cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ወንጌል ለዓለም🔈🌎

''And he said to them, Go into all the world, and preach the gospel to every creature. Mark 16:-15 እንዲህም አላቸው ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ማርቆስ 16:-15 የተመሠረተበት ቀን (ግንቦት 08/09/2012) ለአስተያየት @Geruuu ላይ inbox.

Show more
Advertising posts
5 447Subscribers
+124 hours
-137 days
-4130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አራት መነኩሴዎች ከሚኖሩበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ ጉዞን ይጀምራሉ፣ አርፍደዉ ስለተነሱ የፈለጉበት ቦታ በጊዜ ስላልደረሱ፣ እዛዉ በደረሱበት ቦታ አረፍ ብለዉ ለመሄድ ይወስናሉ፡ ሰዓቱም ስለመሸ ምሽቱንም ባሉበት ቦታ ድንኳን ይዘዉ ስለነበር ድንኳናቸዉ ዘረጉ። ከመተኛታቸዉ በፊት ለመፀለይ ይስማማሉ ከመፀለያችን በፊት አንድ ህግ እናዉጣ አለ አንደኛው መነኩሴ ይህም ህግ ሁላችንም የምንፀልየዉ በዉስጣችን ነዉ ምን አይነት ነገር ቢፈጠር ማዉራት አይፈቀድም አለ፣ የቀሩት ሁሉም በወጣዉ ህግ ተስማምተዉ በዉስጣቸዉ ድምፅ ሳያሰሙ መፀለይ ይጀምራሉ። በጣም ስለጨለመ በድንኳናቸዉ ዉስጥ ሻማ ለኩሰዉ ነበር የሚፀልዮት። ትንሽ እንደቆዮም ከዉጪ በመጣ ንፍስ እየበራ የነበረዉ ሻማ ያጠፍዋዉ። አንደኛዉ መነኩሴ ከመካከላቸዉ ወይኔ ሻማዉ እኮ ጠፍ አለ፣ ሁለኛዉ መነኩሴ ቀበል አድርጎ በፀጥታ ነዉ መፀለይ ያለብን አለ፣ሶስተኛዉ ደግሞ እባካችሁ ዝም እንበል ያወጣነዉን ህግ እየጣሳችሁ እኮ ነዉ አለ፣ አራተኛዉ መነኩሴ በመጀመሪያ ፈገግ ብሎ እኔ ብቻ ነኝ ያላወራሁት አለ። ይህንን ታሪክ ያነሳሁት አንድ መልእክት ለማስተላለፍ ነዉ። በዚህን ጊዜ የአገልጋዮችን ስህተት ወደ social media ይዞ መጥቶ መተቸት የተለመደ ነዉ፣ በአስተምህሮ ወይም በልምምድ ስህተት ዉስጥ ያለን ሰዉ እንድንቃመዉ መፅሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ያስተምረናል 👉ፊል 3:2 ማቴ 16፡12 ገላ 5:5_11_12 1ዮሐ 2:22...... መፅሐፍ ቅዱስ ስህተትን እንድንቃወም ብቻ ሳይሆን የሚያስተምረን ስህተትን ስንቃወም አስቀድመን ማወቅ ስላለብን ነገር እንደ መመሪያ ያስተምረናል። ነገሩ ስህተት መሆኑን ብቻ ማወቅ ሳይሆን ያንን ስህተት የምናቀናበትን መንገድ አስቀድመን ማወቅ መቻል አለብን። ምክንያቱም በአሁን ሰዓት ስህተት የሆነን ነገር ለመቃወም በተሳሳተ መንገድ እየተቃወሙ ያሉ እየበዙ ስለመጡ። በቤተክርስቲያን ዉስጥ በአስተምህሮም ሆነ በልምምድ በስህተት መንገድ ያሉ አገልጋዮች ከመፅሐፍ ቅዱስ መምሪያ ዉጪ ስለሆኑ ነዉ። ከመመሪያው ዉጪ ሆነዉ የተሳሳቱትን የምንመልሳቸዉ በመመሪያዉ ነዉ። ስለዚህ የሳቱትን ለመመለስ የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያን ልንከተል ይገባል። ለእኛ ሲባል የሚሻር የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያም ሆነ ህግ የለም። ለምሳሌ መፅሐፍ ቅዱስ " ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" ይላል(1ኛ ጴጥ4:11) ይህ ለሁሉም ሰዉ የሚሰራ መመሪያ ነዉ። የተሳሳተን ሰዉ በመሳደብ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል በመናገር ነዉ ልናቀናዉ የምንችለዉ። እኛ ስንሳደብ የእኛ ስድብ ልክ ስለማይሆን።" ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።" ይላል መፅሐፍ ቅዱስ።