cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ምክረ አበው

ትክክለኛው ቻናላችን ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን የአባቶቻችን ምክር በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኛ አይደሉም።

Show more
Advertising posts
10 263Subscribers
-224 hours
-27 days
+1930 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

📜ዘፍጥረት 2፥15-18📜 ------------------------------ 15.“እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው።” #ያበጃት_ይጠብቃትም_ዘንድ ፦ ስለዚህ ክፍለ ምንባብ ሰቨርያን እንዲህ ይላል «ይሰራና ይጠብቃትም ዘንድ የሚለው ሌባ ሳይኖር አላፊ መንገደኛም ሳይኖር ወይም ሆን ብሎ ክፉ የሚያደርግ ሰውም ሳይኖር ከማን ነው የሚጠብቃት? ከራሱ ነው የሚጠብቃት።ትእዛዙን ካልተላለፈ ገነትን አያጣትም፥ትእዛዙን መጠበቅ ለሰውልጅ ስራ ነው በዚህ ስራም ራሱን ይጠብቃል የተሰጠችውን ገነትንም ይጠብቃል» ሰውን በመልኩ እንደ ምሳሌው ከፈጠረው በኋላ በኤደን ወደ አዘጋጀለት ልዩ የአትክልት ስፍራ አስገባው። ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ 16.“እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ 17.ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።” የታዛዥነቱ መለኪያ ቀዳሚው ትእዛዝ ይህ ነው ዛፉ መርዛማ ሆኖ ወይም የሆነ ልዩ የዕውቀት ሃይል ኖሮት ሳይሆን ቁጥር 9 እንደተብራራው መልካምና ክፉ የተባሉት የመኖር ሁኔታዎች የሰው ልጅ ለተሰጠው ትእዛዝ ባለው ግብረ መልስ የሚወሰን ነው።ምክንያቱም መልካም ብቻ ነው የሚያውቀው ዛፏን አትንካት ተብሏል ካልነካትም በዚህ መልካምነት ብቻ ይኖራል፥ትእዛዙን ከተላለፈና ዛፏን ቢበላ ግን ክፉን ያውቃል ማለትም በሞት(ከእግዚአብሔር መለየት፥የስጋና የነፍስ መለያየት) መቀጣት መጎስቆልን ያውቃል።ክፉና መልካም የሚያስታውቅ መባሉ ስለዚህ ነው። ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ 18.“እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት።” #የሚመቸውን_ረዳት ፦ ረዳት ባርያ ወይም ተገዢ ሳይሆን በባህርይ በሙላት እርሱን የምታክል ሆና ለዓይኑ ደስ የምታሰኝ ከእርሱ ጋር በደስታ የምትነጋገር በሁሉም ከእርሱ ጋር የምትስማማ ለሁኔታውና ለፍላጎቱ በሙሉ መልስ የምትሰጥ... #እንፍጠርለት ፦ በምዕራፍ 1፥26 እንዳለው ትንታኔ በተመሳሳይ እዚህ ምንባብም እንጠቀመዋለን። እግዚአብሔር ሌሎች ፍጡራንን እያማከረ ሳይሆን፥ የመፍጠር ውሳኔ ምክረ-ሐሳብ ከራሱ ጋር ብቻ እንጂ ሌሎችን አላማከረምና በራሱ ከራሱጋር ማሰቡንና መወሰኑን የሚያሳይ ነው፥ ልክ እኛ እስኪ ዛሬ ይሄን ላድርግ ይሄን ልስራ ብለን በህሊናችን ከራሳችን ጋር እንደምንመክረው ነው።
Show all...
