cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ወንጌል ለዓለም🔈🌎

''And he said to them, Go into all the world, and preach the gospel to every creature. Mark 16:-15 እንዲህም አላቸው ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ማርቆስ 16:-15 የተመሠረተበት ቀን (ግንቦት 08/09/2012) ለአስተያየት @Geruuu ላይ inbox.

Show more
Advertising posts
5 447Subscribers
-124 hours
-167 days
-4330 days
Posts Archive
አራት መነኩሴዎች ከሚኖሩበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ ጉዞን ይጀምራሉ፣ አርፍደዉ ስለተነሱ የፈለጉበት ቦታ በጊዜ ስላልደረሱ፣ እዛዉ በደረሱበት ቦታ አረፍ ብለዉ ለመሄድ ይወስናሉ፡ ሰዓቱም ስለመሸ ምሽቱንም ባሉበት ቦታ ድንኳን ይዘዉ ስለነበር ድንኳናቸዉ ዘረጉ። ከመተኛታቸዉ በፊት ለመፀለይ ይስማማሉ ከመፀለያችን በፊት አንድ ህግ እናዉጣ አለ አንደኛው መነኩሴ ይህም ህግ ሁላችንም የምንፀልየዉ በዉስጣችን ነዉ ምን አይነት ነገር ቢፈጠር ማዉራት አይፈቀድም አለ፣ የቀሩት ሁሉም በወጣዉ ህግ ተስማምተዉ በዉስጣቸዉ ድምፅ ሳያሰሙ መፀለይ ይጀምራሉ። በጣም ስለጨለመ በድንኳናቸዉ ዉስጥ ሻማ ለኩሰዉ ነበር የሚፀልዮት። ትንሽ እንደቆዮም ከዉጪ በመጣ ንፍስ እየበራ የነበረዉ ሻማ ያጠፍዋዉ። አንደኛዉ መነኩሴ ከመካከላቸዉ ወይኔ ሻማዉ እኮ ጠፍ አለ፣ ሁለኛዉ መነኩሴ ቀበል አድርጎ በፀጥታ ነዉ መፀለይ ያለብን አለ፣ሶስተኛዉ ደግሞ እባካችሁ ዝም እንበል ያወጣነዉን ህግ እየጣሳችሁ እኮ ነዉ አለ፣ አራተኛዉ መነኩሴ በመጀመሪያ ፈገግ ብሎ እኔ ብቻ ነኝ ያላወራሁት አለ። ይህንን ታሪክ ያነሳሁት አንድ መልእክት ለማስተላለፍ ነዉ። በዚህን ጊዜ የአገልጋዮችን ስህተት ወደ social media ይዞ መጥቶ መተቸት የተለመደ ነዉ፣ በአስተምህሮ ወይም በልምምድ ስህተት ዉስጥ ያለን ሰዉ እንድንቃመዉ መፅሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ያስተምረናል 👉ፊል 3:2 ማቴ 16፡12 ገላ 5:5_11_12 1ዮሐ 2:22...... መፅሐፍ ቅዱስ ስህተትን እንድንቃወም ብቻ ሳይሆን የሚያስተምረን ስህተትን ስንቃወም አስቀድመን ማወቅ ስላለብን ነገር እንደ መመሪያ ያስተምረናል። ነገሩ ስህተት መሆኑን ብቻ ማወቅ ሳይሆን ያንን ስህተት የምናቀናበትን መንገድ አስቀድመን ማወቅ መቻል አለብን። ምክንያቱም በአሁን ሰዓት ስህተት የሆነን ነገር ለመቃወም በተሳሳተ መንገድ እየተቃወሙ ያሉ እየበዙ ስለመጡ። በቤተክርስቲያን ዉስጥ በአስተምህሮም ሆነ በልምምድ በስህተት መንገድ ያሉ አገልጋዮች ከመፅሐፍ ቅዱስ መምሪያ ዉጪ ስለሆኑ ነዉ። ከመመሪያው ዉጪ ሆነዉ የተሳሳቱትን የምንመልሳቸዉ በመመሪያዉ ነዉ። ስለዚህ የሳቱትን ለመመለስ የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያን ልንከተል ይገባል። ለእኛ ሲባል የሚሻር የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያም ሆነ ህግ የለም። ለምሳሌ መፅሐፍ ቅዱስ " ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" ይላል(1ኛ ጴጥ4:11) ይህ ለሁሉም ሰዉ የሚሰራ መመሪያ ነዉ። የተሳሳተን ሰዉ በመሳደብ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል በመናገር ነዉ ልናቀናዉ የምንችለዉ። እኛ ስንሳደብ የእኛ ስድብ ልክ ስለማይሆን።" ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።" ይላል መፅሐፍ ቅዱስ።እግዚአብሔር የአንደበታችንን ቃል ብቻ ሳይሆን የልባችንን motive (ምክንያት) የሚያይ አምላክ ነዉ የተሳሳተን ሰዉ ስንቃወም እርሱን ለመመለስና ገንዘብ ለማድረግ እንዲሁም በእዛ ስህተት መንገድ የሚሄዱትን ምዕመናንን ለማቅናት እንጂ የተሳሳቱትን ፈፅሞ ለመስበርና ለማጥፍት መሆን የለበትም " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የወደቁ አይነሡምን? የሳተስ አይመለስምን? "( ኤር 8:4) ይላል የሳቱት ቢመለሱ እኛ ለእነርሱ የሚመለስ ልብ እንዳለን እናረጋግጥ። ተሳስታችኋል የተባሉ ከስህተታቸዉ የተመለሱ እዉነተኛዉን አስተምህሮ የሚያስተምራቸዉ አጥተዉ ግራ በመጋባት ዉስጥ ያሉ በርካታ ሰዎች አሉ።😔 ስህተትን መናገር ብቻ ሳይሆን ከስህተቱ ለተመለሰ ሰዉ በፍቅር የሚያቅፍ እጅ ሊኖረን ይገባል።ለዚህ ደግሞ እዉነትን በፍቅር ልንይዘዉ ይገባል " ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን"(ኤፌ4:15) ስህተቱን ለመናገር እንደረበታነዉ ሁሉ እዉነተኛዉን አስተምህሮ ለማስተማር መትጋት አለብን። " እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። "(ዮሐ8:32) በስህተት የተያዘን ሰዉ ነፃ የምናወጣዉ በእዉነት ነዉ። 1+1 ሶስት አይደለም ፥4ትም አይደለም፥10ም አይደለም እያልክ ያልሆነዉን ከምትነግረኝ የሆነዉን 2 ብትነግረኝ ያልሆነዉን እኔ በቀላሉ እለያለሁ። አማኞች ስህተት የሆነዉ ነገር እንዲለዩ እዉነተኛዉን የእግዚአብሔርን ቃል እናስተምራቸዉ። ይህ ከላይ የገለፅኩላችሁ ስህተትን ስንቃወም መፅሐፍ ቅዱስ ከሚሰጠን መመሪያዎች በጥቂቱ ናቸዉ። መጀመሪያ ወዳነሳሁላችሁ ታሪክ ልመላሳችሁ፣ አራቱም መነኩሴዎች ያወጡትን ህግ ሽረዋል። አራቱም የሻሩት ልክ በሚመስል ምክንያት ነዉ፣ አንደኛዉ የሻማ መጥፍቱን እንዲያዉቁ ተናገረ ፥ሁለተኛው ደግሞ የወጣዉን ህግ ለተናገረዉ ሰዉ ለማስታወስ ተናገረ፥ሶስተኛዉ ደግሞ ሁለቱም ፀጥ እንዲሉ እንዳይናገሩ ተናገራቸዉ፥አራተኛዉ በስተመጨረሻ እኔ ብቻ አልተናገርኩም ብሎ አለመናገሩን ተናገረና ህጉን አፈረሰ። ተወዳጆች የእግዚአብሔር ቃል የሁላችንም መመሪያ ነዉ። አንድ አገልጋይ ከተሳሳተ ልንመልሰዉ የሚገባ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ አሳማኝ በሚመስል ምክንያት ግን ስህተት በሆነ መንገድ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ህግ በመሻር መሆን የለበትም። ጌታ ኢየሱስ ታልፎ በሚሰጥበት ምሽት ይሁዳ ጭፍሮችንና ከካህናት አለቆች ከፈሪሳውያንም ከሎሌዎችን ጋር በችቦና በፋና በጋሻ ጦር ሆኖ ወደ ኢየሱስ መጣ ኢየሱስም የሚመጣበትን ሁሉ አውቆ ወጣና ማንን ትፈልጋላችሁ አላቸው። የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ። እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር።እንግዲህ። እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ወደቁ።ደግሞም። ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም። የናዝሬቱን ኢየሱስን አሉት። ኢየሱስ መልሶ። እኔ ነኝ አልኋችሁ፤ እንግዲህ እኔን ትፈልጉ እንደ ሆናችሁ እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው አለ፤ይህም። ከእነዚህ ከሰጠኸኝ አንዱን ስንኳ አላጠፋሁም ያለው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ስምዖን ጴጥሮስም ሰይፍ ስለ ነበረው መዘዘው፥ የሊቀ ካህናቱንም ባርያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠ፤ የባርያውም ስም ማልኮስ ነበረ።ኢየሱስም ጴጥሮስን። ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው፤ አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣትምን? አለው። (ዮሐ 18_1_11) ጴጥሮስ የማልኮስን ጆሮ ለመቁረጥ በቂ ምክንያት ነዉ ያለዉ። ግን ልክ አልለበረም። ኢየሱስ ጎበዝ ብሎ አላበረታታዉም ወዲያዉኑ ሰይፍህን ወደ ሰገባዉ ክተት ነዉ ያለዉ። ተወዳጆች ከእኛ ልክ ካልሆነ አሳማኝ ከሚመስል ምክንያት ይልቅ የእግዚአብሔር ቃል መመሪያ ሁሌም ልክ ነዉ። ክፍል 2 ይቀጥላል .. #ከፀደቀ #መንፈሰ
Show all...
አንድ ሰዉ ስለ እግዚአብሔር ፀጋና፣ፅድቅ ተምሮ ታዲያ ሀጢአትን ብሰራ ምን ችግር አለዉ? ብሎ ካሰበ ትምህርቱ በፍፁም አልገባዉም። በክርስቶስ መፅደቃችን በገባን ልክ ራሳችንን ለፅድቅ ተገዢዎች አድርገን ለማቅረብ እንተጋለን። #ከፀደቀ #መንፈሰ
Show all...
ዶ/ር መለሰ ወጉ ከ50 በላይ ቤተ ክርስቲያናትን ተክሏል! ከ60 ዓመት በላይ ወንጌልን አገልግሏል! ከ30 በላይ መጻሕፍት ጽፎአል! ከ30 በላይ መለስተኛ መጻሕፍት ዐሳትሞአል! ከ200 በላይ "የሕይወት መስታውት" መጽሔት ጽሑፎች!(በመጽሔቶቹ የታተሙት ጽሑፎች ሁሉ የእርሱ ናቸው):: ከ400 በላይ በካሴትና በሲዲ የተዘጋጁ ትምህርቶች አስተላልፎአል! " በመልካም የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች፥ ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።" (1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 5:17)
Show all...
#አሳዛኝ_ዜና😭😭 በተለያዩ ዝማሬዎቹ የተባረክንበት ዘማሪ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ አለም በሞት ተለይቶ ወደሚወደው ጌታ ሄዷል። የሄደው ወደጌታ ቢሆንም የሚወዱት ሲለይ ያሳዝናልና ለወዳጅ ዘመዶቹ ፣ ለቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን....
Show all...
" እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤" (ወደ ቲቶ 3: 5)
Show all...
ፓስተር ቴዲ ሆኗል
በብዙ ዝማሬዎቹ የምናውቀው እንዲሁም በቤተክርስቲያን ውስጥ በዝማሬዎቹ አማኞችን የሚባርከው ዘማሪ ቴዲ ታደሰ መጋቢ ወይም ፓስተር ቴድሮስ ታደስ ተብሎ ተሹሞል። እግዚአብሔር በፊቱ የተሳካ የአገልግሎት ዘመን እንዲሰጠው እንመኛለ። መጋቢ ቴዲ እንኳን ደስ አለህ
Show all...
