cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Mind Change

መጥፎ መጥፎውን እየተውን መልካም መልካሙን እንይዛለን

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
200Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

<< ሰዓት አልቋል >> ክፍል አንድ { 1 } አንድ ጊዜ አንድ ሰው ተደባድቦ የታሰረ ጓደኛውን ለመጠየቅ ወደ እስር ቤት ሄዶ ነበር፡፡ አስጠራውና አንድ ፖሊስ አጠገባቸው ቆሞ ማውራት ጀመሩ ሊያወራው የሄደው ስለ እናቱ ጉዳይ ነበር፡፡ ታዲያ ገና እንደተያዩ ብዙ ጨዋታዎች ትዝ አላቸው እና ማውራት ያለባቸውን ትተው ሲቀላለዱ ቆይተው ልክ የሄደበትን ዋና ጉዳይ ሲጀምርለት ፖሊሱ ወፈር ባለ ድምፅ ‹‹ሰዓት አልቋል›› አለና፡፡ ከዚያም ሳይወዱ በግዳቸው እስረኛውም ወደ እስሩ ጠያቂውም ወደ ቤቱ !! ከእስር ቤቱ ከወጣ ቦሃላ ግን የሆነውን ነገር እያሰበ ገረመው አሁን እናቱን ምንድነው የምላቸው? ተዉት እኔ አዋራዋለሁ ብሏቸው ሄዶ ሲቀላለድ እና ሲሳሳቅ ሰዓት እንደአለቀ ትዝ ብሎት ምንድነው ምነግራቸው ቁም ነገሩን ትቼ በሌላ ወሬ እና ጨዋታ ጊዜ ሳጠፋ ሰአት አለቀብኝ ብላቸው ሰውም አያረጉኝ እያለ በራሱ እያዘነ ወደ ቤቱ ተመለሰ ፡፡ ህይወታችንም ውስጥ ይህ ነው ያለው፡፡ ማድረግ የምንፈልገውን ነገር በወቅቱ ሳንሰራ እንቀርና ልክ ማድረግ ያለብንን ማድረግ ስንጀምር ሞት የሚሉት ጃግሬ ደወሉን ይዞ ከች ይላላ፡፡ ያኔ ሳንኖር እንሞታለን፡፡ ስለዚህም ወዳጄ እኔ ላስታውስህ ‹‹ሰዓት አልቋል›› ከመባልህ በፊት ብዙ ልታደርጋቸው የሚገቡ ነገሮች አሉና ቅድሚያ ስጣቸው፡፡ ክፍል ሁለት ይቀጥላል ....... @christ_zene @christanzenabo
Show all...
ለአስቸኳይ የጸሎት ጥያቄ ፡፡ እባክዎን ለህንድ አብያተ ክርስቲያናት ጸልዩ ፡፡ ትናንት ማታ ሃያ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል ፡፡ እናም ዛሬ ማታ በኦሊሳባንግ ግዛት ውስጥ ከ 200 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን ለማጥፋት ይፈልጋሉ ፡፡ በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ 200 ሚስዮናውያንን ለመግደል ይፈልጋሉ ፡፡ ሁሉም ክርስቲያኖች በመንደሮች ውስጥ ተደብቀዋል ... እባክዎን ይጸልዩ እና በዓለም ዙሪያ ለሚያውቋቸው ክርስቲያኖች ሁሉ ይህንን መልእክት ይላኩ ፡፡ በሕንድ ውስጥ ላሉት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እግዚአብሔርን ምህረትን እንዲያደርግላቸው እግዚአብሔርን ይጠይቁ ፡፡ “ይህንን መልእክት ሲቀበሉ እባክዎ ለሌሎች ሰዎች በፍጥነት ይላኩ ፡፡ እባክዎን ለ 22 ክርስቲያን ሚስዮናውያን ቤተሰቦች በሞት ፍርድ ላይ ይፀልዩ ፡፡ ብዙዎች እንዲፀልዩ እባክዎን ይህንን መልእክት በተቻለ ፍጥነት ያስተላልፉ! 🙏🙏🙏🙏🙏 በፍቅር ላይ, ጆይስ ሜየር. 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry
Show all...
