cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

azyrot አዚሮት

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
161Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አስከፊው ጥላ አድስ አበባ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ህጻናት ተማሪወችን ሳይቀር በጎሳ በማሰለፍ ኦሮሞ የሆኑትን የኦሮሞ መዝሙር እንድዘምሩ ያደርጋሉ። ከኦሮሞ ውጭ ያሉ ብሄሮች ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር እያዘመሩና በጎሳ በጎሳ እየከፋፈሏቸው እንደሆነ ተሰምቷል። ይህ አካሄድ ልክ የሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ ከመካሄዱ ቀድም ብሎ የተደረገ ዝግጅት ነበር።
Show all...
ታሪክን አጣቅሶ የሀገራችንን ህብረተሰብ የሚያውቅ ወላድ እናቶች ምን ያህል እንደሚከበሩና እንክብካቤ እንደሚደረግላቸው መገንዘብ አያቅተውም፡፡ ይህ ብቻም ሳይሆን የሰብአዊ መብት ህጎችም ሆኑ የሴቶች መብቶች በተለይም ለወላድ እናቶች ጥበቃ እንደሚያደርጉ ማንም የሚያውቀው ነው፡፡ ከአጠቃላይ ህጎችም በተለየ ኢትዮጵያ ፈርማና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማፀደቅ በህገ መንግስቱ አንቅፅ 9 ‹4› መሰረት የሀገሪቱ የህግ አካል ያደረገችው የተ.መ.ድ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ጥበቃ ስምምነት አንቀፅ 6 አካል ጉዳተኛ ሴቶች ሰለሚጠበቁላቸው መብቶች ደንግጓል፡፡ ባህልንና ህጎችን ብቻ ሳይሆን ህሊናንም የሚደፈጥጥ ድርጊት በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ጌዶ ዞን ዲላ ከተማ ጪጩ ጤና ጣቢያ መፈፀሙ ተሰምቷል፡፡ በወላድ እናት ዓይንሥውር ወ/ሮ ስምረት ጥላሁን ላይ የተፈፀመው ዘግናኝ ደርጊት በአንዲት ግለሰብ ላይ ብቻ የተፈፀመ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ሳይሆን በዚች ዓይነሥውር እናት በኩል በመላ ዓይነሥውራን ላይ የተፈፀመ አሰቃቂ ድርጊት ነው፡፡ በመሆኑም ማህበራችን አጥብቆ የሚያወግዘውና የሚኮንነው ድርጊት ብቻ ሳይሆን ምንም እንኳ የተወሰኑ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውና የዞኑ ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት አካላት ክትትል እያደረጉ መሆናቸውን ብንረዳም መጠየቅ ያለባቸው አካላት ከመጠየቅ እንዳይድኑ እስከመጨረሻው ድረስ ክትትላችንን እንቀጥላለን፡፡ የኢትዮጵያ ዓይነሥውራን ብሔራዊ ማህበር
Show all...
የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የውጤት አያያዝ እና የማለፊያ ነጥብን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁለት ዙር መሰጠቱ የሚታወስ ሲሆን÷ የውጤት አያያዝ እና የማለፊያ ነጥብም እንደየዙሩ የተለያየ ነው። በዚህ መሠረትም በመጀመሪያው ዙር ተፈታኞች የሲቪክስ ትምህርት ፈተና ውጤት ያልተያዘ ሲሆን÷ ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ መሆኑን ተመላክቷል፡፡ ለመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ 600፣ ለማህበራዊ ሳይንስ ከ 500፣ ለአይነ ስውራን ተፈታኞች ከ 400 ተይዟል፡፡ ለሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ደግሞ ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ 700፣ ለማህበራዊ ሳይንስ ከ 600፣ ለአይነ ስውራን ተፈታኞች ከ 500 ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት መያዙ ተገልጿል፡፡
Show all...
የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር ኢትዮጵያን አያውቃትም ወይ? * የትምህርት ሚኒስቴር የአገር ተስፋ የሆኑ ወጣቶችን መፃዒ እድል ባልተገባ ሁኔታ መዝጋቱ እጅግ አሳሳቢ ነው። ከዓመት በላይ በኮሮና ምክንያት ትምህርት ዘግታ በነበረች አገር፤ ሁለመናዋን የአገር አንድነትና የሕዝብን ደኅንነት በማስቀጠል ላይ አንጠልጥላ ስትማስን በነበረች አገር ውስጥ፤…በአራቱም የኢትዮጵያ ማዕዘናት ወጣቶች ከደብተርና መጽሐፍ ይልቅ በወራሪ የሽብር ቡድኑ ስለተያዙ ከተሞችና ጋራዎች በማብሰልሰል ጭንቅ ጥብብ ሲሉባት በነበረች አገር፤…የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ተፈታኞች የጦር መሣሪያ አንግተው ላይ ታች ሲባዝኑ ባጅተው ጓደኞቻቸውን ቀብረው በሕይወት የተረፉት በሚሊታሪ ዩኒፎርም ለፈተና ተቀምጠው…እያለ…በሰላሙ ጊዜ ሆኖ የማያውቀውን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥቡን ከፍ ማድረግ፦ 1) በወጣቶች ሕይወት መቀለድ ነው። 2) ወጣቶቻችን ታላላቆች ልዩነታቸውን በሰለጠነ መንገድ መፍታት ባለመቻላቸው፤ የታላላቆቹ ስንፍና ሰለባዎች እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው። 3) ወጣቶች የአገራቸውን አንድነት ለማስቀጠል የከፈሉትን ተሳትፎ የሚያኮስስ ነው። 4) የትምህርት ሚኒስቴር በፈተና ወቅት ችግር አልገጠመኝም፤ «ፈተናው በሰላም ተጠናቋል» የሚል መግለጫ ከሰጠ በኋላ የሲቪክስ ፈተና እንዳይያዝ የወሰነበት አግባብም ልክነት የጎደለውና ተጠየቅ ያለበት ነው። የአገራችሁ ነገ የሚያሳስባችሁ፤ በተለይም ወላጆች ጉዳዩን በዋዛ ሳታዩት እስከመጨረሻው ድረስ በመታገል፤ ትምህርት ሚኒስቴር የወሰነውን ውሳኔ ዳግም እንዲያጤን በምታደርጉት ሂደት በተገቢው ሁሉ ከወላጆችና ከተማሪዎች ጎን የምቆም መሆኑንም መግለጽ እፈልጋለሁ። 📝ክርስቲያን ታደለ
Show all...
ምነኛ መታደል ነው? ጫጫታው ግርግሩ፤ ሁካታው ሽብሩ፤ ረሃብ ቸነፈሩ፤ ስደት ስናይፐሩ፤ ቂም በቀል ነገሩ በመላባት በዚህች አለም ከማውራት ከመናገር ታቅቦ፤ ችሎ ማለፍን፤ መታገሥን በህይወት ተገንዝቦ መቆየት እውነት እንዴት ያለ ልብ ቢኖር ነው? በተኩላዎች ከተማ በግ፤ በእኩዮች በክፉዎች ዘመን ደግ ሆኖ ማረፍ እንዴት ያለ መመረጥ ነው? እንደ ሊቁና ቅዱሥ ዮሃንስ አፍወርቅ ቤቱን ወደ ገዳምነት የቀየረበትን እምነት መቀዳጀት፤ የማትጠፋውን የሰውነትን እሣት ምላስን ከርችሞ፤ ልሣንን ለጉሞ እንዲህ በአርምሞ ኖሮ ከምድራዊ ድካም ማረፍ ምነኛ መታደል ነው? እኮ ምነኛ መሠጠት? ተዘከረነ እግዚኦ አምላከ አቡነ መርቆሪዎሥ በውሥተ መንግስትከ! የአቡነ መርቆሪዎስ አምላክ ተለመነን! ቅዱሥነትዎ! ቡራኬዎ ከምትወዷት ሀገርዎ ከኢትዮጵያና ከልጅዎችዎ ከህዝቧ ጋር ትኑር! በረከትዎ አይለየን! በሀጢዓት ባህር ለተዘፈቅሁ ለእኔ ለወልደትንሣኤ ለከንቱውና ለከርታታው ልጅዎ ይለምኑልኝ! አሜን! (ሰላም ለተፈጥሮና ለፍጡራን በሙሉ ይሁን!) አያሌው ተስፋዬ. https://t.me/joinchat/RuPmDA5drDKAAwxd https://t.me/joinchat/L50fVzoeFhsxYjZk
Show all...

