cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

UNION FELLOWSHIP©✝

#we deal about the strength and weakness of our fellowship #we advertise what programmes we have and had in the week. #we address you an information about such things whole over Ethiopia. #PRAYER IS THE ONLY MEANS OF RECEIVING SPIRITUAL POWER!!!!! @UACSFF

Show more
Advertising posts
553Subscribers
No data24 hours
-37 days
-330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

.__.__.__._. |የእርቅ ጅ| .—.—.—.— ⌚️ጊዜው እንደ ኤሮፓውያን አቆጣጠር በ 1960 ዎቹ ገደማ ነበር አንድ የወንጌል መስካሪ (missionary) ከባለቤቱ ጋር ወደ  ኔዘርላንድ/ newgene ወደተባለች አንድ ሀገር (sowe) ወደ ተባሉ ህዝቦች ታላቁን ተልዕኮ ለማብሰር  ወደስፍራው ያቀናሉ:: 🎈በዚች ሀገር በጊዜው የነበረው ከፍተኛ እልኸኝነት ፣ቂም በቀል ብሎም የፖለቲካ ውጥረት ያስከተለው የእርስ በእርስ ግጭት ብሎም የዘር መከፍፈል እና ጎጠኝነት አያሌ ሰዋችን ለሞት በርካቶችን ለአካል ጉዳት ብሎም ለከፍተኛ ኪሳራ ዳርጓቸው እንደ ነበር:: የታሪክ መዛግብት ይተርካሉ ሀገሪቱንም በደም ጎርፍ አጥለቅልቋት ነበር፤ ታድያ በዚህ አሰቃቂ ወቅት እግር የጣለው ይሄ የወንጌል መስካሪ ስፍራውን ከረገጠ ቅፅበት አንስቶ ለእነዚህ በድቅድቅ ጨለማ ላሉ ህዝቦች ወንጌልን እንዴት እንደሚመሰክር ሀሳብ ይገባዋል:: ♨️ ይሄንን ጭንቀቱን በፀሎት ለላከው አምላኩ ዘወትር በፀሎት ማሰማቱን ተያያዘ ከዛም ከእለታት በአንዱ ቀን በአንድ ትንሽዪ መንደር ውስጥ ሲራመድ በርከት ያሉ ሰዎች ተሰብስበው ይመለከታል ነገሩን ለማጣራት ቀረብ ብሎ ሲመለከት የ sowe ህዝቦች የጎሳ የእርቅ ስነስርዓት ነበር:: 🔅በስርዓቱም ላይ አንድ ምንም የማውቅ እንደተወለደ ያለ ህፃን ልጅ ሁለቱም ጎሳዎች ይለዋወጣሉ ሁለቱም ጎሳዎች ልጆቹን ያሳድጋሉ ልጆቹ በህይወት እስካሉ ድረስ እርቁ የፀና ይሆናል::  ልጁም የእርቅ ምልክት የእርቅ ልጅ ሆኖ ይኖራል መስካሪውም ይሄን ልጅን የእርቅ ምልክት አድርጎ የመጠቀምን ባህል አንድ ነገርን ለማውራት ተጠቀመበት:: 🔻ይሄም በፃድቁ እግዚአብሔር አምላክ እና በሃጢአት የወደቀውን የሰው ልጅ ለመታረቅ የእርቅ ጅ የሆነውን ኢየሱስን ወደ ምድር መላኩን ለመናገር በር ተከፈተለት:: 🎴በቂም በበቀል በዘር በጎጠኝነት ለተጨማለቀው ህዝብ ከጨለመው ህይወታቸው ላይ የመኖርን ፀዳል ፈነጠቀ በባህላቸው መሰረት ልጁ በህይወት እስካለ ድረስ እርቁ የፀና ይሆናል:: ኢየሱስ አምላክ ዘለአለማዊ ስለሆነ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር ያለው እርቅ ዘላለማዊ ነው:: ⚜️ይሄ ወንጌላውያን በማህበረሰብ ውስጥ በኖረበት ዘመን የክርስቶስ መወለድ ባሰብ ቁጥር በእንባ ይሞሉ ነበር:: ከበራላቸው የወንጌል ብርሀን የተነሳ በእርቅ እና በሰላም መኖር ጀመሩ ጦርነቱም ታሪክ ሆና ቀረ። 🔱በመጨረሻም በዚህ የእርቅ ልጅ የሚያምን ፣ የሚቀበል ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ይኖረዎል::
“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወዶአልና፤”    -ዮሐንስ 3፥16
⚠️ከእግዚአብሔር ጋር እርቅን መፍጠር የምትፈልጉ አሁንም ይሄ የእርቅ ልጅ ምንም ክፍያ የማይፈልግ በነፃ የሚያስታርቅ ነፃ ስጦታ ነው ከእግዚአብሔር ጋር እርቅን የምትፈልጉ ያነጋግሩን:: 〽️aranatha Digital Network ⛈@Maranatha_MDN⛈ .| @Maranatha_MDN2 |.