#ያላመኑ_ሰዎች_መንፈስ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው ሕብረት አንጻር ሙት እንጂ ፍጽሞ ሙት አይደሉም በማያመን ሰው ውስጥ ያለው የሰው መንፈስ በክርስቶስ ሲያምን ሕያው የሚሆን ሙት አይደለም ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የማያምኑ ሰዎች ሕያው የሆነ ሆኖም ዓመጸኛ መንፈስ እንዳላቸው መናገሩ ግልጽ ነው፡። ለምሳሌ የሐሴቦንን ንጉሥ የሴዋንን መንፈስ "እግዚአብሔር አደንድኖት " ነበር (ዘዳ 2:30) ወይም ናቡከደነፆር መንፈሱ ደንድኖ ልቡ በእብሪት ተሞልቶ ነበር(ዳነ 5:20) ወይም ታማኝ ያልሆኑት የእስራኤል ሕዝብ እልከኞችና ዓመጸኞች ከመሆናቸው የተነሳ "መንፈሳቸው በእግዚአብሔር የማይታመን ነበር " መዝሙር 78:8) ሐዋርያው ጳውሎስ "መንፈሳችሁ ከጽድቅ የተነሳ ሕያው ነው "(ሮሜ 8:10) ስል "ለእግዚአብሔር ሕያው " መሆንን ለመግለጽ ነው እንጂ መንፈሳችን በፊት ፈጽመ "ሙት" ነበር ለማለት አይደለም በእርግጥ መንፈሳችን ከእግዚአብሔር ጋር ምንም ዓይነት ኀብረት ስለሌለው በዚያ አንጻር ሙት ነበር። በተመሳሳይ ሁኔታ ሁላችንም በሁለንተናዊው ሰውነታችን በበደላችን በኃጢአታችን ምክንያት ሙታን ነበርን (ኤፌ 2:1) ነገር ግን በክርስቶስ ኢየሱስ ለእግዚአብሔር ሕያዋን ሆነናል ስለዚህ ለኀጢአት ሞተን ለእግዚአብሔር ሕያዋን እንደሆንን ራሳችንን እንቆጥራለን ሮሜ 6:11 :; አንዱ የሰውነታችን ክፍል (መንፈስ )ተብሎ የሚጠራው) ብቻ አይደለም ሕያው የሆነው እኛ በሁለንተናችን በክርስቶስ "ዐዲስ ፍጥረት "ነን 2ቆሮ 5:17።
Show all...
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ፃዲቅ ክፍል 5 #ፅድቁ #ተቆጥሮልኝ #ፃድቅ #ሆንኩኝ #ከፀደቀ #መንፈሰ ቀን 20:07:2016
Show all...
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 4 #ፅድቅን #የተከተሉ #እስራኤላዉያን #ከፀደቀ #መንፈሰ ቀን 17_07_2016
Show all...
❤🤔🤔🤔ወዮልኝ ❤🤔🤔              እኔ ወንጌልን ላረሳ ኪዳን የገባሁት ሞትና ትንሳው አውጃለሁ ያልኩት ከደሙ ጠጥቼ ስጋው የቆረስኩት           እኛ ከበላን እንጀራህ ከጠጣን ፅዋህን ልናወራው ሞትህ የመስቀል ፍቅርህን ነበረ ኪዳኑ ልናውጅ ድምፅህን በጫት በሲጋራ በሀሺሽ ተይዞ ወንድሙን በመጥላት በቂም ተመርዞ ኑሮ ለመረረው ግራ ገብቶት ላለው ችላ አትበለው ለርሱም ጥሪ አለው በልባችን አምነን በአፋችን መስክረን በሞት ለሚነዱት የህይወት ሽታ ሆነን እንድንኖርለት ነው ጌታ የነገረን ታያ ምን ሆነንነው ኧረ ምን ነክቶን ነው ከመመስከር ይልቅ ዝምታ የመረጥነው ከወንጌሉ በላይ ክብር ያስቀደምነው የምስራች ትተን ለስጋ ከኖርን ከመመስከር ይልቅ ካስቀደምን ክብር ወዮ እንበል ያኔ ወገን ከምድር የወንድሜ መሞት በእሳት መግባቱ እኔው ካልነገርኩት ሳይመጣ ንዳዱ በፍፁም አይቀርም በሲዖል መንደዱ በስጋ የወለደኝ ያ ውዱ አባቴ አምጣ የወለደች ያቺ ውብ እናቴ የተሸከመችኝ የኔዋ እህቴ ከልቡ የመከረኝ መካሪው ወንድሜ ለሲዖል ሲጣሉ ኧረ እንዴት ያስችለኝ ማረፍያ የሆነ መድሀኒት እያለኝ አዋጅ ብዬ ልውጣ እነሱም ያምልጡ ለጥልቁ ያ ገዢ ታልፈው ሳይሰጡ ወደ እቅፉ ይግቡ ከደሙ ይጠጡ በወንጌል አላፍርም ብለህ የገባኸው ልትሰብከው በአፈህ ኪዳን ያደረከው ወዮ ያኔ ጉድህ እሱን ችላ ካልከው ተነስ ተነሽ ተነስ ተነሽ አብረን እንነሳ የቲጂ አቤኒ የእናቱ ብሩክ
Show all...