(ከትልቅ ወይም ከትንሽ ቢሆን መወለድ ሙያ አይደለም፤ ራስን ለታላቅ ታሪክ መውለድ ግን ሙያ ነው)። ይህ በአራዳ ጊዮርጊስ አደባባይ በሚገኘው ለአጤ ሚኒሊክ መታሰቢያነት በሚል በተዘጋጀው ሀውልት በእግርጌ በኩል የሰፈረው ድንቅ አባባልና ዘመናችንን የሚዋጅ የበሰለ ንግግር ነው. በብሄር ስም የተደራጃችሁ ፓርቲዎችና፤ ለብሔራችሁ፤ ለጎሳችሁ የምታደሉ፤ ታሪክ እንደሰራ ራሳችሁን የምታታልሉ ሰዎች ሰምታችኋል! (ከትልቅ ወይም ከትንሽ ቢሆን መወለድ ሙያ አይደለም፤ ራስን ለታላቅ ታሪክ መውለድ ግን ሙያ ነው)። የተናገረውን የሚያደርግ፤ ያደረገውን የማይናገር ትሁት ንጉስ ዳግማዊ እምዬ ምኒልክ. በክፋት ላሰበው፤ ቀፎው እንደ ተነካበት እንደ ንብ መንጋ የሚወር፤ ሲያሸንፍ፤ ሲረታ ድል አደረግሁ ብሎ የማይኮፈስ የማይንቀባረር፤ ምርኮኞቹን ደግ እንደሰሩ አብልቶ አጠጥቶ ወደ ሀገራቸው በክብር የሚሰድ፤ ግፍ ለፈጸሙ ምህረትን ይቅርታን ማድረግ የሚወድ፤ ለማንዴላ ስርዓትን ያስተማረ፤ ጥቁር ህዝቦችን ያቀራረበ ያፋቀረ ድንቅ መሪ. ያቆየኽልን ኢትዮጵያ ለዘለአለም በአንድነት በፍቅር፤ በህብረት በክብር፤ ከፍ ከፍ እንዳለች ትኑር! አያሌው ተስፋዬ ነኝ. (ሰላም ለተፈጥሮና ለፍጡራን በሙሉ ይሁን!). https://t.me/joinchat/RuPmDA5drDKAAwxd
Show all...
ስለ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሐውልት! ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ፈረስ ላይ በግርማ ሞገስ ተቀምጠው የሚታየው ይህ ሐውልት፤ የተሰራው በልጃቸው ንግሥት ዘውዲቱ ጊዜ እንደሆነ የታሪክ መዛግብት ይጠቅሳሉ። ንግሥቲቱ ሐውልቱን ያሠሩት የአባታቸው የአፄ ምኒልክ ማስታወሻ እንዲሆን በማሰብ ነው። ሐውልቱ ሁለት ነገሮችን ያመላክታል፤ እነርሱም ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል እና የስልጣኔ ራእይ ናቸው። ሐውልቱ የተሰራው ከመዳብ ነው፤ የተቀረጸው ደግሞ በጀርመናዊው አርክቴክት ሃርትል ስፒንግለር ሲሆን፣ የተቀረፀው ጀርመን አገር ነው። ሐውልቱ በጀርመን አገር ተሠርቶ ከመጣ በኋላ የሚቆምበት ቦታ በዝግጅት ላይ እያለ ንግሥት ዘውዲቱ በድንገት መጋቢት 24 ቀን 1922 ዓ.