እግዚአብሔር የአንደበታችንን ቃል ብቻ ሳይሆን የልባችንን motive (ምክንያት) የሚያይ አምላክ ነዉ የተሳሳተን ሰዉ ስንቃወም እርሱን ለመመለስና ገንዘብ ለማድረግ እንዲሁም በእዛ ስህተት መንገድ የሚሄዱትን ምዕመናንን ለማቅናት እንጂ የተሳሳቱትን ፈፅሞ ለመስበርና ለማጥፍት መሆን የለበትም " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የወደቁ አይነሡምን? የሳተስ አይመለስምን? "( ኤር 8:4) ይላል የሳቱት ቢመለሱ እኛ ለእነርሱ የሚመለስ ልብ እንዳለን እናረጋግጥ። ተሳስታችኋል የተባሉ ከስህተታቸዉ የተመለሱ እዉነተኛዉን አስተምህሮ የሚያስተምራቸዉ አጥተዉ ግራ በመጋባት ዉስጥ ያሉ በርካታ ሰዎች አሉ።😔 ስህተትን መናገር ብቻ ሳይሆን ከስህተቱ ለተመለሰ ሰዉ በፍቅር የሚያቅፍ እጅ ሊኖረን ይገባል።ለዚህ ደግሞ እዉነትን በፍቅር ልንይዘዉ ይገባል " ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን"(ኤፌ4:15) ስህተቱን ለመናገር እንደረበታነዉ ሁሉ እዉነተኛዉን አስተምህሮ ለማስተማር መትጋት አለብን። " እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። "(ዮሐ8:32) በስህተት የተያዘን ሰዉ ነፃ የምናወጣዉ በእዉነት ነዉ። 1+1 ሶስት አይደለም ፥4ትም አይደለም፥10ም አይደለም እያልክ ያልሆነዉን ከምትነግረኝ የሆነዉን 2 ብትነግረኝ ያልሆነዉን እኔ በቀላሉ እለያለሁ። አማኞች ስህተት የሆነዉ ነገር እንዲለዩ እዉነተኛዉን የእግዚአብሔርን ቃል እናስተምራቸዉ። ይህ ከላይ የገለፅኩላችሁ ስህተትን ስንቃወም መፅሐፍ ቅዱስ ከሚሰጠን መመሪያዎች በጥቂቱ ናቸዉ። መጀመሪያ ወዳነሳሁላችሁ ታሪክ ልመላሳችሁ፣ አራቱም መነኩሴዎች ያወጡትን ህግ ሽረዋል። አራቱም የሻሩት ልክ በሚመስል ምክንያት ነዉ፣ አንደኛዉ የሻማ መጥፍቱን እንዲያዉቁ ተናገረ ፥ሁለተኛው ደግሞ የወጣዉን ህግ ለተናገረዉ ሰዉ ለማስታወስ ተናገረ፥ሶስተኛዉ ደግሞ ሁለቱም ፀጥ እንዲሉ እንዳይናገሩ ተናገራቸዉ፥አራተኛዉ በስተመጨረሻ እኔ ብቻ አልተናገርኩም ብሎ አለመናገሩን ተናገረና ህጉን አፈረሰ። ተወዳጆች የእግዚአብሔር ቃል የሁላችንም መመሪያ ነዉ። አንድ አገልጋይ ከተሳሳተ ልንመልሰዉ የሚገባ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ አሳማኝ በሚመስል ምክንያት ግን ስህተት በሆነ መንገድ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ህግ በመሻር መሆን የለበትም። ጌታ ኢየሱስ ታልፎ በሚሰጥበት ምሽት ይሁዳ ጭፍሮችንና ከካህናት አለቆች ከፈሪሳውያንም ከሎሌዎችን ጋር በችቦና በፋና በጋሻ ጦር ሆኖ ወደ ኢየሱስ መጣ ኢየሱስም የሚመጣበትን ሁሉ አውቆ ወጣና ማንን ትፈልጋላችሁ አላቸው። የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ። እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር።እንግዲህ። እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ወደቁ።ደግሞም። ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም። የናዝሬቱን ኢየሱስን አሉት። ኢየሱስ መልሶ። እኔ ነኝ አልኋችሁ፤ እንግዲህ እኔን ትፈልጉ እንደ ሆናችሁ እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው አለ፤ይህም። ከእነዚህ ከሰጠኸኝ አንዱን ስንኳ አላጠፋሁም ያለው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ስምዖን ጴጥሮስም ሰይፍ ስለ ነበረው መዘዘው፥ የሊቀ ካህናቱንም ባርያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠ፤ የባርያውም ስም ማልኮስ ነበረ።ኢየሱስም ጴጥሮስን። ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው፤ አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣትምን? አለው። (ዮሐ 18_1_11) ጴጥሮስ የማልኮስን ጆሮ ለመቁረጥ በቂ ምክንያት ነዉ ያለዉ። ግን ልክ አልለበረም። ኢየሱስ ጎበዝ ብሎ አላበረታታዉም ወዲያዉኑ ሰይፍህን ወደ ሰገባዉ ክተት ነዉ ያለዉ። ተወዳጆች ከእኛ ልክ ካልሆነ አሳማኝ ከሚመስል ምክንያት ይልቅ የእግዚአብሔር ቃል መመሪያ ሁሌም ልክ ነዉ። ክፍል 2 ይቀጥላል .. #ከፀደቀ #መንፈሰ
Show all...
