cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

NOTHING ...💞

Advertising posts
497Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ቅናሽ ካለማ… አዲሱን የአቢሲንያ ባንክ አፖሎ የዲጂታል መተግበርያ ሲጠቀሙ በሲኒማ ትኬት፥ በምግብ እና መጠጥ ትዕዛዝዎ ላይ ቅናሽ ያገኛሉ። አፖሎን አውርደው ዛሬውኑ ይጠቀሙ። መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ። https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo #Apollo #OurNewProduct #DigitalEthiopia #Ethiopia #technology #innovation #digital #BankofAbyssinia #DigitalEthiopia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all #Apollodigitalproduct, #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank, #poweredbybankofabyssinia, #thechoiceforall
Show all...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ተፈትኖ የወደቀው ፌስቡክ ❌ ፌስቡክ ፤ በኢትዮጵያ ሶስት ብሔሮች ላይ ያነጣጠሩ #የጥላቻ_ንግግሮች ያዘሉ ማስታወቂያዎች ይለይ እንደሆነ የተሰጠውን ፈተና መውደቁ ተሰምቷል። ፌስቡክን የሙከራ ማስታወቂያዎችን በመጠቀም የፈተኑት " ግሎባል ዊትነስ " እና " ፎክስ ግሎቭ " የተባሉ ሁለት ተቋማት ከቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት መምህር ዳግም አፈወርቅ ጋር በመተባበር ነው።  ምርመራው የተከናወነው የፌስቡክ የጥላቻ ንግግር መለያ ምን ያህል ጥሩ እንደሆነ ለመፈተን እና የኩባንያው የደህንነት መቆጣጠሪያ ስልቶች ሁከት የሚያባብሱ ማስታወቂያዎችን መከላከል ይችል እንደሁ ለመፈተሽ ነበር። በአማርኛ ቋንቋ በፌስቡክ የተጻፉ 12 የከፉ የጥላቻ ንግግሮችን የለዩት ምርመራ አድራጊዎቹ እነዚሁኑ ይዘቶች ለኩባንያው እንደ ማስታወቂያ በማቅረብ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴው ለመለጠፍ ይፈቅድላቸው እንደሁ ሙከራ አድርገዋል። የኩባንያውን የቁጥጥር አቅም ለመፈተሽ በምሳሌነት የተመረጡት የጥላቻ ንግግሮች የተካተቱባቸው ማስታወቂያዎች፤ የአማራ፣ የትግራይ እና የኦሮሞ ብሔሮች ላይ እኩል ያነጣጠሩ ናቸው። በማስታወቂያዎቹ አረፍተ ነገሮች መካከል " ሰዎች እንዲገደሉ፣ እንዲራቡ ወይም ከአንድ አካባቢ እንዲጠፉ በቀጥታ ጥሪ የሚያደርጉ፤ ሰዎችን ከእንስሳት ጋር የሚያነጻጽሩ እና ሰብዓዊነት የጎደላቸው” ገለጻዎች እንዳሉበት ተገልጿል። አብዛኞቹ የማስታወቂያዎቹ ይዘቶች የዘር ማጥፋት እንዲፈጸም ጥሪ የሚያቀርቡ መሆናቸውም ተገልጿል። ከእነርሱ ውስጥ አንዳቸውም ለመተርጎም ውስብስብ እንዳልነበሩ ተመላክቷል። ግሎባል ዊትነስ ፤ " የትኞቹንም ማስታወቂያዎች አላተምናቸውም። የሚታተሙበትን ቀን ወደ ፊት እንዲሆን በማድረግ፤ ፌስቡክ ማስታወቂያዎቹን መቀበል እና አለመቀበሉን ካሳወቀን በኋላ አጥፍተናቸዋል " ብሏል። የጥላቻ ንግግሮቹ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴው ለህዝብ ይፋ አለመደረጋቸውን አረጋግጧል። በምርመራው መሰረት ፌስቡክ የቀረበሉትን 12ቱንም የጥላቻ ንግግሮች በማስታወቂያ መልክ በገጹ እንዲቀርቡ ፈቃድ ሰጥቷል። ሁሉም ማስታወቂያዎች ፌስቡክ በአጠቃቀም መመሪያው (community standards) የጥላቻ ንግግር ብሎ ከሚበይናቸው ውስጥ የሚካተቱ ናቸው። በሙከራ ደረጃ ፌስቡክ የተፈተነባቸው ማስታወቂያዎች በማህበራዊ መገናኛ ዘዴው ላይ ለዕይታ ቢበቁ ኖሮ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ከ57 አመታት በፊት የጸደቀውን ስምምነት የሚጥሱ ነበሩ። ስምምነቱ ማናቸውም አይነት የዘር መድሎዎ ለማስወገድ የጸደቀ ነው።   በድርጅቶቹ ምርመራ የተገኘው ውጤት በስተመጨረሻ የቀረበለት ፌስ ቡክ፤ ማስታወቂያዎቹ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴው እንዲታተሙ መፈቀድ እንዳልነበረበት ማመኑን ግሎባል ዊትነስ አሳውቋል። ፌስቡክ ለኢትዮጵያ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች የደህንነት ቁጥጥሩን ለማጥበቅ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን መግለጹንም ምርመራውን ካከናወኑት ድርጅቶች አንዱ የሆነው ግሎባል ዊትነስ አመልክቷል። Credit - www.ethiopiainsider.com @tikvahethiopia
Show all...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳና አካባቢው ተፈናቅለው የነበሩ የህበረተሰብ ክፍሎች ወደ ቀያቸዉ ተመለሱ። በምዕራብ ጎንደር ዞን አዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ነጋዴ - ባህር ከተማ በወቅታዊ የፀጥታ ችግር ምክንያት ተፈናቅለው አይከልና ሰራባ ጊዜያዊ መጠለያ የነበሩ የህበረተሰብ ክፍሎች ዛሬ ወደ ቀያቸዉ ተመልሰዋል። ከአካባቢያቸው ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች ነጋዴ - ባህር ከተማ ሲደርሱ የነጋዴ ባህር ከተማ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ደማቅ አቀባበል እንዳደረገላቸው ተገልጿል። Photo Credit : ጭልጋ ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia
Show all...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
🫂 ከጭልጋና አካባቢው ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች ወደ ቦታቸው እየተመለሱ ይገኛሉ። በጭልጋና አካባቢዋ ተፈናቅለው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሠራ እንደሚገኝ ተነግሯል። ከትላንት አንስቶ ከአይከል እና በዙሪያዋ ተፈናቅለው የነበሩ 11 ሺህ 938 የህበረተሰብ ክፍሎች ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ ሲሆን ወደ አይከል ከተማ ሲገቡ ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ ተቀብሏቸዋል። ተፈናቃዮቹ ከዚህ በፊት በአይከል ከተማና በአካባቢዋ ይኖሩ የነበረ ሲሆን ከማንነት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቦታቸው ተፈናቅለው በተለያዬ ቦታ ነበሩ። አሁን ላይ በተፈጠረው አንፃራዊ ሰላም ከትላንት አንስቶ ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሯል። ፎቶ ፦ የጭልጋ ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia
Show all...
ለተቃውሟችን ለከት ካላበጀን ሀገራችንን እንጎዳለን! ዶ/ር ዐቢይ ፋኖን ሊያፈርስ ነው እያሉ ሲያደነቁሩን የነበሩ አሉባልታውያን ዛሬ መንግሥት ፋኖን እውቅና ሰጥቶ በሽልማት ሲያምበሸብሽ ምን ይሉ ይሆን? #ሰላም_ለሰው_ዘር_በሙሉ #ኢትዮጵያ #Ethiopia
Show all...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " የታላቁ ህዳሴ ግድብ 3ኛውን የውሃ ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ ነው ፤ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ በትኩረት እየተሰራ ነው " - ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ የመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ ፥ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው የምትገኘው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ያለምንም ፀጥታ ችግር እንዲከናወን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ሌ/ጀኔራል ደስታ " ሠራዊቱ የተሠጠውን ተልኮ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት መፈፀም በመቻሉ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ ግብአቶች በሰላም ተጓጉዘው እንዲደርሱ እና ሰራተኞችም ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ማድረግ ተችሏል " ብለዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ #3ኛውን_የውሃ_ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ሌ/ጀኔራሉ " የግድቡ ግንባታ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ በትኩረት እየሰራ ነው " ብለዋል። አክለውም " የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ ዕድገታችንን ለማደናቀፍ #ከሱዳን ሰርገው የሚገቡ ኃይሎችን እየተከታተለ ሴራቸውን እያከሽፈው ይገኛል ፤ በቀጣይም ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ሲቪል አመራሮች ጋር ተቀናጅቶ ግዳጁን በአስተማማኝ ለመወጣት ዝግጁነቱ የላቀ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። #FDRE_Defense_Force🇪🇹 ፎቶ ፦ ፋይል @tikvahethiopia
Show all...