ም. አረፉ። ነገር ግን የተጀመረውን ሥራ የንግሥቲቱን አልጋ የወረሱት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እንዲጠናቀቅ በማድረግ፤ በንግሥናቸው በዓል ዋዜማ ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም. በታላቅ ክብር ተገልጧል። አፄ ምኒልክ በሐውልቱ ላይ የሚታዩት ካባ ለብሰውና በእጃቸው ደግሞ ጣምራ ጦር ይዘው ነው። ይጋልቡበት በነበረው በፈረሳቸው በ‹ዳኘው› ላይ ተቀምጠው የሚታይ ሲሆን፤ ‹ዳኘው› በመባል የሚታወቀው ይኸው ፈረስ የሚታየው ፊቱን ወደ ሰሜን አቅጣጫ መልሶ፣ በኋላ እግሮቹ ቆሞ እና የፊት እግሮቹን ወደላይ አንስቶ ነው። ፊቱን ወደ ሰሜን አቅጣጫ የመመለሱ ጉዳይ ጦርነቱ የተካሄደበት ቦታ በሰሜን ኢትዮጵያ አድዋ መሆኑን ለማስታወስ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የአድዋ ጦርነት በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ በወራሪው የጣሊያን መንግሥትና በዳግማዊ አፄ ምኒልክ በሚመራው የኢትዮጵያ ጦር መሃከል የተካሄደ ጦርነት ሲሆን፣ ጦርነቱ በኢትዮጵያ አሸናፊነት በድል ተጠናቋል። የኢትዮጵያውያን ብሎም የአፍሪካውያን ኩራት ሆኖም ዛሬ ድረስ መዝለቁ እውን ነው። ሐውልቱ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በብዙ ዘርፍ ለአገር ትልልቅ ተግባራትን ያከናወኑ ንጉሥ በመሆናቸው ታላቅ ስራቸውን ለማንጸባረቅ የተቀረፀ እንደሆነ ይታወቃል። ጣሊያኖች ከአርባ ዓመታት በኋላ ዳግም ኢትዮጵያን በወረሩ ጊዜ ሐውልቱን አፍርሰው ቀብረውት የነበረ ቢሆንም፤ ከነፃነት በኋላ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሐውልት ከተቀበረበት ቦታ ወጥቶ እንደገና ታድሶና ተጠግኖ ቀድሞ በነበረበት ቦታ ሚያዝያ 27 ቀን 1934 ዓ.ም. እንዲቆም መደረጉን ከታሪክ መረዳት ይቻላል። (ሰላም ለተፈጥሮና ለፍጡራን በሙሉ ይሁን!) አያሌው ተስፋዬ. https://t.me/joinchat/RuPmDA5drDKAAwxd https://t.me/joinchat/L50fVzoeFhsxYjZk
Show all...
ወይ የዘንድሮ አድዋ! ወይ ድፍረት! ጣልያን እንኳን እንደዚህ አልደፈረችንም. እናንተዬ፤ ኦሮሚያን ልገንጥል እያሉ ሲወበሩ የነበሩ ወናጋም ኦነጎች መጀመሪያ ራሳቸውን ገንጥለው ነው ለካስ! ማል መናጋ፤ ትል ነበር እናቴ. ምን ይዘላብዳል፤ ለማለት. ፎኦኦኦኦኦ! ጉድ እኮ ነው! የሰማሁት በእውኔ ነው፤ ነው ወይስ በህልሜ፤ ጫካ ተወልዶ ያደገው፤ ቤቶፎቢያ ያለበት አራዊታም ቅንጭላት ቀጄላ መርዳሳ ጭራሽ ብሎ ብሎ አድዋን ያለ ሚኒሊክ እንድናስብ ፈለገ እንዴ! ኦነግን ያለ ታደሰ ብሩ፤ ያለ ዮሃንስ ለታ፤ ያለ ባሮ ቱምሳ ማሰብ ይቻለዋልን፤ መልሱን ለኦቦ ከጄላ ይቅርታ ቀጄላ ትቼዋለሁ. ጣልያን በገዛ ሀገሯ ለግራዚያኒ መታሰቢያ ሀውልት ለማቆም መንገድ ጀምራ ኢትዮጵያውያን ቁጣቸውን ሲያሰሙ ዳግም ሊገርፉን ነው እንዴ! በማለት ተንቦቅቡቀው ፕሮጀክቱን እንደተዉት የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው. ከመግለጫው በፊት ይህን ሊያስብ ይገባ ነበር. የቧልት ሚኒስትራችን አቶ ከጄላ መርዳሳ ቆም ብሎ ሊያስተውል በተገባው ነበር. ሻምበል አብዲሳ አጋ የኢትዮጵያ እንጂ የኦሮሚያ ጀግና አይደለም ለሚል ታሪክን በኩረጃ ተምሮ በኩረጃ ለሚያወራ ሰው ጆሮ መስጠትም አልነበረብንም! ክብረ በዓሉን ከአድዋ አደባባይ፤ ከቅዱስ ጊዮርጊሥ ቤተ-ክርሥቲያን ወደ አድዋ ድልድይ፤ ወደ ወንዝ ዳርቻ ወስዶ እንዲከበር ማድረግ ምን የሚሉት ነው፤ ዋቃ ጉራቻ፤ ሰግለን ቦረና እያለ በየዓመቱ ላልተፈታው ዲያቢሎስ ውሃ የሚረጨው አመሉ ብልጭ ብሎበት ይሆን፤ ነው ወይስ እኛ ተጃጅለንለት፤ እሺ ይሁን ብለን አድዋ ድልድይ ሄደን ስናከብር እሱ ደግሞ በጎን ሹልክ ብሎ የሚኒሊክን ሀውልት ሊያፈርሠው! የለም የለም የለም! አሁንም ጠቡ ከቅድሥት ቤተ-ክርሥቲያን፤ ከኦርቶዶክሥ ተዋህዶ ጋር እንደሆነ ፍንትው አድርጎ አሳይቷል! ይኼ እብሪቱ ግን የትም እንደማያደርሰው እሱም ያውቀዋል፤ እኛም እናውቀዋለን. የኢትዮጵያ ጥንታዊ የአርበኞች ማህበርን ግን ብራቮ! ቪቫ ብያለሁ. ወንዳታ! ወንድ ልጅ ቆረጠ ይሉሃል እንዲህ ነው. ፈሪ ሲያገኝ በአደባባይ ራሱን ዠግና አድርጎ ለሚኮፍሰው ለሚቆልለው ገለባ እንዲህ ማስተንፈስ ነው እንጂ! በእድሜ ትልቁ፤ በትምህርት ደረጃህ ትንሽ የሆንከው አቶ ኦቦ ክጀላ መርዳሳ ሆይ! እረፍ፤ ተጠንቀቅ፤ አድብ! ከምድር እስከ አርያም የተዘረጋችውን አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሠንደቅ ዓላማን ለብሠህ የመጣልህን ዝም ብለህ አትትፋ! በአንድ ወቅት ዶር ነጋሶ ጊዳዳን ቃለ መጠይቅ ሳደርግላቸው፤ ይቺ ሠንደቅ የኦርቶዶክስ ናት እንጂ የሌላው አይደለችም ብለውኝ ነበር. ምክንያቱም የኦነግና የሸኔ መስራች ስለነበሩ. እናማ ከአንተም የምጠብቀው አዲስና የተሻለ ነገር የለም! እንደዚያው ነው እንጂ! ለማንኛውም እንኳን ለ126ኛው የአድዋ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን፤ አደረሳችሁ! መልእክቱ ጣልያናዊውን ሚስተር ቀጄላን አይመለከትም! አያሌው ተስፋዬ ነኝ! ተጻፈ በ22/06/14 ዓ/ም.
Show all...