My love for you‍‌‌‌‌‍‍‍‍‌‌😗‌‌ I love you. I know you will be shocked, but you mean so much to me. I try to get closer to you, but you seem to be too busy.The more I give you my attention,the more you think of someone else. it hurts when I call and no one answers. I try to give myself to you, but you do not seem to be ready. Give me a chance to love you. It's me JESUS. Every day, you open your inbox to read your friends messages, but how often do you open you Bible to read God's message? Please until the end. My name is Jesus. You barely have time for me. I love you and bless you, I am always with you. You have to spend 30 minutes of your time with me today🥺. Do not pray, Just give God praise. Today I want this message to circulate around the world before midnight. Will you help me? Please do not break the chain and I will help you with something you need! A blessing is in your way. Stop whatever you are doing right now and forward this message. Tomorrow will be the best day of your life. Do not break this chain. Send this page to 10 friends in 10mins. The clock starts now‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ d‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ I've been in prison‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ for your sake.‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌the people spit‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️on me‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌for your sake‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️I was mistreated‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌for your sake‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️humilized‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌for your sake‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️on the cross‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️for your sake Death and risen‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ FOR YOU ‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️‍‌‌‌‌‍‌‌❤‌‌️ If you're not ashamed of Jesus send this to 10 people you love ‌‌‍‌‍‍
Show all...
ህይወቴ የተቀየረው በዚህ ቃል ነው😭🔥 #ይሄን ቃል የሰማ ሁሉ ይቀየራል #ስሙት እና ተቀየሩ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @SisayAzusaRevivall @SisayAzusaRevivall @SisayAzusaRevivall
Show all...
እሱ ተፈርዶበታል አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል፤ እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ። በምን ዓይነትም ሞት ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲያመለክታቸው ይህን ተናገረ። ዩሐ 12:31-33 እዚህ ቦታ ኢየሱስ እያወራ ያለው ስለሞቱ እንደሆነ እናያለን። ስለዚህ የዚህ አለም ፍርድ ደርሷል ማለት እሱ መስቀል ላይ ተሰቅሎ መሞቱን ያም የዓለም ፍርድ እንደሆነ እየተናገረ ነው። ማለትም ኢየሱስ የዓለምን ፍርድ ተቀብሏል ሰዎች ሁሉ ሊፈረድባቸው የነበረው ፍርድ እሱ ተፈርዶበታል። በአውዱ መሰረት "ከምድር ከፍ ባልኩ ጊዜ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ" ማለት "በመስቀል ላይ በተሰቀልኩ ጊዜ ዓለም ላይ ያለውን ፍርድ ሁሉ ወደ እኔ እስባለሁ ሰዎች ለሰሩት ስራ እኔ ፍርዱን እቀበላለሁ" እያለ ነው። ለዚህ ነው በልጁ ለሚያምን ሰው ሁሉ ፍርድ የሌለበት። ኢየሱስ በእኛ ቦታ ሆኖ ስለተፈረደበት እኛ አይፈረድብንም። ሰዎች የሚፈረድባቸው በልጁ ባለማመናቸው ብቻ ነው። በእርሱ #በሚያምን_አይፈረድበትም፤ #በማያምን_ግን_በአንዱ_በእግዚአብሔር_ልጅ_ስም_ስላላመነ_አሁን_ተፈርዶበታል። ዮሐ3:18 @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry
Show all...