የምድራችን አስፈሪው ጦር ናዚን ቀጥቅጦ ያሸነፈበትን 77ተኛ አመት በድምቀት አክብሯል። አስርሺ ወታደሮች በተገኙበት በቀዩ አደባባይ የተከበረው የድል ቀን በአሉ ፕሬዳንታቸው ቭላድሜር ፑቲን ነፃነትን ለሚሹ ጭቁን ህዝቦችና ለሩሲያ ወዳጆች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ናዚን አርካሪውን ሰብረው ያሸነፉት የቀድሞው የሶቬት ሕብረት አባል ሀገሮች ተወካይዎቻቸውን ወደ መስኮ መላካቸውን ሩሲያ 29 የዜና አውታር ዘግቧል። . የድል ቀኑን በማስመልከት ንግግር ያደረጉት ፕሬዚዳንት ፑቲን፣ ወታደሮችን የአባቶቻቸውን ገደል ለመድገምና ዳግም እያቆጠቆጠ ያለውን የናዚን አስተሳሰብ ከወገቡ ለመቅጨት እየተዋጉ ነው፣ በቅርቡ የትውልድ አገራቸውን ( ዩክሬንን ) ነፃ አውጥተው፣ የአባቶቻችን ታሪክ ይደግማሉ፣ የሩሲያ ጥላቶችም ደህ ብትር ቀመሰው መልሰው ወደ ሩሲያ ፊታቸውን አዙረው መተኛት ያቆማሉ፣ አሁን እያደረግነው ያለ ውጊያ በዕቅዱ መሰረት እየሄደ ነው፣ ሆኖም ሩሲያዊያን እነዚህ የናዚ አሽከሮችን በደንብ መግረፍ አለባቸው፣ ለመግረፍም መዘጋታቸውን ማቋረጥ የለባቸውም ሲሉ ሆመጠጥ ያለ ንግግር አድርገዋል። ተቀናቃኛቸው የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በበኩላቸው፣ በኬቭ አደባባይ ብቻቸውን እየተጓዙ ባደረጉት ንግግር ጥላት ከ77 አመት በኋላ ዳግም ወረራ መፈፀሙን አሳውቀው፣ ድሉ የዩክሬንና የምዕራባውያን ነው ሲሉ ዝተዋል። የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ይሄንን ተንቀሳቃሽ ምስል ከለቀቁ በኋላ የፓክስታኑ የዜና ኤጀንሲ በሰራው ዘገባ ላይ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ የለቀቁት ቪዲዮ በህዳር ወር የተቀረ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሏል። . አሜሪካ የሩሲያን የድል ቀን ማክበር አስመልክታ በፔንታጎን አመራሮቿ በኩል መልዕክት ያስተላለፈች ሲሆን፣ ፑቲን ሦስተኛውን የአለም ጦርነት ለማስነሳት እጫፍ የረደሰ ይመስላል፣ ሰውየው ምን አይነት ህሌና እንዳለው አላቅም USA መፍትሔ መፈለግ አለባት፣ ቻይና ግን የሩሲያን አካሄድ እያች ዝምታ መርጣለች ባበደ አለም ውስጥ እንዴት ያለ ንግድ ልታካሂድ እንዳሰበች አላቅም ስትል ቻይናን ወቅሳለች። የሰሜን ኮሪያው ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ለሩሲያዊያን የድል ቀን እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን፣ ሩሲያ በፈለግሽኝ ቀን ጥሪኝ አለሁኝ፣ አሁንም በዝባዧን አሜሪካን በሳይበር ማሳደድ ይዣታለሁ፣ በቅርቡ ከአሜሪካ የምትፈልጊውን ሚስጥር እሰጥሻለሁ ስትል አሳውቃለች። Abay News Network ሊንኩን በመጫን የANN የዩቲዩብ ቻናል ቤተሰብ ይሁን ! https://youtu.be/1riQyH2_eLE
Show all...
ANN ( Abay News Network )ኢንተርናሽናል ሚዲያ !

ANN ( Abay News Network ) ኢንተርናሽናል ሚዲያ .!