ከኢትዮጵያ የተዘረፉ የአብያተ ክርስቲያናት ቅርሶች በርካሽ ዋጋ በኢንተርኔት ለሽያጭ ቀርበዋል በጦርነቱ ወቅት ከበርካታ የትግራይ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ቅርሶች መዘረፋቸውን አረጋግጫለሁ" በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተዘርፈው ከአገር ሳይወጡ እንዳልቀሩ የተገመቱ በርካታ የአብያተ ክርስቲያናት ጥንታዊ ቅርሶች ኢቤይ እና አማዞንን በመሳሰሉ የኢንተርኔት የመገበያያ መድረኮች ላይ እጅግ በርካሽ ዋጋ እየተሸጡ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ከእነዚህ ቅርሶች ውስጥ ብዙዎቹ "ኢቤይ" በተሰኘው የኢንተርኔት ገበያ ላይ እንደቀረቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ፣ በሃይማኖት ተቋማት ላይ ጥቃት መፈጸሙና ጥንታዊ ቅርሶች መዘረፋቸው መዘገቡ አይዘነጋም፡፡ ቢቢሲ ኒውስዴይ በጉዳዩ ዙርያ ያነጋገራቸው የቋንቋ ታሪክ ተመራማሪና በሐምቡርግ ዩኒቨርስቲ የድኅረ ዶክትሬት ተማሪ የሆኑት ዶ/ር ሐጎስ አብረሃ፤ በጦርነቱ ወቅት ከበርካታ የትግራይ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ቅርሶች መዘረፋቸውን አረጋግጫለሁ" ብለዋል፡፡ በወቅቱ ከተዘረፉት ቅርሶች አንዳንዶቹ ጥንታዊና እጅግ ብርቅዬ እንደነበሩ ዶ/ር ሐጎስ አስረድተዋል። ተመራማሪው ከኢትዮጵያ የተዘረፉት ቅርሶች በብዛት እየተሸጡ ያሉበት ዋጋ እጅግ ርካሽ የሚባል እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ቅርሶቹ በዚህ ወቅት እንዴት ተዘርፈው ከአገር ሊወጡ እንደቻሉ ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም፣ በሱዳንና ኬንያ በኩል ወጥተው ሊሆን እንደሚችል ግን ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በኢቤይ የኢንተርኔት የግብይት መድረክ ላይ ባለፉት ጥቂት ወራት በርካታ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሃይማኖታዊ ቅርሶችን ለሽያጭ ካቀረቡት ድርጅቶች መካከል ዎርሌይ ኢንተርፕራይስ ኢንተርናሽናል ኤልኤልሲ ይገኝበታል። ድርጅቱ ለገበያ ካቀረባቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርጾች መካከል ከ15ኛው እስከ 17ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ በእጅ የተጻፈ ሃይማኖታዊ መጽሐፍ ይገኝበታል። በእንስሳት ቆዳ ላይ በግዕዝ ቋንቋ የተጻፈው ሃይማኖታዊ መጽሐፍ ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም በ240 ዶላር ለገበያ ቀርቧል። ከ15ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን ባሉት ዓመታት በግዕዝ ቋንቋ ሳይጻፍ አይቀርም የተባለለት መጽሐፍ ደግሞ በ1250 ዶላር ለሽያጭ ቀርቧል።
Show all...
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል። አቶ ታገሰ ፥ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ አዋጁ ለአፈ-ጉባኤውና ለአፈ-ጉባኤው ጽ/ቤት በሰጠው ስልጣን እንዲሁም በአዋጁ በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ከቀረቡት 632 ዕጩዎች መካከል 42ቱ መለየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀረቡ 42 ዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከአማካሪዎች ጋር ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንት ደግሞ የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት አመራር አካላት በሚገኙበት በዕጩዎች የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ ላይ ምክክር ተደርጎ ግብአት የሚሰበሰብ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በማስከተልም በም/ቤቱ ድረ-ገጽና በማህበራዊ ሚዲያ የእጩዎችን ማንነት በመግለጽ በቂ ግብአት ከተሰበሰበ በኋላ ሰብሳቢና ም/ሰብሳቢን ጨምሮ 11ዱ ዕጩ ኮሚሽነሮች ለም/ቤቱ ቀርቦ ከፀደቀና ዕጩዎች ከተሰየሙ በኋላ ወደ ስራ እንደሚገባም ገልጸዋል።
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!