👉 ዕብራውያን2:1-4 👈 👉❇️ ከእግዚአብሔር መራቅ ❇️👈 📍የዚህ ስፍራ ዋነኛ ሀሳብ አንድ ነው ----Drifting away ~{ከእግ/ር መራቅ}...... 1️⃣#THE REALLY DANGER OF “drifting way ❇️መዳናችንን "ቸል"ማለት ልንችል ይሆናል ::-ዕብ2:3 ❇️ከእ/ር መለያየት ልንችል ይሆናል::ዕብ3:12-14 ❇️ልንነሳ ማንችልበት አወዳደቅ ልንወድቅ እንችላለን::-ዕብ6:4-6 ❇️የኢየሱስ መስዋትነት ለሀጥያታችን ጥቅም የማይኖርበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል::ዕብ 10:26-27 2️⃣#የተናገረበት ክብር(dignity) ❇️በኢየሱስ -ዕብ2:3 ❇️በመልአክት -ዕብ2:3 ❇️በሰሙት ደቀ-መዛሙርት ዕብ2:3 ➖የነዚህን ቃል አለ መስማት "ንቀት' ይሆንብናል:: 3️⃣#ምስክርነት(conformation) ❇️በምልክት ❇️በድንቅ ነገር ❇️በልዩ ልዩ ተአምራት ➖ጥቅሱን -ዩሐ 10:37-38 ላይ አለ:: ❇️መንፈስ ቅዱስንም በማደል -1ቆሮ12:7-11 4️⃣#ከእ/ር እንድንርቅ ሚያረጉ ነገሮች (Currents Thant make us drift ) ❇️ግዜ መዛል ገላ 6:9 ❇️ለእ/ር ያለንን ፍቅር መቀነስ ራዕይ 2:4 ❇️ማህበረስብ ❇️ባልንጀራነት (ከመንፈሳዊ ሕይወት የራቀ ጉዋደኛ) -1ቆሮ 15:33 ❇️ሀሳብ መበላሸት -2ቆሮ11:2-3 ❇️ስጋ ... ስጋችን ከመንፈሳችን ጋር ይቃወማል ገላ 5:16:17 5️⃣#ከመራቅ እንዴት እንመለስ :- ❇️✝️የእ/ር ቃል ማንበብ ..ሐዋ ስራ 7:11 ✝️ትጋትን መጨመር (pray)2ጴጥሮስ 1:10,5 ✝️ግማሽ ልብ መሆን የለብንም ✝️we have to give FULL Commitment -ፊል 3:12-15 ✝️ፅድቃችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ማወቅ (1ዩሐ2:1) ✅እግዚአብሔርን የማያውቅ ማንኛውም ሰው ተራ ሰው ነው....ተራ ሰው ደግሞ ከእግዚአብሔር ከተገኘው መለኮታዊ ባህሪይ ይልቅ ከአፈር የተገኘው ባህሪውን ያንፀባርቃል.. ...ሕይወቱም በአፈር እና በሞት ይገለፃል ...(Dr M.M) ❇️ስለዚህ friends በዘመናት ውስጥ የማይለወጠውን አምላክ በልባችን ውስጥ ለመለወጥ ካሰብን ትልቅ ስህተት ነው::አሁን አሁን ካለንበት ጥሩ ከሆነ አጥብቀው መያዝ መጥፎ ከሆነ ፈቀቅ ማለት አለብን አለዚያ ወደ ጭቃ መዘፈቅ ከፈለግን ከእግዚአብሔር መራቅ እንችላለን ግን....... ግን መመለስ ከባድ ነው::ዕብ6:4-6 🔰 መፅሐፍ ቅዱስን በማንበብ 👆ጥቅሶቹን በደንብ እየመረመራቹ በቃሉ በርቱ .... 🙏የኢየሱስ ፀጋ ከናንተ ጋር ይሁን ......አሜን!!!! ይቀላቀሉት join ❤️❤️👇👇👇 @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry
Show all...