Show all...
👍 1 1💯 1
#MDN_Profile_Picture_Challenge .                . .                . .የእርቅ ልጅ . ._____. .                . #MDN_Profile_Picture_Challenge 🎋ይህንን ምስል ፕሮፋይል ላይ በማድረግ ለእርቅ የሚሆን የእግዚአብሔር ልጅ መድኃኒዓለም የሆነ ኢየሱስ መወለዱን ለዓለም እናውጅ!! 〽️aranatha Digital Network ⛈@Maranatha_MDN⛈ .| @Maranatha_MDN2 |.
Show all...
2🙏 2
😍 ቤተሰብ + 👋ምህረት እና ቸርነት ይብዛላችሁ ቀን ቀንን እየወለደ እግዚአብሔር መድሃኒያለም ርህራሄውን አብዝቶልን ይኸው ለ2016 የክርስቶስ ውልደት መታሰቢያ የአምልኮ መርሀግብር ደረስን አዎ ማክሰኞ 9:30 ጀምሮ በአምልኮ መንፈስ ወዱ ስጦታችንን ከዘፀአት መዘምራን ጋር እና ከእየሩሳሌም ወራሾች ጋር በመንፈስ እናመልካለን ታድያ ለዚህ የአምልኮ እድል አድለኛ ሰዎች ሁላችንም እንደምንገኝ ስጋት አይገባኝም 😍ቤተሰብ + ቤተሰብ አይጋበዝም መምጣታቹ እርግጥ ስለሆነ ማርፈድ አይቻልም + እንደ ወትሮው ግቢ ውስጥ ያሉ ልጆች ይሄንን ድንቅ እድል ያገኙ ዘንድ 😍ቤተሰብ + ሁላችንም telegram Instagram Facebook ገፆቻችን ላይ profile በዚህ ምስል በመቀየር ብሎም story በማድረግ ማስታወቂያ እንሰራለን ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ🙏 ማክሰኞ ታሪካዊ ቀን እንደሚሆን እናምናለን
Show all...
💯 2 1🥰 1🙏 1
#CHRISTMAS #FAMILY #DAY #POSTCARD #GIFT #2016 🙏ሰላም እና ምህረት ይብዛላችሁ 🤩ቤተሰብ + እንደምን ቆያቹ ከላይ የምትመለከቱት ምስል የዘንድሮው የ #CFD 2016 ከ ህብረታችን ለእናንተ ወድ ቤተሰቦቻችንን ያዘጋጀነው የገና ስጦታ post card ነው በውስጡ ተጨማሪ ቸኮሌት ስጦታ አለው በ #CFD PROGRAM ላይ ለተገኛቹ ምርጦቻችን በሙሉ አበርክተናል በተለያየ ምክንያት ያልተገኛችሁ ቤተሰቦቻችን ለሁላችሁም ያዘጋጀነው በቂ ስጦታ ስላለ በግቢ የምትገኙ ክርስቲያን ተማሪዎች በሙሉ ከህብረታችን መሪዎች መቀበል ትችላላችሁ ስለ #CFD 2016 LOTTERY እና የገና ፕሮግራም pp challenge አመሻሽ ላይ እንመለስበታለን
Show all...
