cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ABENEZER Solomon

Singer

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
163Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አብልቸው ልሙት “በሰው ልብ ውስጥ ራእይ ብቻ ሊሞላው የሚችል ባዶነት አለ” በአንዲት ከተማ ውስጥ አንድ ከቤተሰቦቹ ኃብትን የወረሰ ባለጠጋ እንደነበረ ይነገራል፡፡ ይህ ሰው የፈለገውን ያህል ወጪ በፈለገው ጊዜ ለማውጣት የሚያስችለው በቂ ገንዘብ ነበረው፡፡ ጥሩ ቤት፣ ጥሩ መኪናና የተሟላ ሁኔታ ነበረው፡፡ በዚህ ምቹ ሕይወት ብዙ አመታትን ኖሯል፡፡ ሆኖም ኑሮ የሕይወት ድግግሞሽ አዙሪት ሆኖበታል፡፡ ይበላል፣ ይጠጣል፣ ከወዳጆቹ ጋር ይጫወታል፣ እቤቱ ይገባል፣ ይተኛል፣ እንደገና ደግሞ ጠዋት ይነሳል፡፡ የሚቀጥለውም ቀን ያንኑ ይደጋግመዋል፡፡ ከቁጥር በላይ ጓደኞች አሉት፡፡ ሰውየው ይህ የኑሮ ዑደት ሰለቸውና ወደ ግራ መጋባት መጣ፡፡ የስሜት ቀውሱ ሲበዛበት አንድ ቀን፣ “ራሴን አጠፋለሁ” ብሎ ተነሳ፡፡ ራሱን በምን መልክ ሊያጠፋ እንደሚችል ሲያስብ በአካባቢው ያለ አንድ ትልቅ ድልድይ እንዳለ ትዝ አለው፡፡ ወደዚያ ድልድይ ሄዶ ራሱን በመጣል ራሱን ሊያጠፋ መንገድ ጀመረ፡፡ የሚያስፈራ ከፍታ ባለው በዚያ ድልድይ ጫፍ ላይ ቆሞ ራሱን ሊጥል ሲዘጋጅ በድንገት አንድ ድምጽ ሃሳቡን ሰረቀው፡፡ የሚያሳዝን የሕጻን ልጅ ድምጽ ነው፡፡ ዘወር ብሎ ሲመለከት አንድ ህጻን ተመለከተ፡፡ ይህ ሕጻን እርቦት በጣም ከስቷል፡፡ እዚያ ድልድይ ጋር ማን ትቶት እንደሄደ አይታወቅም፡፡ ይህ ራሱን ሊያጠፋ የነበረ ሰው ይህንን ሕጻን ጠጋ ብሎ ሲያየው ከረሃብ የተነሳ መገርጣቱን ተመለከተና በጣም አዘነለት፡፡ በልቡም እንዲህ ሲል አሰበ፣ “ይህንን የከሳ ሕጻን አንድ ቀን እንኳን አብልቸው ልሙት”፡፡ ስለዚህም፣ ራሱን የማጥፋት ቀጠሮውን ለበኋላ አስተላለፈው፡፡ ሕጻኑን አቅፎ አነሳውና ወስዶ ካጠበው፣ በደንብ ካበላውና ካጠጣው በኋላ ራሱን ወደማጥፋት እቅዱ ለመመለስ መንገድ ቀጠለ፡፡ በመንገድ ላይ ሲሄድ ግን የዚህ ሕጻን ሁኔታ ከአይኑ አልለይ አለው፡፡ ደግሞ እንዲህ ሲል አሰበ፣ “እኔ ከሞትኩ በኋላ ይህንን ህጻን ማን ሊያበላው ነው? ገና በአንድ ቀን ምግብ ፊቱ መለስ ብሏል”፡፡ ይህንን ካሰበ በኋላ ስላላስቻለው ህጻኑን ትቶ ወደመጣበት አካባቢ በመመለስ እንደገና ሊያበላው ወሰደው፡፡ ሌላ ቀን ጨመረለት፡፡ እንደገናም ሌላ ቀን አበላው፡፡ እንዲህ እያለ ለጥቂት ቀናት ካበላው በኋላ ልጁን ሲያየው ነፍሱ ተመልሳለች፡፡ አሁን ይሄ ባለጠጋ ተመልሶ ራሱን ስለማጥፋት ማሰብ ሲጀምር የዚህ ልጅ የወደፊት ሕይወት ይታየው ጀመረ፡፡ ይህ ልጅ አድጎ ጥሩ ደረጃ ላይ ሲደርስ ለማየት መናፈቅ ጀመረ፡፡ ለመኖር ጓጓ፤ የሚኖርለት ትርጉም አግኝቷልና፡፡ ከዚያም በኋላ ዳግም ራስን ስለማጥፋት አስቦም አያውቅ፡፡ ሰው የሚከስረው ንግድ አልሳካ ሲለው አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው ብቸኝነት የሚሰማ ብቻውን ሲሆን አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው ዝቅተኝነት የሚሰማው ከሌሎች ስላነሰ አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው ወዲ ወዲያ የሚንከራተተው መንገዱ ሲጠፋው አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው በማይመለሱ ጥያቄዎች የሚሞላው መልስ ሲያጣ አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው … ሰው ስራ የሚያጣው ስራ ሲጠፋ አይደለም፣ ራእይ ሲያጣ ነው @Abenada
Show all...
ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዩርጊስ ━━━━━━━━━━━━ ➠ TITLE: "አንተን ሳስብ" ➠ GENRE: New Worship ➠ Quality: mp3 ➠ SIZE: 3.8 MB ➠ TIME: 4:05 ➠ CHANNEL : @marsilchannel ━━━━━━━━━━ ➠share link:t.me//marsilchannel
Show all...
🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶 Bemengede lay
Show all...
ቆጠርከኝ እንደ ባለማዕረግ ሳለፋ ምንም ሳላደርግ ምህረትህ በዝቶልኝ በላዬ አረ ደግ እኮ ነህ ጌታዬ ልናገር እኔስ ቸርነትህን አላውቅም ክፉ መሆንህን @Abenada
Show all...
እግዚአብሔርን መውደድ
Show all...
Show all...
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤 @Abenada
Show all...
🎙🎙🎙🎙🎙 GoleGota
Show all...
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤 @Abenada
Show all...
ABENEZER
Show all...
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤 @Abenada
Show all...
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤 @Abenada
Show all...
😇የሚባርክ መዝሙር 🎤ዘማሪት አሜን (Ami) 🎼ገበተህ በማንነቴ 🗝Single song🗝 @Abenada
Show all...
" የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። " (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4:17-18) @Abenada
Show all...
Show all...
Amen. 🎙🎙🎙🎙🎙🎙🎙🎙 Tebarekilen 🙏🙏🙏🙏🙏🙏 @Abenada
Show all...
#አንተ_ማለት_ለእኔ...... #እየሱስ በፍቅርህ ነፍሴን የማራካት፤ በመስቀል ሞት በጣር የወለድካት፤ የሃጢአት እረግማኔን ወስደህ ከእኔ፤ የዘላለም ህይወት ወራሽ፣ብለህ የጠራሀኝ ልጄ፤ የገዛሀኝ በደም ፣መገረዝን ያየው በመንፈስህ፤ #እየሱስ አንተማ ለእኔ የደም ሙሽራዬ ነህ ፥ እኔም የአንተ ሙሽራ ፥ልገኝ ናፍቅያለው በበጉ ሰርግ ላይ ፤ ሆኜልህ ያለነውር ያለነቀፋ ከአንተ ውጪ ወደ ሌላ ሳላይ፤ ጠበቅህላው ዳግም እስክትመጣ በክብር በግርማ፤ እያልኩኝ ማራናታ ማራናታ ጌታ እየሱሴ ቶሎ ቶሎ ና!!! ራእይ 19 ⁶... ሃሌ ሉያ፤ ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላካችን ነግሦአልና። ⁷ የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሚስቱም ራስዋን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን ሐሤትም እናድርግ ክብርንም ለእርሱ እናቅርብ። . . “አክሊልን እንደ ለበሰ ሙሽራ፥ በጌጥ ሽልማትዋም እንዳጌጠች ሙሽራ፥ የማዳንን ልብስ አልብሶኛልና፥ የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛልና በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፥ ነፍሴም በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች።” — ኢሳይያስ 61፥10 “ሲፓራም ሚስቱ ባልጩት ወሰደች፥ የልጅዋንም ሸለፈት ገረዘች፥ ወደ እግሩም ጣለችው፤ አንተ ለእኔ የደም ሙሽራ ነህ አለች።” — ዘጸአት 4፥25 #አንተ_ማለት_ለእኔ...... #እየሱስ በፍቅርህ ነፍሴን የማራካት፤ በመስቀል ሞት በጣር የወለድካት፤ የሃጢአት እረግማኔን ወስደህ ከእኔ፤ የዘላለም ህይወት ወራሽ፣ብለህ የጠራሀኝ ልጄ፤ የገዛሀኝ በደም ፣መገረዝን ያየው በመንፈስህ፤ #እየሱስ አንተማ ለእኔ የደም ሙሽራዬ ነህ ፥ እኔም የአንተ ሙሽራ ፥ልገኝ ናፍቅያለው በበጉ ሰርግ ላይ ፤ ሆኜልህ ያለነውር ያለነቀፋ ከአንተ ውጪ ወደ ሌላ ሳላይ፤ ጠበቅህላው ዳግም እስክትመጣ በክብር በግርማ፤ እያልኩኝ ማራናታ ማራናታ ጌታ እየሱሴ ቶሎ ቶሎ ና!!! ራእይ 19 ⁶... ሃሌ ሉያ፤ ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላካችን ነግሦአልና። ⁷ የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሚስቱም ራስዋን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን ሐሤትም እናድርግ ክብርንም ለእርሱ እናቅርብ። . . “አክሊልን እንደ ለበሰ ሙሽራ፥ በጌጥ ሽልማትዋም እንዳጌጠች ሙሽራ፥ የማዳንን ልብስ አልብሶኛልና፥ የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛልና በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፥ ነፍሴም በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች።” — ኢሳይያስ 61፥10 “ሲፓራም ሚስቱ ባልጩት ወሰደች፥ የልጅዋንም ሸለፈት ገረዘች፥ ወደ እግሩም ጣለችው፤ አንተ ለእኔ የደም ሙሽራ ነህ አለች።” — ዘጸአት 4፥25 @Abenada/ 🎙🎙🎙🎙🎙
Show all...
@Abenada 🎙🎙🎙🎙🎙
Show all...
@Abenada/ 🎙🎙🎙🎙🎙
Show all...
Mengd ena zemara🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶
Show all...
Mesgi bro tebarekelegn 🎙🎙🎙🎙🎙🎙🎙🎙
Show all...
Aneten Becha ABENEZER solomon 🙏🙏🙏 @Abenada/
Show all...
Show all...
✝ #የሕይወት_ብርሃን #አንብባቹ_ስትጨርሱ_ሼር_በማድረግ_ለሌሎች_ያጋሩ። #ፍጥረት ሁሉ ህያው የሆነው በእግዚአብሔር ህይወት ነው። ከእግዚአብሔር የተገኘችው ህይወትም፥ ለሰው ልጆች ሁሉ የምታበራ ብርሀን ናት።(ዮሐ 1:4) ይህችም በጨለማ ውስጥ የምታበራ ብርሀን ምንም አይነት የጨለማ ሀይል አያሸንፋትም።(ዮሐ 1:5) #እግዚአብሔር ብርሀን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ የለም። (1 ዮሐ1:5) እግዚአብሔር የእኛን ጨለማ ሊያስወግድ በስጋ ተገለጠ። " ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር።" (የዮሐንስ ወንጌል 1:9) #በስጋ የተገለጠው አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ብርሀን ነው። እርሱ የእኛን የጨለማ ስራ የሆነውን ሀጥያት በደሙ አስወግዶ ከእርሱ እና ከአባቱ ጋር ህብረት እንዲኖረን አድርጓል። " ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:3) #አሁን በኢየሱስ የቤዛነት ስራ አማካኝነት ከአምላክ ጋር ህብረት አለን። ስለዚህም በፊት በጨለማ እንመላለስ የነበርነው አሁን ብርሀን በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነን በብርሀን እንመላለሳለን። " ደግሞም ኢየሱስ። እኔ የዓለምብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት_ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።" (የዮሐንስ ወንጌል 8:12) #የህይወት ብርሀን ይሆንልናል ማለት በብርሀን መኖር ወይም ከጨለማ ስልጣን ማምለጥ / በጨለማ ያለመመላለስ ወይም በብርሀን መመላለስ ማለት ነው። #ማንኛውም ሰው ኢየሱስን አምናለው የሚል ከጨለማ ስልጣን ማምለጡን እና ሀጥያትን ወደሚፀየፍበት ማንነት መሸጋገሩን ማረጋገጥ አለበት። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት አለኝ የሚል ነገር ግን በጨለማ የሚመላለስ ሰው ውሸታም ነው እውነትም በእርሱ የለም። " ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን ብንል በጨለማም ብንመላለስ እንዋሻለን እውነትንም አናደርግም፤" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:6) #ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ያለው በብርሀን ይመላለሳል እንጂ በጨለማ አይመላለስም። " ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥(1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:7) የዛሬው መልዕክት ነው ለወዳጅዎ 💝 #ሼር 💝
Show all...