#ሃያ አንዱ ማኅበራዊ ሕግጋት መልዕክቱን አንብበው ሲጨርሱ #Share ያድርጉት (Social Rules ተብለው የተዘረዘሩ የማኅበራዊ ሕይወት ሕግጋትን ስመለከት ለኛስ አትጠቅምም ወይ ብዬ ነው ወዲህ ማምጣቴ) ================== 1. ይሰለቹሃል አስሬ አትደውል፤ ሰዎች ጋር ከሁለቴ በላይ አይደወልም። ተሰልቺ ትሆናለህ! 2. 'ሼም ነው' ነው የሚከፍለው ሌላ ሰው ነው ብለህ ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ምግብና መጠጥ አትዘዝ! 3. አይባልም "... እንዴ እስካሁን አላገባሕም? ለምንድነው እስካሁን ያልወለድሽው? እንዴት ዲግሪሽን እስካሁን ሳትይዢና ሳትይዝ ወዘተ..." አይባልም። 4. ክፈል አብሮህ ላለው ሰው ታክሲ ላይም ሆነ የትም ቦታ አግባብ ነው ብለህ ስታምን ቀድመህ ክፈል። ገና ለገና ይከፍላል ብለህ ከሱ ስትጠብቅ ደምህን እያሯሯጥክ ትሰቃያለህ። 5. ነውር ነው ሰው እየበላም ይሁን በማንኛውም ሰዓት ከሰዎች ጋር ካለህ ጥርስህን አትጎርጉር፣ አፍንጫህንና ሌሎች ያልተገቡ ቦታዎችንም አትነካካ። ============ 6. አታቋርጥ ግዴለህም አብሮህ ያለው ሰው አውርቶ ይጨርስ። ጥልቅ እያልክ አታቋርጥ። ከባሕልም ከስልጣኔም ውጪ ነው። 7. አታብሽቅ ሆን ብለህ የማናደድ ባሕሪ ካለህ ተው። ሰዎች ለመባል የማይወዱትን ተው። ሰዎች ብዙ የማይናገሩትና የተሸከሙት የራሳቸው ብሽቀት ስላለባቸው ለተሻለውና ለሚበረቱበት ሕይወታቸው አድናቆት ስጥ። 8. አመሥግን ለተደረገልህ ማንኛውም ቅንጣት ነገር አመሥግን። 9. ያለስስት አድንቅ ሰዎችን በይፋ አድንቃቸው፣ መልካም ያልሆነ ነገራቸውን ግን በግል አውራቸው። 10. ክፉ አስተያየትህን ቆጥብ ያልሆነ ነገር ብታይ እንኳን አፍህ በበጎ ቃላት ይቀይረው። ወፍሮ ያየኸውን ሰው ኤጭ ተዝረጠረጥክ ከማለት ተቆጠብ። =================== 11. ካልሆኑ ጥያቄዎች ታቀብ ሰዎች የሕክምና ቀጠሮ ሄደው መምጣታቸውን ነግረውህ ይሆናል። የውጤቱን ምንነት ለማወቅ ግን በጥልቀት አትጠይቅ። በነገሩህ ልክ መልካሙን ተመኝላቸው። በቻልከው መጠን በመረጃና በጥቆማ አግዛቸው እንጂ ድንበር አትዝለል። 12. ስነ ስርዓት ሰዎች ከስልካቸው ላይ ፎቶ እንድታይ ቢሰጡህ ከፈቀዱልህ ውጪ ሌላ ፎቶ ካላየሁ ብለህ ስልክ አትፈትሽ። ሁሉም ሰው ታልፎ እንዲገባበት የማይፈልገው የራሱ አጥር አለው። 13. ክብር ለሁሉም ከላይ ጫፍ ላለ የሥራ ኃላፊና ከታች ዝቅ ባለ ስራ ላይ ለሚገኘው ሰው እኩል ክብር ስጥ። እንደውም ከላይ ካለው ይልቅ ታች ላለው ሰው የሰጠኸው ክብር ብዙ እውቅና አለው። ለንቀትህ ግን የማንንም አድናቆትና ጭብጨባ አታገኝም። 14. ስልክህን አስቀምጥ ሰዎች በቀጥታ ላንተ እያወሩ ስልክህን የምትነካካ ከሆነ ቀሽምነት ነው። ከሰው ሰራሹ ይልቅ ራሱ ሰው ትልቅ ዋጋ አለው። 