ከአባቶቻቸው ጋር የሚመጣውን ለመቀበል ተዘጋጅተዋል። ዜና ዝቋላ አቦ "…ታላቁ የዝቋላ ደብረ ከዋክብት ገዳም አክራሪው የወሃቢያ የኦሮሞ እስላም ሠራዊት በኦነግ ብልፅግና ሸኔ በሁሉም አቅጣጫ ወደ ገዳሙ በመግባት ከገዳሙ ጥበቃዎች መሣሪያ፣ ከገዳማውያኑ እናቶች የእጅ ስልኮቻቸውን በመንጠቅ “የእኛ ግዛት ስለሆነ ከዚህ በኋላ እኛ ነን የምናስተዳድረው እናንተን አይመለከትም” እንዳሏቸውም ተሰምቷል። የዛሬ ጠዋት መረጃ የለኝም። "…ይህ ሁላ የሚሆነው የሃገሪቱ አየር ኃይል ቤዝ ከሚገኝበት ደብረ ዘይት ግቢ ውስጥ በሉት። መሃል ሃገር ሆኖ ከአዲስ አበባ ተቁሞ የሚታይ ገዳም በኦነግ ቁጥጥር ስር ነው ሲባል ማን ያምናል? እንዲህ ያሉ ዜናዎችን መዘገብም፣ መስማትም የሚፈልግ ያለመኖሩ ደግሞ ይደንቃል። ሰዉ ሁላ እንግሊዝ ተሸነፈችብኝ፣ ፖርቹጋል ወደቀችብኝ ጨጓራዬ ተላጠ፣ ሆዴ ነደደ፣ አንጀቴ ተቃጠለ፣ አረርኩ፣ ደበንኩ ሲል ስታየው ትደነቃለህ። "…አዲስ አበባ ስሚ…!!
Show all...
አንተ.... ኤልያስ ሽታኹን (መወድስ) ~ ~ ~ ~ በሁሉም በየትም አንድም ሦስትም:: አንተ ሦስትም አንድም ቁጣና መውደድም:: አንተ ብቸኛና ብዙ ሁሉም እንዲገዙ:: አንተ ብዙና ብቸኛ የማታንቀላፋ ዓለሙ እንዲተኛ:: አንተ የሰማይ ሰማዩ አንተ የባህር ባህሩ አንተ የፍቅር ፍቅሩ አንተ ተስፋ ለበድን አንተ አፍ የማታስከድን አንተ በዚህ ሲሉህ በዚያ አንተ ሙሉ ደስታ አንተ ሙሉ ቦታ እስመ ዐልቦ መገን ሥላሴ ተመስገን!!! አንተ ኩላሊቴን የምትመረምር ባታገኝብኝም አንድ ድንቅ ታምር እንድኖር ሰጠኸኝ ሌላ የቀን ክምር:: ተመስገን!!! አንተ "በቃኝ" ስልህ የማትሰማኝ አንተ ትልቁን ልትሰጠኝ ትንሽ የምትቀማኝ አንተ "ማንም የለኝም" ስል ዝም ጭጭ እያልከኝ አንተን እስክይዝህ አንተ ራስህ ያዝከኝ:: ግሩም ግጥም በግሩም እና ተወዳጅ ገጣሚ❤❤❤❤🌼🌼🌼
Show all...
ግጥም ዘእግዝትነ ቅድስት ድንግል ማርያም። (በከመ ጸሐፈ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ) ከመ ንስር ባቲ ክልዔ አክናፍ ዐበይተ:: ድንግልናቲሃ ክልዔቲ ይመስለኒ ሊተ:: በሕሊናሃ ወበሥጋሃ ኢገብረት ወኢምንተኒ ኃጢአተ:: አርዌ ሶበ ዴገና ተነጽሐ ታሕተ:: አምሰጠቶ በአክናፍ አመ ወለደት ወልደ ተባዕተ:: እስከ ገዳም ወመካን ሶበ ጎየት ግብተ:: አመ ትትዐቀብ በህየ ፲፻ወ፪፻ወ፺ ዕለታተ:: በከመ ይቤ ወልደ ነጎድጓድ ዘርእያ ትካተ:: ትክድንክሙ በአክናፊሃ ኩሎ ጊዜያተ:: ከመ ትኩንዋ ወትኩንክሙ ኅቢተ:: ማኅበርክሙ ኩሎ ትንሣእ አሥራተ:: ትዕቀብክሙ አእሩገ ወወራዙተ ወሕፃናተ:: ታእትት እምኔክሙ ሕማመ ወኀዘነ ወሞተ:: እምደወልክሙ ፄዋዌ ወኩናተ:: ምክያደ ዐውደ እክልክሙ ትምላእ በረከተ:: ትፌኑ ለረድኤትክሙ መላእክተ አእላፋተ:: ዘመነ ጽጌ 2015 ዓ.ም. ሥዕል:- ጣና ሐይቅ ዑራ ኪዳነምሕረት የቤተ መቅደስ     ሥዕለ ማርያም
Show all...
የታቦቱ ሌላ መጠሪያ የመሠዊያ ታቦት (ታቦተ ምሥዋዕ) የሚል ሲሆን ቅዱስ ጳውሎስ ስለዚህ መሠዊያ ‹‹መሠዊያ አለን በድንኳኒቱ የሚያገለግሉ ከእርሱ ሊበሉ መብት የላቸውም›› በማለት ስለ ሐዲስ ኪዳኑ መሠዊያ ይነግረናል፡፡ (ዕብ. 13፡10) ይህ መሠዊያ በኦሪት ድንኳን የሚያገለግሉ የአሮን ልጆች ከእርሱ ሊበሉ መብት የሌላቸው ለእኛ ክርስቲያኖች ብቻ በመሠዊያው ያለውን ሥጋና ደም እንድንበላ የተሠጠን ታቦተ ምሥዋዕ (Christian Alter) ነው፡፡ እነርሱ ቤተ እስራኤላውያን ነቢዩ እንደተናገረው "ከእንግዲህ አይሹትም የቃልኪዳኑ ታቦት ብለውም አይጠሩትም" ለእኛ ለአዲስ ኪዳን ልጆች ግን የተሠጠን የሥጋ ወደሙ ቃልኪዳን ነውና ዘላለማዊ ነው:: የታቦትን የሐዲስ ኪዳን አገልግሎት ስንናገር የሚቃወሙ ሰዎች ከሚያነሡት ተደጋጋሚ ትችት ‹‹አንዱ ታቦት ያላት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ናት›› የሚል ነጥሎ የመምታት ጥረት ነው፡፡ በተለይም የግብፅ ቤተ ክርስቲያንን በመጥቀስ ‹‹ግብፆች ታቦት የላቸውም›› የሚል ንግግር ይዘወተራል፡፡ ለዚህ ጉዳይ እኛ መልስ ከምንሠጥ የራሳቸው የግብፃውያንን ምላሽ ብቻ ማስቀመጥ ይቀልለናል፡፡ ግብፃውያን ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ጋር አቻ የሆኑ ሁለት ንዋያተ ቅድሳት አሏት፡፡ አንደኛው የመሠዊያው ጽላት (ሰሌዳ) /Alter Board/ ሲሆን ሁለተኛው ታቦት /Ark/ ነው፡፡ ቄስ ታድሮስ ማላቲ የተባሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ እውቅ ጸሐፊ ‹‹Church The House of God›› በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ስለ የመሠዊያው ሠሌዳ (Alter Board) አሠራር ሲናገሩ ‹‹ይህ የመሠዊያ ጽላት አንድ መስቀል ወይም ብዙ መስቀሎች ይሳሉበታል ፤ አልፋና ኦሜጋ ተብሎ ይጻፍበታል ፤ ከዚያም መዝ. 86፡1 ላይ ያለው መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው የሚለው የመዝሙረ ዳዊት ቃል ይጻፍበታል፡፡›› ይሉና ስለ አሠራሩ ሲናገሩ ‹‹የግብፅ ቤተ ክርስቲያን መሠዊያው ስለሚሠራበት ቁስ የተደነገገ ሕግ የላትም ፤ እስከ አራተኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ከእንጨት ብቻ ይሠራ ነበር፡፡ ከዕብነ በረድና ከድንጋይም ሊቀረጽ ይችላል፡፡›› ይህንን ካሉ በኋላም እግረ መንገዳቸውን ስለ ኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦተ ምሥዋዕ ሲናገሩ ‹‹ከእንጨት የሚሠራ ታቦተ ምሥዋዕ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መሥጠቱን ቀጥሏል›› (Wooden Alters continue in use in the Ethiopian Church at the present time) ብለው ያጠቃልላሉ፡፡ ይህ ስለ መሠዊያ እንጂ ስለ ታቦት አይናገርም፡፡ ስለ ታቦት ደግሞ እኚሁ ጸሐፊና በቤተ ክርስቲያኒቱ ኦፊሴላዊ ድረ ገጾች ላይ የሚከተለው ተጽፎአል፡፡ ‹‹In the middle of the Alter, there is a wooden box, called in Coptic 'pi totc' which means 'a seat' or 'a throne', and is used as a Chalice-Stand. Usually it is cubicle in shape, about thirty centimetres high and twenty-five centimetres wide, the top is closed with high flaps. The beautiful carving is inlaid with ebony and ivory and is decorated with four small icons. It can be only the Lord in the last supper, St Mary, Archangel Michael, St. Mark and then the patron Saints. It is called 'the Throne' for it represents the presence of the Crucified Lord. Its name also corresponds to the 'Ark of the Old Testament', for it contained the Tablets of Law written with the finger of God to declare God's covenant with man. The new Ark now contains the true Blood of Christ, as the New covenant, that fulfils the Law and the prophets.›› (‹‹ከመሠዊያው መካከል የሚቀመጥ የእንጨት ሳጥን ሲኖር ይህ በኮፕት ቲቶት ተብሎ የሚሠራ ሲሆን ትርጉሙም ‹መንበር› ወይም ዙፋን ማለት ነው፡፡ ጽዋው የሚቆመውም በዚህ ላይ ነው፡፡ ቅርጹ ክበባዊ ሲሆን 13/25 ሴንቲሜትር ነው፡፡ ከላይ በጨርቅ ይሸፈናል፡፡ በጥቁርና ነጭ ኽብረ ቀለማት ያጌጠ ሲሆን አራት ሥዕላት በዙሪያው ይደረጋሉ፡፡ ሥዕላቱ የጌታችን ጸሎተ ሐሙስ ሥዕል የእመቤታችን ፣ የቅዱስ ሚካኤልና የሚታሰበው ቅዱስ ሥዕላት ናቸው፡፡ ‹ዙፋን› ተብሎ የሚጠራው የተሰቀለው ጌታ እንደሚያድርበት በማሰብ ነው፡፡ ይህ ስያሜም ‹ከብሉይ ኪዳኑ ታቦት› ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ያ ታቦት እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያደረገው ቃልኪዳን የተጻፈባቸው የሕግ ጽላት ያሉበት ነበር፡፡ አሁን ያለው አዲሱ ታቦት ግን እውነተኛውን የክርስቶስ ደም የያዘ ሲሆን ክርስቶስም ሕግንና ነቢያትን ፈጽሞ አዲሱን ኪዳን የሠጠን ነው፡፡››) ይህ ማብራሪያ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ስለ እኛ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ከሠጡት ማብራሪያ ጋር ምንም አይለያይም፡፡ ይህን እንደ ማሳያ ጠቀስን እንጂ ታቦቱ ዑደት ባለማድረጉ እና በሥርዓቱ ይለያያል እንጂ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለሥጋ ወደሙ መሠዊያ ነው ብላ ከምታከብረው ታቦት ጋር በክብርና በአገልግሎት አቻ የሆኑ በቅብዐ ሜሮን የሚከብሩና በመንበር የሚቀመጡ ንዋያተ ቅድሳት በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት አሉ፡፡ ባለንበት ዘመን በሥጋ ወደሙ እውነተኛነት ከማያምኑ ሰዎች ጋር ስለ መሠዊያው አስፈላጊነት በመከራከር ብዙ ጊዜ ሲባክን ይታያል፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጻፈበትን ታቦት ‹ጣዖት› ነው የሚሉ ‹ክርስቲያኖች› እያየን እንደነቃለን፡፡ ‹‹ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይንበርከክ›› ተብሎ የተጻፈበት ‹ጣዖት› እንዴት ይኖራል? ‹‹አልፋና ኦሜጋ›› የሚል ጣዖት አለ? ወንጌል በላዩ ላይ የተቀመጠበት ፣ በቅብዐ ሜሮን የከበረ ፣ ሥጋ ወደሙ የሚፈተትበት ታቦት እንዴት ጣዖት ተብሎ ይጠራል? አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ተብሎ በሥላሴ ስም የሚቀደስበትን ታቦት ባዕድ አምልኮ ለማለት መድፈር እንዴት ያስደነግጣል፡፡ አንዳንዶች ‹ታቦት ተሰርቆ ተሸጠ› የሚሉ ዜናዎችን በማራገብ ታቦቱ ኃይል የለውም ሊሉን ይሞክራሉ፡፡ እንኳን የክርስቶስ ስም የተጻፈበት ታቦት ቀርቶ ራሱ ክርስቶስ በሠላሳ ብር ተሸጦ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ እየተተፋበት ፣ እየተደበደበ ተጎትቶ ተሰቅሎ የለምን? ክብር ይግባውና ኃይል የለውም ሊባል ይችላል? ‹‹ታቦቱን ገልጠን እናሳያለን›› ብለው እየፎከሩ ቤተ ክርስቲያንን ያዋረዱ የሚመስላቸው ፣ በታቦቱ እግዚአብሔርን የምታመልከውን ቤተ ክርስቲያን ታቦት ታመልካለች ብለው ያላለችውን በግድ ብላለች ብለው ድርቅ የሚሉ ሰዎች ስናይ ከማዘን ውጪ ምን እንላለን? ቤተ ክርስቲያን ታቦትን የምትሸፍነው ስለሚሠዋበት የጌታችን ሥጋና ደም ክብር እንጂ ቢገለጥ የምታፍርበት ነገር ኖሮ አይደለም፡፡ ቢገለጥ የሚታየው የመድኃኔዓለም ክርስቶስና የቅዱሳኑ ስም ነው፡፡ ጌታዋ ዕርቃኑን በመሰቀሉ ያላፈረች ቤተ ክርስቲያን ስሙ በተጻፈበት ታቦት አታፍርም! ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጥር 10 2009 ዓ ም
Show all...
+++ ታቦትና ኢየሱስ ክርስቶስ +++ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታቦታት ላይ የተጻፈው ምንድር ነው? ተብለው ቢጠየቁ መልስዎ ምን ይሆን? ‹ዐሥርቱ ትእዛዛት ተጽፈዋል› ካሉ መልስዎ ትክክል አይደለም፡፡ ትክክለኛውን መልስ ከመመልከታችን በፊት ጥቂት ነገሮች ስለ ታቦት እንመልከት፡፡ ብዙ ጊዜ ስለ ታቦት አስፈላጊነት በሚሠጡ ማብራሪያዎች ላይ ሰፊውን ቦታ የሚይዘው ስለ ብሉይ ኪዳን ታቦት የሚናገሩ ጥቅሶችን በመጥቀስ በመሆኑ ምክንያት ስለ ታቦት የሚነሡ ጥያቄዎች እንዳያቋርጡ ያደረገ ይመስላል፡፡ ስለዚህ በዚህች አጭር ጽሑፍ ‹ነገርን ከሥሩ› የሚለውን አካሔድ ሳንከተል በቀጥታ ስለ ሐዲስ ኪዳን ታቦት ብቻ እንመለከታለን፡፡ ታቦት በሐዲስ ኪዳን ለምን ያስፈልጋል? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ጌታችን በመጨረሻዋ ምሽት ሐሙስ ምሥጢረ ቁርባንን ባስተማረ ጊዜ ያደረገውን እናስታውስ፡፡ ጌታችን ሐዋርያቱ በተሰበሰቡበት ‹‹እንጀራውን አንሥቶ ባረከ ቆርሶም ሠጣቸው እንካችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ፡፡ ጽዋውንም አንሥቶ አመሰገነ እንካችሁ ጠጡ ይህ ስለብዙዎች የኃጢአት ይቅርታ የሚፈስሰው የሐዲስ ኪዳን ደሜ ነው አለ›› (ማቴ. 26፡26) ጌታችን አስቀድሞ ‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው›› ብሎ በትምህርት የመሠረተውን ምሥጢረ ቁርባን በተግባር ለሐዋርያቱ በዚህ መልኩ አስተማራቸው፡፡ (ዮሐ. 6፡56) ሐዋርያቱም ከጌታችን ዕርገት