አንድ ሰዉ ስለ እግዚአብሔር ፀጋና፣ፅድቅ ተምሮ ታዲያ ሀጢአትን ብሰራ ምን ችግር አለዉ? ብሎ ካሰበ ትምህርቱ በፍፁም አልገባዉም። በክርስቶስ መፅደቃችን በገባን ልክ ራሳችንን ለፅድቅ ተገዢዎች አድርገን ለማቅረብ እንተጋለን። #ከፀደቀ #መንፈሰ
Show all...
ዶ/ር መለሰ ወጉ ከ50 በላይ ቤተ ክርስቲያናትን ተክሏል! ከ60 ዓመት በላይ ወንጌልን አገልግሏል! ከ30 በላይ መጻሕፍት ጽፎአል! ከ30 በላይ መለስተኛ መጻሕፍት ዐሳትሞአል! ከ200 በላይ "የሕይወት መስታውት" መጽሔት ጽሑፎች!(በመጽሔቶቹ የታተሙት ጽሑፎች ሁሉ የእርሱ ናቸው):: ከ400 በላይ በካሴትና በሲዲ የተዘጋጁ ትምህርቶች አስተላልፎአል! " በመልካም የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች፥ ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።" (1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 5:17)
Show all...
#አሳዛኝ_ዜና😭😭 በተለያዩ ዝማሬዎቹ የተባረክንበት ዘማሪ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ አለም በሞት ተለይቶ ወደሚወደው ጌታ ሄዷል። የሄደው ወደጌታ ቢሆንም የሚወዱት ሲለይ ያሳዝናልና ለወዳጅ ዘመዶቹ ፣ ለቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን....
Show all...
" እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤" (ወደ ቲቶ 3: 5)
Show all...
ፓስተር ቴዲ ሆኗል
በብዙ ዝማሬዎቹ የምናውቀው እንዲሁም በቤተክርስቲያን ውስጥ በዝማሬዎቹ አማኞችን የሚባርከው ዘማሪ ቴዲ ታደሰ መጋቢ ወይም ፓስተር ቴድሮስ ታደስ ተብሎ ተሹሞል። እግዚአብሔር በፊቱ የተሳካ የአገልግሎት ዘመን እንዲሰጠው እንመኛለ። መጋቢ ቴዲ እንኳን ደስ አለህ
Show all...
#ያላመኑ_ሰዎች_መንፈስ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው ሕብረት አንጻር ሙት እንጂ ፍጽሞ ሙት አይደሉም በማያመን ሰው ውስጥ ያለው የሰው መንፈስ በክርስቶስ ሲያምን ሕያው የሚሆን ሙት አይደለም ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የማያምኑ ሰዎች ሕያው የሆነ ሆኖም ዓመጸኛ መንፈስ እንዳላቸው መናገሩ ግልጽ ነው፡። ለምሳሌ የሐሴቦንን ንጉሥ የሴዋንን መንፈስ "እግዚአብሔር አደንድኖት " ነበር (ዘዳ 2:30) ወይም ናቡከደነፆር መንፈሱ ደንድኖ ልቡ በእብሪት ተሞልቶ ነበር(ዳነ 5:20) ወይም ታማኝ ያልሆኑት የእስራኤል ሕዝብ እልከኞችና ዓመጸኞች ከመሆናቸው የተነሳ "መንፈሳቸው በእግዚአብሔር የማይታመን ነበር " መዝሙር 78:8) ሐዋርያው ጳውሎስ "መንፈሳችሁ ከጽድቅ የተነሳ ሕያው ነው "(ሮሜ 8:10) ስል "ለእግዚአብሔር ሕያው " መሆንን ለመግለጽ ነው እንጂ መንፈሳችን በፊት ፈጽመ "ሙት" ነበር ለማለት አይደለም በእርግጥ መንፈሳችን ከእግዚአብሔር ጋር ምንም ዓይነት ኀብረት ስለሌለው በዚያ አንጻር ሙት ነበር። በተመሳሳይ ሁኔታ ሁላችንም በሁለንተናዊው ሰውነታችን በበደላችን በኃጢአታችን ምክንያት ሙታን ነበርን (ኤፌ 2:1) ነገር ግን በክርስቶስ ኢየሱስ ለእግዚአብሔር ሕያዋን ሆነናል ስለዚህ ለኀጢአት ሞተን ለእግዚአብሔር ሕያዋን እንደሆንን ራሳችንን እንቆጥራለን ሮሜ 6:11 :; አንዱ የሰውነታችን ክፍል (መንፈስ )ተብሎ የሚጠራው) ብቻ አይደለም ሕያው የሆነው እኛ በሁለንተናችን በክርስቶስ "ዐዲስ ፍጥረት "ነን 2ቆሮ 5:17።
Show all...