📜ኦሪት ዘፍጥረት 2፥11-15📜 _____ #ማስታወሻ ፦ የተለያዩ ትናንሽ ምንጮች በተለያየና ዝቅተኛ ወደሆነ ቦታ በመፍሰስ እየተቀላቀሉ #መጋቢ_ወንዝን ይፈጥራሉ፤እነዚህ የተፈጠሩት መጋቢ ወንዞችም እየተቀላቀሉ አንድ ትልቅ ወንዝ ይፈጥራሉ።ትላልቅ የተባሉት ወንዞችም ወደሌላ ቦታ እንደፈሰሱ ከነርሱ ለሚበልጥ ወንዝ መጋቢ ሊሆኑ ይችላሉ።ይህ በዘመናችን ያለ የወንዝ አፈጣጠር ሂደት ነው። የመጀመርያው ግን የተለየ ነበረ ከኤደን የሚፈልቀው ትልቁ ወንዝ ወደ አትክልቱ ስፍራ(ገነት) ገብቶ እንዳጠጣ ሌላ አራት ወንዞችን ፈጥሮ ይወጣል።እዚህጋ መጋቢው ትልቁ ወንዝ ነው። 🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊 11.“የአንደኛው ወንዝ ስም ፊሶን ነው እርሱም ወርቅ የሚገኝበትን የኤውላጥ ምድርን ይከብባል የዚያም ምድር ወርቅ ጥሩ ነው፤” #ኤውላጥ(ሐዊላ) ፦ በኩሽ ልጅ (ዘፍ10፥7) የተሰየመ በሲና አከባቢ ያለ አገር(ዓረቢያ) ነው።ከገነት የወጣው የወንዙ አንደኛው ክፍል(ፊሶን) በዚህ አካባቢ ይፈስ የነበረ። ------------------------------------ 13.“የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል።”   #ኢትዮጵያ ፦ ይህ በዕብራይስጡ የኩሽ ምድር ብሎ ነቢዩ ሙሴ የፃፈውን  ”ኢትዮጵያ” ተብሎ በግሪክኛ ሰባ ሊቃናት(septuagint) የተተረጎመ ነው።ፀሓፊው (ነቢይ ሙሴ) ቦታውን በቀጥታ ሲገልጥ፥የሰባ ሊቃናት ትርጉም ግን የፊትን ቀለም ስለሚገልፅ አሻሚ እሳቤ እንዲፈጠር አድርጓል።ምክንያቱም በግሪክኛ «ኢትዮጵያ» #ጥቁር ማለት ስለሆነ። ብዙ ሊቃውንት ደግሞ ወንዙ ከቪክቶሪያ ሃይቅ የሚነሳውና ዓባይን ጨምሮ ብዙ የብዙ ሃገራት ወንዞች እየመገቡት ወደ ግብፅ የሚፈሰው «የናይል-ወንዝ» ነው ብለው ተርጉመውታል።ነገር ግን ናይል ከጥፋት ውሃ በኋላ ባለው የመልክአ ምድር አቀማመጥ የተፈጠረ ወንዝ ስለሆነ ትርጓሜው አያስኬድም አመጣጡ ከኤደን እንደመሆኑ።ዞሮ ዞሮ ግዮን ወደ የአሁኑ አፍሪካ ይፈስ የነበረ ወንዝ ነው። -------------------------- 14.“የሦስተኛውም ወንዝ ስም ጤግሮስ ነው እርሱም በአሦር ምሥራቅ የሚሄድ ነው።” #አሦር ፦ በሴም ልጅ ዘፍ10፥11 የተሰየመና ነነዌ መናገሻውን ያደረገ የአሁኖቹ ኢራቅ፣ቱርክ፣ኢራን ወዘተ የሚያጠቃልል ግዛት ነው።ጤግሮስ(tigris,hiddekel) በዚህ ግዛት በስተምስራቅ የሚፈስ ወንዝ ነው። --------------------------- 15.አራተኛውም ወንዝ ኤፍራጥስ ነው።” ኤፍራጥስ ከአሶር በስተምዕራብ የሚፈስ ወንዝ ነው።እግዚአብሔር ለአብርሃም የሚሰጠው ርስት ድንበሩ እስከዚህ ወንዝ እንደሆነ ተጠቅሷል።👇👇 “በዚያ ቀን እግዚአብሔር ለአብራም እንዲህ ብሎ ቃል ኪዳን አደረገ፦ ከግብፅ ወንዝ ጀምሮ እስከ ትልቁ ወንዝ እስከ #ኤፍራጥስ_ወንዝ ድረስ ይህችን ምድር ለዘርህ ሰጥቼአለሁ፤”— ዘፍጥረት 15፥18
Show all...