በኋላ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹እንጀራውን በመቁረስ ይተጉ ነበር›› (ሐዋ.2፡42) ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ከጌታ የተቀበልሁትን ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ ሠጥቻችኋለሁ›› በማለት ሥጋ ወደሙን እንዴት መቀበል እንደሚገባና ‹ሳይገባው የሚቀበል የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ›› እንዳለበት በማስተማር የቁርባንን ሥርዓት ደነገገ፡፡ (1ቆሮ. 11፡23-30) ልብ እንበል የክርስቶስ ሥጋና ደም መሠጠቱን የሚያምን አንድ ክርስቲያን ይህ የከበረ ሥጋና ደም እንደ ተራ ማዕድ በየቦታው ፣ በየጠረጴዛው ሊቀርብ ይችላል ብሎ ለማሰብ እጅግ ይከብደዋል፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ዘመነ ሰማዕታት አልፎ ስደትዋ እስካበቃበት ዘመን ድረስ በሒደት እየተሻሻለ በመጣ የቤተ መቅደስ ሥርዓት የሐዲስ ኪዳኑን መሥዋዕት በክብር ለመሠዋትና ለምእመናን ለማቀበል በቅታለች፡፡ የበግና የፍየል ደም ይሠዋ በነበረበት የኦሪት ዘመን እንኳን ለብቻው ትልቅ መሠዊያ ተዘጋጅቶ ፣ መሠዊያው ተቀድሶ ሰው በማይገባበት በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በክብር ተቀምጦ ነበር፡፡ በድንኳኒቱ ውስጥ የሚያገለግሉት አሮንና ልጆቹም የተለየ ልብስ ለብሰው የበጉን ደም በመሠዊያው ዙሪያ ባለው ቀርነ ምሥዋዕ (የመሠዊያ ቀንድ) ላይ እየቀቡ ሥርዓቱን ይፈጽሙ ነበር፡፡ ለበግና ለፍየል መሥዋዕት ይህ ሁሉ ክብር ከተሠጠ እንደ በግ ስለ ሁላችን ኃጢአት ራሱን መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበው የእግዚአብሔር በግ ፣ እንደ ሊቀ ካህናትነቱ እጁን በመስቀል ላይ ዘርግቶ የተሠዋውና ሥጋና ደሙን እንካችሁ ብሉ ብሎ የሠጠን የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም መሥዋዕት ሆኖ የሚቀርብበት መሠዊያ ምንኛ የከበረ ይሆን? የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሥጋ ወደሙ ‹መሠዊያ› የምትለው ታቦት በቅርጽም ፣ በአገልግሎትም ፣ በክብርም በኦሪት እግዚአብሔር ለሙሴ ከሠጠው ታቦት ጋር አንድ አይደለም፡፡ የቀደመው ታቦት በአራት ካህናት የሚያዝ በውስጡ ጽላት የሚቀመጥበት ሲሆን የአሁኑ ታቦት ግን የጽላት ቅርጽ ያለው ጽሌ (ሰሌዳ) ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ የሐዲስ ኪዳኑን ታቦት በሦስት ስያሜ ትጠራዋለች - የቃልኪዳኑ ታቦት ፣ ጽላት እና መሠዊያ ብላ፡፡ የቃልኪዳኑ ታቦት የሚባለው እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ስላደረገው ስለ ቀድሞ ቃልኪዳን ሳይሆን ‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው›› ተብሎ ስለተሠጠው እና ‹‹ስለብዙዎች የኃጢአት ይቅርታ የሚፈስሰው የሐዲስ ኪዳን ደሜ ነው›› ብሎ ጌታችን ስለ ሠጠን አዲሱ ኪዳን ነው፡፡ (ማቴ. 26፡26-30) የቃልኪዳኑ ታቦት የሚባለው በሥጋ ወደሙ ስለተሠጠን ሐዲስ ኪዳን ነው፡፡ ታቦት መባሉ ደግሞ እግዚአብሔር በረድኤት የሚያድርበት ፣ በሥጋ ወደሙ ደግሞ በአካል የሚገለጥበት ዙፋን ስለሆነ ነው፡፡ ጽላት (ሰሌዳ) የሚባለው ዐሠርቱ ትእዛዛት ተጽፈውበት አይደለም፡፡ የሕግ ሁሉ ፈጻሚ የሆነው የመድኃኔዓለም ክርስቶስ ‹‹አልፋና ኦሜጋ›› የሚለው የከበረ ስሙ በታቦቱ ላይ ስለተጻፈ ነው፡፡ (ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን /ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታዬ/ ፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ/) አንዳንድ ሰዎች ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ከኦሪቱ ጋር አይመሳሰልም!