15. አድብ ሰዎች ካልጠየቁህና ካልፈቀዱልህ በስተቀር በራሳቸው ሕይወትና ሥራ ጣልቃ አትግባባቸው። ========================== 16. ተቆጠብ ከረጅም ጊዜ በኋላ ያገኘሃቸውን ሰዎች አስጨናቂ ጥያቄ አትጠይቃቸው። ሰዎች ቆይታቸውን እንዲሁም ዕድሜና ደሞዛቸውን ጨምሮ የመናገርና ያለመናገር ብቸኛ ባለመብት ራሳቸው እንደሆኑ እወቅ። 17. መነጽርህን አውልቅ ከሰዎች ጋር በዓይንህ አውራ። ከማንም ጋር በመንገድ ላይ ተገናኝተህ ስታወራ መነጽርህን ከዓይንህ ማንሳት እንዳለብህ አስታውስ። ክብርም ነው! 18. አትሳሳት በድኅነት አስተሳሰብ ሆነህ ስለሀብታሞች ምንነትና ማንነት አታውራ፤ ልጅ ሳይኖርህ ስለልጅና ልጅ ስላላቸው ሰዎች ባሕሪ አትፍረድ። 19. ለስልክ መልዕክት ምላሽ መስጠት በስልክህ የጽሑፍ መልዕክት ሲደርስህ አንብበህ ዝም ማለት ነውር ነው። ተገቢውን ምላሽ በበጎነት ቃል መመለስን ልማድህ አድርገው። 20. ዕቃ መልስ የወሰድከውን ማንኛውም ቁስ ባለቤቱ ሳይጠይቅህ በፊት ቶሎ መልስ። 21. አማራጭ ሐሳቦች ሁሌም አሉ የያዝከውን ሐሳብ ሳትፈራ አውጣው። ሌሎች እንዲወያዩበትና እንዲተቹት ክፍት አድርገው፤ አንተም ሐሳብህም ትጎለብታላችሁ። ነገርህን ደገፉትም አልደገፉት ምንጊዜም ቢሆን ላነሳኸው ሐሳብ ጥሩ ግብዓት አይጠፋም። ልክ አልሆን ወይ እያልክ ወይም ሐሳቤ ያንስ ይሆን ወይ ብለህ አትሸማቀቅ፤ ተሸማቀህ ትቀራለህ! t.me/psychoet ©Abraham Tsehaye
Show all...
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ 🤷‍♂

| እውነት | ፍትህ | ፍቅር | ✔ሥነ ልቡና | የተለወጠ ግለሰብ አለም ይለውጣል! የተለያዩ የስነልቦናና የላቀ የሰው ልጅ አስተሳሰብ ላይ የተሰሩ video ለማግኘት የዩቲዩብ ቻናሌን ይከታተሉ "የማወቅና የመለወጥ ሰአት አሁን ነው "

https://www.youtube.com/user/TheNahusenai

Facebook አድራሻዬ Fb.com/psychologyet

🏆ድል🏆 🗣ዌል..! ተዘጋጅታቹሃል? ምታቀርቡት ፕሮጀክት ተዘጋጅቷል? ለፈተና አጋዥ መፅሀፍት ተለብልቧል? ደግ! 👉ነገር ግን ጥንት ተዋጊ ሰዎች ፈረሳቸውን አዘጋጅተው: ይመጣል የተባለው ጠላትን አፈር ድሜ ሊያበሉ ሲዘጋጁ:- 🧐ጠቢቡ ሰለሞን ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤ ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። (ምሳሌ 21:31) አለ:: 👊ስለዚህ ሁሉን በተዘጋጀንበት ጊዜ: ታጥቀን ልንወጣ ስንል ድሉን ልንሻ የሚገባው ከእግዚአብሄር ዘንድ ነው:: ምንም ዝግጅት ቢኖር የእሱ እጅ ከሌለበት ድል የራቀ ነው:: Then... ምንም ብንለፋ #እሱ_ብቻ_ድልን_ይሰጣል:: @GCI_Biblical_Ministry
Show all...