ሰይጣን ክፉ ሰው ሊያደርግህ ሞክሮ ካልሆነለት መልካም ተግባራትን ያስተውሀል የማትፀልይ፣መፅሐፍ ቅዱስ የማታነብ፣ቅዳሴ ላይ የማትሳተፍ ወዘተ በማድረግ ለሌሎች ስጋዊ ተግባራት ለመዝናናት ምናምን ግን ግዜ ያለህ እንድትሆን ያደርግሀል ስለዚህ ስንፍናን ተዋጋ ከሰይጣን ነው!!
Show all...
ከ2016 ዓመታት በመላእክት የተሰበከው የምስራች “በመድሐኒትነቱ ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሆነ ክርስቶስ ጌታ ተወልዶላችኋል” የሚል ነው።የተወለደው መድሓኒት፥የሰው ልጅ እርሱን በማመን እንዲድን አብ ለዓለም የሰጠው የፍቅር ስጦታ ነው።ስለዚህ ስጦታ በልዕልና(አርያም) ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁን፥በምድርም ይህን ስጦታ ተቀብሎ የሚኖርበት የህሊና ሰላም ለሰውልጅ ይሁን አሜን!! እንኳን አደረሰን 😇😇 የሉቃስ ወንጌል 2:10 - 11 “መልአኩ ግን እንዲህ አላቸው፦ “እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ ታላቅ ደስታ የሚሆን የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ እነሆ! አዳኝ እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ዛሬ በዳዊት ከተማ ተወልዶላችኋልና።” የዮሐንስ ወንጌል 3:16 “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር ዓለምን እጅግ ስለ ወደደው አንድያ ልጁን ሰጠ።”
Show all...
ሐሳብ የስሜት ሕዋሶች ውጤት ነው...በልብህ የሚመላለሰውና የምታሰላስለው ነገር ከምትሰማው ከምታየው ከምትዳስሰው ወዘተ የተነሳ ነው። በልብህ ሲመላለስ ልማድ ከልማድ ቀጥሎ ፀባይህ(የስብእናህ መገለጫ) ወደ መሆን ያድጋል።ማንነትህ መንፈሳዊ እንዲሆን ሕዋሳትህ የእግዚአብሔርን መንፈስ(ፈቃድ) ይፈልጉ።
Show all...
ክርስቶስን በማመን መዳን የተባለው የዘላለም ህይወት እንዲሁም ጽድቅንና ቅድስናን በነፃ ከተሰጡት፤ አማኙ እነዚህን ለመጠበቅ እንደየ አቅሙ በቻለው መጠን #መጋደል ይጠበቅበታል። ስጦታ እንደመሆኑ እኛም ለስጦታው ግብረመልስ መስጠት ያስፈልገናል። ተጋድሎአችንም ከስጋችንና ከሰይጣን ጋር ነው። 🧠ስጋችን ከዚህ የእምነት ስጦታ እንዳይጎድል ክፉ መሻቱን በመግታት በጸሎት በመልካም ስራዎችንና እንደ ቃሉ ለመኖር ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ማድረግን እናለማምደዋለን እያለማመድንም ህብረቱ ን እናሳድገዋለን። 👹 ሰይጣንን ደግሞ በስጋ ዝለን ደክመን ይህን ስጦታ እንድንጥል ስለሆነ የሚዋጋን በአግዚአብሔር ቃል እየተቃወምነው እንዋጋዋለን። ይህን ስጦታ ለመጠበቅ እየወደቅክም እየተነሳህም ከስጋዊ ድካም እስክታርፍ (እስክትሞት) ድረስ ተጋድሎው ይቀጥላል።ተጋድሎው መገዛት ነው መገዛትም ፍቃዱን ማገልገል ነው። መልካምና ክፉ አገልጋይ የሚያስብለንም የጸጋ ስጦታውን ለመጠበቅ ለራሳችን ምን ሰራን የሚል ነው።
Show all...