1👏 1🙏 1
#CHRISTMAS #FAM #DAY 😍 ቤተሰብ + 👋ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ ዛሬ ስለነበረን 2016 #CHRISTMAS #FAM #DAY ክብሩን እግዚአብሔር ይውሰድ የእውነትም በክርስቶስ የተካፈልነውን ቤተሰብነት ያስተዋልንበት ድንቅ ጊዜ ነበረን የተገኘን ምንም ጥርጥር የለውም ያልተገኘን ወገኖች ግን ብትገኙ ደስታችን ነበር ስለ መርሀግብሩ የተወሰነ ገለፃ ላልተገኛቹ በምናብ ገባኤውን እናሳያቹ 🧎‍♂የፀሎት አምልኮ : ከተወዳጁ ሰብሳቢያችን ከ አማኒ ጋር ደንቅ ጊዜ ነበረን ✍ስነፅሁፋዊ አምልኮ: ስራ እና አዝናኝ ጨዋታዎች : በፌቨን አና በቤተልሔም 🙌የዜማ አምልኮ: ዘማሪ ምንተስኖት + ዘማሪ ሄኖክ + ዘማሪ አሸናፊ + ዘማሪ እንዳሻቸው ሙዚቀኛ ሚንጂ + መዚቀኛ ሀብታሙ ጋር ወደ ሰማይ ሰማያት ከፍ ብለን ነበረ በዚህ መርሀግብር በአምልኮ ያስተባበራቹን በሙሉ ፀጋ እና ምህረት ይብዛላችሁ ከልብ ትወደዳላችሁ 🙏 😍ብሎም የዘንድሮውን የ2016 #CFD POSTCARD ይፍ ተደርጎ ለሁሉም ቤተሰቦቻችን ተበርክቷል + የ2016 በ የገቢ ማሰባሰቢያ ሎተሪም ይፍ ተደርጎ ስራ ላይ ውሏል ስለዚህ ሰፍ ባለ ገለፃ እንመለሳለን 😍ቤተሰብ + ስለናንተ ቃላት ያጥረናል ብቻ አክብራችሁ ስለታዘዛችሁን ትውልድ ይታዘዛቹ ፀጋ ይብዛላችሁ ደም እንወዳቹዋለን 🥰
Show all...
2🥰 2👏 2👍 1🤩 1
😍#CHRISTMAS #FAMILY #DAY😍 😍 ቤተሰብ + 🎉ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ ቤተሰቡ + በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ተናፍቂው የ2015 የገና የቤተሰብ ቀን ደረሰ ደረሰ ደረሰ🎉 የፊታችን ቅዳሜ ሁላችንም ህይወት የሰጠንን ጌታ በአንድነት ከፍ እናደርጋለን በግቢ ውስጥ ያለን ሁላችንም የዪኒየን ፌሎ ቤተሰቦች ብሎም ከዚህ ቀደም የነበርን አሁን በተለያዪ ቦታች ያለን ሁላችንም በጊዜው መገኘት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው 😍 አዎ ቅዳሜ 8:00 እግርች Christmas family day ያመራሉ ማርፈድ አይቻልም መቅረት ማርፈድ የታሪክ ተጠያቂ ያደርጋል (አይቻልም ) 🏃‍♂🏃‍♂🏃‍♂
Show all...
👍 4🥰 1🤩 1
👋 ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ 😍ቤተሰብ+ እንደምን ከረማቹልኝ  በብዙ ምህረት እንደበዛላችሁ አልጠራጠርም ምክንያቱንም እርሱ አንድዪ መድሃኒያለም በብዙ ተሸክሞን በዘወትር ልምምዶቻችንን ምንም እንደ ሀሳብ ባንሆንም በፍቅሩ ቁስለት ላይ የጥላቻን እንጨት ብንሰድ ይኸው ችሎን በፀጋው ብቻ ተችለን ለመቆየት በማያመቸው  ልባችን ውስጥ እየኖረ በብዙ በደላችንን እና መቆሸሻችን ብሎም በሃጢአት ውድቀታችን ልባችን ተሰብሮ በልጅነታችን ቡዙ ጊዜ ተስፍ በንቆርጥም እርሱ ግን  በአባትነቱ ለአፍታ ተስፍ የማይቆርጠው ዛሬም ይሄን ፅሁፍ ስናነብ እያየን ያለ መንፈስ ቅዱስ ለዘለአለም ስሙ የገነነ ይሁን🙏 ለምን አልገደልከኝም ? ምርጦቼ ምን መሰላቹ  ዛሬ ትንሽ ሆድ ብሶኛል የእውነት😔  አመሻሽ አከባቢ አንድ ፅሁፍ እያየው በአለም አቀፍ ደረጃ በማህፀን እና ፅንስ ህክምና የሚታወቀው    d/r wael elbanna እንዲህ ብሎ የህክምና ምርምሩን አስቀምጦ አገኘውት "በአለም ላይ ካሉ ከእያንዳንዱ አስር ሺህ ነፍሰ ጡር እናቶች መካከል አንዷ  ይህ በፅንሷ ውስጥ የተበላሸ ቅርጽ የያዘ ልጅ ትፀንሳለች ይህም ማለት የራስ ቅል አለመኖር እና የአንጎል ክፍል መጥፋት ነው. ይህም ከነአካቴው የጭንቅላት ክፍል አለመኖር ነው። ..... 