›› ብለው እንደ ትልቅ መከራከሪያ ሲያውጁ ማየት እጅግ ያስገርማል፡፡ አንዴ ‹ኦሪታዊት ነሽ› አንድ ጊዜ ደግሞ ‹‹ለምን እንደ ኦሪቱ አልሆንሽም›› ብሎ ንትርክ ግራ ያጋባል፡፡ የኦሪቱን ያልመሰለው አሁን ያለነው ሐዲስ ኪዳን ላይ ስለሆነና የታቦቱ አገልግሎት የተለየ ስለሆነ ነው፡፡ የሐዲስ ኪዳኑ ታቦ ት ከቀድሞው አንድ ታቦት ተለይቶ በቁጥር የበዛውም ለብዙዎች መድረስ ያለበት የክርስቶስ ሥጋና ደም የሚፈተትበት መሠዊያ ስለሆነ ነው፡፡ መድኃኒት ቤት የሚበዛው መድኃኒት የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሲበዙም አይደል? ታቦት የበዛው በታቦቱ የሚሠዋው መሥዋዕት ለብዙዎች ስለ ኃጢአት ይቅርታ የሚፈስሰውና ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻው ያለሱ ሕይወት የላችሁም የተባልነው ሥጋና ደሙ ለኃጢአት በሽተኞች ስለሚያስፈልገን ነው:: ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እንዲህ ሲሉ ያብራራሉ ‹‹የኦሪት ጽላት እግዚአብሔር በደመና ተከናንቦ ሙሴንና አሮንን የሚያነጋግርበት ለእስራኤል ብቻ በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡ ይህ ግን (የሐዲስ ኪዳኑ ታቦት) የአምላክ ሥጋና ደም የሚፈተትበት (ጌታችን) ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን የሚጠራበት የምሕረት ምሥዋዕ (መሠዊያ) ነው፡፡ ክብርና ስግደትም የሚደረግለት ለዚህ ነው፡፡›› (የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ገጽ 109) ሌላው አስገራሚ ነገር አቡነ ጎርጎርዮስ በታቦት ሥርዓት ከግሪኮች አንዲሚስዮን ጋር እንደምንመሳሰል ጠቅሰው ሲጽፉ ግሪኮቹ ደግሞ ስለ አንዲሚስዮን ሲያብራሩ ከኢትዮጵያ ታቦት ጋር የሚመሳሰል ብለው መጻፋቸው ነው። በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት በታቦታቱ ሁሉ ላይ የተጻፈው ‹‹አልፋና ኦሜጋ›› የሚለው የመድኃኔዓለም ክርስቶስ ስም ነው፡፡ ከስሙ ጋር ደግሞ በሁሉም ታቦታት ላይ የሚከተለው ጥቅስ በግእዝ ተጽፎአል፡፡ ‹‹ከመ ለስሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይስግድ ኲሉ ብርክ ዘበሰማያት ወዘበምድር›› ‹‹ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ›› የሚል ነው፡፡ (ፊልጵ. 2፡10) በታቦቱ ፊት የሚሰግድ ሰው ለምን እንደሚሰግድ በታቦቱ ላይ የሚጻፈው ይህ ጥቅስ ያስረዳናል፡፡ ምክንያቱ ‹‹ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይሰግዱ ዘንድ›› ስለሚገባ ነው፡፡ የክርስቶስ ሥጋ እንደሚቆረስ ደሙ እንደሚፈስስ የሚያምን ሰው በዚህ መሠዊያ ፊት በፍርሃት ለክርስቶስ ይሰግዳል፡፡ ሥጋ ወደሙን ‹‹ተራ መታሰቢያ ብቻ ነው›› የሚል ሰው ግን በመሠዊያው ፊት እንዲሰግድና መሠዊያውን እንዲያከብር አንጠብቅም፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በታቦቷ ጽፋ ክብር የምትሠጥ የሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ልጆች ስለሆንን እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፡፡
Show all...