ቆየት ያሉ እና አዳዲስ የአምልኮ መዝሙሮች ይፈልጋሉ?  እንግዲያስ አድሱን የአምልኮ መዝሙሮች የምገኙበትን ቻናላችንን ይቀላቀሉን👇👇 https://t.me/+Kr8zEBYUAR4yNjA8 አሁኑኑ ይቀላቀሉን ከኛ ጋር ጌታን ያምልኩ
Show all...
🎶 የአምልኮ መዝሙሮችን ለማግኘት🎶
መንፈሳዊ ግጥም ለማግኘት✅
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 2 የእኛ ፅድቅ በእግዚአብሔር ፊት #ለመፅደቅ #ፅድቅን #ያዋጣ #የለም #ከፀደቀ #መንፈሰ ቀን 28_06_2016
Show all...
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 3 #ፅድቃችን #በእግዚአብሔር #ፊት እግዚአብሔር #ጻዲቅ ነዉ ማነዉ በፊቱ #የሚቆመዉ? ቀን 2_07_2016
Show all...
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 1 የእግዚአብሔር ፅድቅ ክርስቶስ አጸደቀን #ከፀደቀ #መንፈሰ ቀን 24_06_2016
Show all...
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 1 የእግዚአብሔር ፅድቅ ክርስቶስ አጸደቀን #ከፀደቀ #መንፈሰ ቀን 24_06_2016
Show all...
ርዕስ #ቃሉን #ላከ #ከፀደቀ #መንፈሰ ቀን 21_06_2016
Show all...
የብዙሀኑን መልእክት እና ኮሜንት አይተናል። በቅንነት የመለሳችሁ እግዚአብሔር ይባርካቹ እያልን የተሳለቃችሁ ደግሞ 1ሳሙ 2:12-17 ጋብዘናቹሀል። መዝሞሩ መፅሀፍ ቅዱሳዊ ሲሆን ሀሳብም ከታች ባለው የቃል ክፍል ጋር የተያያዘ ነው። “ደግሞም ስቡን ሳያቃጥሉ የካህኑ ሎሌ መጥቶ የሚሠዋውን ሰው፦ ጥሬውን እንጂ የተቀቀለውን ሥጋ ከአንተ አይወስድምና እጠብስለት ዘንድ ለካህኑ ሥጋ ስጠኝ ይለው ነበር።”   — 1ኛ ሳሙኤል 2፥15
Show all...
ወንጌላዊ ኤርሚያስ አበበ በጠና ታሟል❗️
ለረጅም ጊዜ በወገቡ ላይ በደረሰበት ከፍተኛ የነርቭ ችግር ለረጅም ጊዜ ሲሰቃይ ቆይቷል። አሁን ባለበት በኒውዚላንድ ነጻ ህክምና ቢኖርም ካለው ወረፋ የተነሳ የወንድማችን ህመሙን ሊቋቋመው የሚችለው አልሆነም። ስለዚህም በግል ሆስፒታል አሊያም ህክምና ሊያገኝ ወደሚችልበት ስፍራ ሄዶ መታከም ስላለበት፣ ወጭውም ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ሁላችንም የጌታን ፍቅር እንድናሳይ እንድናሳክመው እንጠይቃችኋለን። የሚል መረጃ አየተዘዋወረ ይገኛል እኛም የበኩላችን እንወጣ። ጎፈንድሚ https://gofund.me/8909ff30 ማንኛውም ክርስቲያናዊ መረጃ እንዲያመልጣችሁ አናደርግም መረጃም ካላችሁ በinbox ማለትም @Gift29 ላኩልን እናሳውቃለን❤ @Markengera
Show all...
