cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

photo stayl ውድድርⓂ

📸ተለቅ የምስራች ይዘን ከች ብለነል ፎቶ ማወዳደር ስንጀምር በታላቅ ደስታ ነው። ከ ትናንሽ እስከ ትላልቅ ከ ጥቁር እስከ ቀይ ከ ሴት እስ ወንድ ሁሉንም የሚያካትት ታላቅ የ ሳምንት ውድድር ፎቶ ለመላክ @photo533 for spam @p2oto*2** For any equation ✍️ @photo533 ✍️

Show more
EthiopiaAmharicThe category is not specified
Advertising posts
819Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሰዎች እንዴት ናችሁልኝ🥰ጠፍሁ አይደል ይቅርታ ወደ ድሮው አቋማችን በቅርቡ እንመለሳለን ውድድርና ጥያቄ መልሳችንን እንጀምራለን ነቃ ነቃ በሉ ለሰውሞ ሼር አርጉ🙏
Show all...
የህዝብ ስቃይ‼ << መንደሮች በእሳት እየተለኮሱ ነው!… ንፁሐን እየተገደሉ ነው!…» አሁን፦ የወርቄ መንደሮች በእሳት እየጋዩ ነው!… 024 ወርቄ ድቡቡቲ፣ አብሆይ፣ ጎቢሳ አሁን በወያኔ ጁንታ የሽብር ቡድን ተለኩሰዋል… 023 ወርቄ ኤርባና አባ ገለቢ… አሁን እየነደዱ ነው… በርካታ ህዝብ ተገለዋል… ህዝቡ ተንገላቷል… ማርማርቲ የሚባል ቦታ ላይ አቶ መሀመድ ፈንታ ከሰባት አመት ልጁ ጋር ተመቶ ወድቋል… በርካታ የአርሶ አደሩ ከብቶች እየተነዱ ነው። ውረኔ… የከብቶች ማሳማሪያ "ቆማ" ከሁለት መቶ ከብቶች በላይ… ጮቢ በሚባል ቦታ ከመቶ ዘጠና በላይ… ከብት 023 ወርቄ ፍየልና ግመል ነድተዋል… "አማራ_አሻ" እና "ከኖ_ጎላ" ከሁለት መቶ በላይ ከብቶች ፍየልና ግመል ነድተዋል!… በተመሳሳይ በራያ ቆቦ ወረዳ አርበት ላይ የጥላት ኃይል በጣም ተከማችቶ ስላለ፤ ከፍተኛ ውድመት እያደረሰ ነው!… የነዋሪውን ከብትና ፍየል እያረደ እየተመገበ ነው!… እሮቢት!… ጎብዬ እና ቆቦም ተመሳሳይ ነው!… ወንዱ መሳሪያ አምጣ!… ሴቱን ስንቅ ሰንቁ እያለ ጥላት እያስገደደ ነው!!!… በመጨረሻ መረጃ ሰጭዎቼ ያስተላለፉት መልዕክት «መንግስት! ካለ በአስቸኳይ ይድረስልን!…» ብለዋል!… ህዝብ ከዚህ በላይ መሰቃየት የለበትም! ሁላችንም የራያ ህዝብ ጥቃት ተሰምቶን በጋራ ልንቆም ይገባልና!… ጥላትን በጋራ እንመክት>> ቴዎድሮስ አያሌው
Show all...
አስቸኳይ ነው‼…ሼር አድርጉላቸው በአማራ ክልል በቅርቡ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት!  የ2014/2015 ዓ.ም በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ፈተናው እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ተፈታኝ ተማሪዎች ቀድመው ሊዘጋጁባቸው  የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡ 1.  ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ማዕከልም ይሁን በመፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ መገኘት ግዴታ በመሆኑ አድሚሽን ካርድ ፎርም ከሞሉበት  ትምህርት ቤት እና ወረዳ በአካል በመገኘት እስከ መስከረም 10/2015 ዓ.ም እንዲረከቡ፡፡ 2.   በአድሚሽን ካርዱ ላይ የስም፣ የስትሪም እና የጾታ ወዘተ..ስህተት ካለ በአስቸኳይ ለትምህርት ቤቱ እና ለወረዳው ሪፖርት እንድታደርጉ በጥብቅ እያሳሰብን ይህንን የማያደርጉ ተማሪዎች ካሉ ፈተና ለመውሰድ እንደሚቸገሩ፤ 3.  ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ የትምህርት ቤት ወይም የኗሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት የሚገባ መሆኑ፤ 4.  ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ጊዜ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ  ይዘው መገኘት ያለባቸው መሆኑ ከዚህ ዉጭ ሌሎች ቁሳቁሶችን በዩኒቨርሲቲ ግቢ እና በመፈተኛ ክፍል መያዝ የተከለከለ መሆኑ፤ 5.  ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ፣ ወረዳው እና ዞኑ በሚያዘጋጀው የጉዞ ፕሮግራም መሰረት ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ መሆኑን በመረዳት ዝግጅት ማድረግ ያለባቸው መሆኑን፤ 6.  ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲሄድ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ልብስ ይዞ የመምጣት ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን መረጃ ሸር በማድረግ ለተማሪዎችና ተማሪ ወላጆች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርስ ትብብራችሁን እንድታደርጉ በተፈታኝ ተማሪዎች ስም ቢሮው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
Show all...
ህውሃት በሁለተኛው ዙር ወረራ የመጀመሪያ መዳረሻ ደሴ በመቀጠል ምዕራብ አቅጣጫ ጉጉፍቶ ፣ወረኢሉ፣ጃማ መርሃቤቴ፣አድርጎ ሱሉልታና አዲስ አበባ የመድረስ ዕቅድ ይዞ እንደተነሳ ከምርኮኞች ኪስ የተገኘው ማስታወሻ ያመለክታል።
Show all...
✔ዛሬ በዘመን መለወጫ አውደ ዓመቱ ሰሜን ወሎ ዙሪያውን ከ50 በላይ ሰርጎ ገቦች መያዛቸው ተሰምቷል። ✔ዛሬ በየትኛውም ግንባር የጮኸ ጥይት አለመኖሩ ታውቋል። ✔ትናንት ምሽት በአልውሃ አካባቢ ተሰባስቦ የመጣው የህውሃት ታጣቂ በሠዓቱ በተወሰደ እርምጃ ነገሮች ተስተካክለዋል ሲሉ የመረጃ ምንጮቼ ነግረውኛል።
Show all...
ዛሬ በየትኛውም ግንባር ይሄነው የሚባል ውጊያ አልተካሄደም።ሠላም ምርጫችን ነው።2015 የመሳሪያ ድምፅ የማንሰማበት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን።ነገር ግን ህውሃት ይህንን ፈላጊ አይመስለኝ።ዛሬ ጳጉሜ 5 ቀን 2014 ከሰአት በኋላ ጀምሮ ተጨማሪ ወራሪ ኃይሉን ከመቀሌ ወደ አለማጣ እያስገባ ነው።ከተንቤ፣ደደቢት፣ሽሬና አዲግራት ሲተኮስበት በራያ ግንባር ማጥቃትን መምረጡ ታውቋል።
Show all...
ራያ ግንባር ✔ወልዲያ ከተማ ሰፈር ተቀምጦ ትናንት ጥይት ሲተኩስ የነበረው ሁሉ በመንደር ወሬ ነው።ውጊያው አሁንም ጎብዬና ሮቢት እየተካሄደ ይገኛል። ✔አልውሃ፣ወርቄ፣እና ጉራ ወርቄ ዛሬም ጦርነት አለ። ✔ተኩለሽ፣መሀጎና ቃሊም አቅራቢያ ውጊያ እየተካሄደ ነው። ያለው እውነታ ይህንን ይመስላል።
Show all...
የጨነቀ ነገር ህውሃት በመቀሌና አከባቢው የሰዓት እላፊ ገድብ ጥሏል።ከ12:00 በኋላ መንቀሳቀስ አይቻልም።ከመቀሌ ከተማ የእርዳታ ድንኳኖችን አፍርሷል።
Show all...
በአዲስ አመት ዋዜማ እንደዚህ ስራ ይበዛብሻል ብዬ አስቤ አላውቅም😄 ለማንኛውም ጎብዬንና ሮበትን አስመልሳለች።
Show all...
ህወሃት ትናንት ከጎብዬ የተወሰነ ሀይል በየተራራው በመተው ሌላውን ወደ ቆቦ ከወሰደ በኋላ ለሊቱን ተቀያሪ ሀይል በማስጠጋት አሁንም በላጎ እንዲሁም በአላውሃ በኩል ውጊያው እንደቀጠለ እና የከባድ መሳሪያ ተኩስ እንደሚሰማ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጭምር መረጃ ለመሰብሰብ ችያለሁ። ጥምር ጦሩ በራያ ግንባር ትንቅንቅ ላይ ነው። ©አዩ ዘሀበሻ
Show all...