♥️ •••ፍቅር ይህ ነው........♥️ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና::እግዚአብሔር ፍቅሩ በመካከላችን የገለጠው እንዲህ ነው...👇👇👇 ❤️እኛ በእርሱ አማካኝነት በህይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር 👉አንድያ ልጁን👈ወደ አለም ላከ:: ♥️ፍቅር ይህ ነው!!!!እኛ እግዚአብሔር እንደ ወደድነው ሳይሆን እርሱ እንደ ወደደንና ስለ 👉ሀጥአታችን ማስተሰሪያ👈ልጁን መላኩ ነው:: #ወዳጆቼ_ሆይ_እግዚአብሔር_እንዲህ_ከወደደን #እኛም_እርስ_በእርሳችን_ልንዋደድ_ይገባናል #አብ_ልጁን_የዓለም_አዳኝ_ይሆን_ዘንድ #እንደላከው_አይተናል_እንመሰክራለን!!!! ((1ኛ ዮሐንስ4:1-21)) በልባችን የተወለደው ክርስቶስ ኢየሱስን የምናስብበት #ገና ይሁንልን!! ይቀላቀሉት 👇👇👇 @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry @GCI_Biblical_Ministry
Show all...
የፈረሱ ነገር... 🚗መንገድ ላይ ነው ያለንው:: በመኪናችን አጠገብ "ዥው...ዥው" እያሉ የሚያልፉት መኪኖች ጆሮን ይገርፋሉ:: ከጠባቡ መንገድ መሃል ግን አንድ የተጋጋጠ ፈረስ ቁሟል:: እየሄድኩበት ያለበት መኪና ውስጥ ያሉትን ሰዎች ጠየኩ:- 🐴”ይሄ ፈረስ ለምንድነው እመንገድ መሃል የቆመው?" አንደኛው "Life ነዋ... ብዙ አመታት ሲያተርፍበት የነበረው ሰውዬ ሲከዳው ምን ያድርግ...ከዚህ ሁሉ ስቃይ ሲኖዬ ገላግለኝ ብሎ ይሆናል..." ፈገግ አልኩኝ:: ሌላኛው ተለቅ ያለው ሰውዬ ግን... "ዝንቦቹ ናቸው:: ከቁስሎቹ የተነሳ ዝንቦች ስለሚበዘቡት በሚያልፉት መኪኖች ንፋስ ማባረር ይፈልጋል... ለዛ ነው ሚቆመው:: ዞሮ ዞሮ ግን ዝንቡን ሲሸሽ መገጨቱ አይቀሬ ነው::" ሲገርም... 👉ከራሴ ነገር ጋር አገናኘሁት... ➡️እኛም አንድ ነገር ለመሸሽ ስንል ህይወታችንን አስጊ ነገር ውስጥ ልንከት እንፈልጋለን:: የተፋታች ሴት ህይወት ሲመራት የመጠጥ ሱሰኛ መሆን ትጀምራለች:: መከረኛውን ህይወትዋን በመከራ ውስጥ ልታቀዘቅዝ ትሻለች:: ድባቴ ሊሸሽ ፈልጎ ሱስ ውስጥ የሰመጠ ብዙ ነው:: ➡️ትንሹን ኩሬ ለመዝለል ፈልጎ ትልቁ ገደል የገባ ስንት አለ:: ትንሿ ውሻ አስደንብሮት... ጅብ የነከሰው ስንት ነው...? ➡️ችግር መኖሩ አይደለም... ችግሩን ምንሸሽበትና ምንመክትበት ነገር ግን ዋና ነገር ነው:: አምባችን ያደረግንው ምንድነው? መሸሺያችን ምንድነው? መዝሙረኛው እንዳለው... መ.ዳዊት 18 2፤ እግዚአብሔር ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት ረዳቴ፥ መታመኛዬና የደኅንነቴ ቀንድ መጠጊያዬም ነው። እሱ መጠጊያችን ነው:: እሱ መሸሺያችን ነው:: . . ግን አይገርምም... የፈረሱ ነገር...?😁 @GCI_Biblical_Ministry
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!