ሙሽራው ይመጣል
Show all...
ፍትህ ለአፋር ቅዱሳን!
ይህንን መልእክት ሼር በማድረግ ለአለም እናሳውቅ🙏 ማንኛውም ክርስቲያናዊ መረጃ እንዲያመልጣችሁ አናደርግም መረጃም ካላችሁ በinbox ማለትም @Gift29 ላኩልን እናሳውቃለን❤ @Markengera
Show all...
ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። የዮሐንስ ወንጌል 14:6
Show all...
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕራፍ 1) ---------- 6፤ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ። 7፤ በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት። 8፤ ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን። 9፤ በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤ 10፤ በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።
Show all...
Singer wubahet Tilahun ስንት ጊዜ https://youtube.com/watch?v=R15UkEo5dgA&si=9Bbk2DBDs8xJtKmT
Show all...
.          አሀዱ እላለሁ በረከት ተስፋዬ || New Clip ❤️❤️❤️ sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ https://t.me/joinchat/AAAAAEc7LsLkjQ-Xk3eBOA
Show all...
#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_10_5_2016_አ/ም " ኢየሱስም መልሶ ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው ። " የዮሐንስ ወንጌል 3 : 3 ዳግመኛ መወለድ ምን ማለት ? በድጋም ወደ እናታችን ማህፀን ገብተን መወለድ ነው ወይ ? እንደዛስ ማድረግ ይቻላል ወይ ? ዳግመኛ የምንወለደው ከምንድ ነው ? መልሱ በአጭሩ ይህ ነው 👇👇👇 " ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም ። "   የዮሐንስ ወንጌል 3 : 5 የእግዚአብሔር ልጅ መሆን የምቻለው ና መንግስቱን መውረስ የምቻለው በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ዳግመኛ በመውለድ ብቻ ነው ።              #በመልካሙ_የቀረበ
Show all...
#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_9_5_2016_አ/ም " ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ አለ ።  እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ ። " የዮሐንስ ራእይ 22 :11- 12 እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ነፃ ፈቃድ ሰጥቶታል ። ፈቃደኛ ሳይሆን የግድ እንድከተለው አይፈልግም  ። ይበጀኛል ፣ ያወጣኛል የምለውን መንገድ መርጦ የመከተል ነፃነት ተሰጥቶል ። ነገር ግን የምበጀው ና የምያወጣው መንገድ የቱ እንደ ሆነ እግዚአብሔር አምላክ ፍንጭ ሰጥቶቷል ፤ የምያወጣውን  መንገድ አሳይቶቷል ፤ ሆኖም በግድ ግን  ተከተለኝ አይልም  ፤ በፍቅር ና በውዴታ እንጂ ። ለዚህ ነው መጽሐፍ "ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ " የምለው ምክንያቱም በመጨረሻ ቀን ላደረጋት ለእያንዳንዱ ነገር ዋጋውን ይቀበላል ። ጻድቅ የጽድቅን ዋጋ ስቀበል አመጸኛውም የአመጹን ዋጋ ይቀበላል ። ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክ ነፃ ፈቃድ ሰጥቶኛል ብለን ከእርሱ መንገድ ፈቀቅ ብለን ነገ እንዳንፀፀት ዛሬ በጊዜ እንመለስ ።                   #በመልካሙ_የቀረበ
Show all...
Hillina Kassahun (ፍለጋ) Filega New song sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ https://t.me/joinchat/AAAAAEc7LsLkjQ-Xk3eBOA
Show all...
Hillina Kassahun (ፍለጋ) Filega New song
Show all...