😢ለዚህም መፍትሔው ልጁ መወለድ ስለማይችል በእርግዝና ወቅት  ፅንሱን በመግደል ማስወረድ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው" ብሎ አስፍሯል 🤔ወዳጆቼ ዛሬ በብእሬ ልሞግታችሁ እንደው ከአስር ሺዎቹ አንዷ የአንተ/ቹ እናት ብትሆንስ ? 🤔የአባቴ ልጆች እንደው የእውነት ያ ያልተሟላ ፅንስ አንተ/ቺ በትሆንስ/ኚስ ? መልሱን ለእናንተው ተውኩ ለካ ጥሩ ቤተሰቦች ስላሉን አይደለም ያለነው ለካ በእናታችን ማህፀን ሳለን ጥሩ ሀኪሞች ስለተከታተሉን አይደለም ኧረ ያ እናታችን ማህፀን ውስጥ ሳለን እንደሚባለው የተመጣጠነ ምግብ ሙዝ እና ማንጎ ስለተመገበች አይደለም ለካ ትውልድ አይቶብን ነው ያለገደለን ለዛ ነው መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ ሲል የተቀኘው “ከተወለድሁ ጀምሮ በአንተ ተደገፍሁ፤ ከእናቴ ማሕፀን ያወጣኸኝ አንተ ነህ፤ አንተ የዘወትር ምስጋናዬ ነህ።”   — መዝሙር 71፥6 (አዲሱ መ.ት) 🙏የእኔ ቤተሰቦች እንደው አስብት ነገሩ ሳይንስ እንዳለን የተቃራኒ ፆታ ግንኙነት አይደለም የሰራን የጥቃቅን የዘር ፈሳሾች እንቅስቃሴ እና ትስስር አይደለም የሰራን ገና አለም ሳይፈጠር አስቦን ለክብሩ ፈልጎን ነው የእውነት ለካ ወር ስለተቆጠረ አይደለም የተወለድነው ለካ ቀናት ስለተደራረብ አይደለም የመጣነው ለካ እንድናገለግለው ነው ያልገደለን መዝሙረኛው በሌላው መዝሙሩ እንዲህ ሲል በአግራሞት ተቀኘ “አንተ ውስጣዊ ሰውነቴን ፈጥረሃልና፤ በእናቴም ማሕፀን ውስጥ አበጃጅተህ ሠራኸኝ።”   — መዝሙር 139፥13 (አዲሱ መ.ት) 🤔ደግሞ ከሁሉ የሚገርመው ዝም ብለን አለምጣታችን የምር ከተወለድን በኋላ እራሱ ህይወታችን የሞት ተግባራችን የጥፋት መንገዳችን የእርግማን ነበር ግን እርሱ ቸር አይደል ልጁን ልኮ በፀጋ በሆነ ድነት የዘለአለም ህይወትን በመስቀል ፍቅር ገለጠው በበደል በጨቀየን በእኛ ዳግመኛ የመንግሥቱን ስራ አሰበ “ከኀጢአተኞች ዋና በሆንሁት በእኔ እንደ ምሳሌ አድርጎ ያሳይ ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ።”   — 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥16 (አዲሱ መ.ት) 🙏ቤተሰቦቼ ከመገረም ውጭ ምን እንላለን እናመሰግናለን ጌታ ሆይ🙏 እራሳችንን ያለንበትን ብንፈትሽ በእራሳችን ሩጫ ተጠምደን የመንግሥቱን ተልእኮ ረስተን ያን የመስቀል እንባ ዘንግተን በእራሳችን መንገድ እየሮጥን እንገኛለን በእየሱስ የፀጋ ወንጌል  ዘለአለማዊ ድነት ተካፍለን ግን የመንግስቱ ስራ የዘነጋን ልቦናዎቻችን ይብሩ በመጨረሻም እንዲህ በሚል ፀሎት ልዝጋ አቤቱ አባታችን ሆይ በመንግስትህ ስራ ላይ ፦ ህይወት ሰተኸኝ አትጣን ጊዜ ሰተኸኝ አትጣን ፀጋን ሰጠኸኝ አትጣን ደምህን አፍስሰህልን አትጣን ለፀጋው ወንጌል ተማኝ የሚያሳፍር በጎ ባሪያዎች አድርገን አሜን🙏                         ✍Kibreab_x ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff @uacsff
Show all...
2👏 1🙏 1