"ቤተ ክርስቲያን የምትታገሰው እንደ ሀገር ስለምታስብ ነው።" ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጥቷል። መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቋሚና ጊዜያዊ ፕሮጀክት መምሪያ ኃላፊ ከደቂቃዎች በፊት በጠቅላይ ቤተ ክህነት ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል። መልአከ ሕይወት በመግለጫቸው ኢትዮጵያንና ቤተ ክርስቲያንን ለይቶ ማየት እስከማይቻል ድረስ ቤተ ክርስቲያን አበርክቶዋ እጅግ ትልቅ እንደነበር አስታውሰዋል። በሀገራዊና በልማት ጉዳይ ላይም ከሌሎች በኢትዮጵያ ካሉት የሀይማኖት ተቋማት ጋርም እጅና ጓንት ሆና እየሠራች ትገኛለች ብለዋል። ነገር ግን አሁን አሁን ላይ የሚታየውና የሚነገረው ክብረ ነክ ነገር ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን አይገባትም። በሃይማኖት ሽፋን የሚደረገው ሕገወጥ ድርጊት እጅግ የሚያሳዝን ነው ሲሉ አክለዋል። ተአምረ ማርያም ቤተ ክርስቲያናዊ መሠረት ያለው መጽሐፍ ነው። ሰሞኑን በመጽሐፉ ዙሪያ የተሰጠው ትችት ተገቢ ያልሆነና በሕግ የሚያስጠይቅ ነው ብለዋል። እየጠፋን ዝም ብለን የምንታገስ አይሆንም። ቤተ ክርስቲያን ትዕግሥት የምታበዛው መልስ መስጠት አቅቷት ሳይሆን የምትታገሰው እንደ ሀገር ስለምታስብ ነው። በመሆኑም እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል። በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አንዱ የአንዱን ሃይማኖት እያከበረ እንዲኖር ሕግ ያለ ቢሆንም ቤተክርስቲያን የማንንም ድንበር አላፋ ባልሄደችበት ሁኔታ የቤተክርስቲያንን ድንበር አለፈው ለሚመጡ አካላት ተቋሙ ሊጠይቃቸው ይገባል ብለዋል። ቤተ ክርስቲያን ሚዛናዊ ሥራ እየሠራችና ሌሎቹን እያከበረች ባለችበት ሁኔታ በሀይማኖት ካባ ተደብቀው ሰላም ሲሆን የማይወዱ አካላት ቤተ ክርስቲያንን የማይገባት ስም እየሠጡ ይገኛሉ። ይህ አግባብም የሚያዛልቅም አይደለም ብለዋል። እኛ ሌላውን አልነካንም ሌላው ለምን ይነካናል? ቤተ ክርስቲያን የማንም ሥጋት ሆና አታውቅም ሌሎች ሲነሱባት ግን መንግሥት ዝም ማለት የለበትም ሲሉም ነው ያሳሰቡት። የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአስቸኳይ ተሰብስቦ ጉዳዩን እንደሚያወግዝና እልባት እንደሚሰጥ እንጠብቃለን ሲሉ ተናግረዋል። ሕዳር 26 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
Show all...