እያንዳንዱ በምድር ላይ ያለ ሰው በተፈጥሮ ያገኘው ስጦታ አለው።ይህም ስጦታ በዓለም ላለው የሰው ልጅ አንዱ ለአንዱ የሚያገለግልበት ነው።ይህ ስጦታ እያንዳንዳችን እንደየአቅማችን መስራት የምንችለውና የተለያየም ነው።በዚህች ምድር ላይ ያለው የሰው ልጅ ለሚገጥሙት እያንዳንዳቸው ችግሮች መፍትሔው በሌላው ሰው እጅ ላይ ነው ስለዚህ እርሱ ባደለን ተፈጥሯዊ ስጦታ አማካይነት ፍላጎቱንና ፈቃዱን ስለምንፈፅም ሰውን ማገልገል ፈጣሪን ማገልገል ነው። ባለስልጣን ብንሆን ሐኪም፥መሃንዲስ ብንሆን ነጋዴ፥መምህር ብንሆን አማካሪ፥መንፈሳዊ አገልጋይ ብንሆን ፈላስፋ፥ዳኛ ብንሆን የፀጥታ አስከባሪ፥ገበሬ ብንሆን ተቀጣሪ ሰራተኞች፥ወላጆች ብንሆን የሃገር ሽማግሌዎች...ወዘተ ነገ ስጦታ በሚያድለው አምላክ ፊት ምን ሰራህበት ሌሎችን በማገልገል ምን አተረፍክበት ተብለን እንጠየቅበታለን!!ለሰው ልጅ ህይወት መቃናት በሞያችንና በአቅማችን መስራታችን ለእግዚአብሔር ክብር ነው። ስጦታ + ሐላፊነት =ተጠያቂነት ተፈጥሯዊ ስጦታ ሐላፊነት ነው ሐላፊነት ደግሞ የሚያሸልም ወይም የሚያስቀጣ ተጠያቂነት አለው። ሰውን በታማኝነት ማገልገል "አንተ የታመንክ አገልጋይ በትንሽ ታምነሀልና በብዙ እሾምሀለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ" የሚል የዘላለም የህይወት ቃል እንሰማበታለን።በአግባቡ የማያገለግል ግን አንተ ክፉ ሐኬተኛ የማይጠቅም አገልጋይ ተብሎ ወደ ጨለማ ይጣላል ስጦታውም ተቀምቶ ለሌላ በቅንነት ለሚያገለግል ትጨመርለታለች!! በዚህ ሳምንት ስለ ስጦታና አገልጋይነት ይሄንን ነው የምንማረው።
Show all...
#finding_of_the_true_cross ሮማውያን ወንጀለኛን በተለያየ ቅርፅ የተመሳቀለ እንጨት ግንድ ላይ ሰቅለው ይገድሉ ነበር።ቅርፆቹም ❕ አንድ ወጥ ግንድ ፦ ሁለት እጆቹ ተደራርበው ወደ ላይ ወጥረው ሁለት እግሮቹም ደራርበው በሚስማር ይቸነክሩበታል ❌ ተቃራኒ አቅጣጫ የሚመሳቀል ሁለት ግንድ፦ እጆቹና እግሮቹ እያንዳንዳቸውን ለየብቻ በተቃራኒ አቅጣጫ ወጥረው ይቸነክሩበታል #T ወደ ታችና ወደ ጎን የሚመሳቀል ሁለት ግንድ፦ ይህ የተለመደ መስቀያ ነበር ሁለት እጆቹና እሮቹ በሚስማር ይቸነክሩበታል ወይም ሁለቱ እጆቹ ወደ ተቃራኒ ኣቅጣጫ ኣስረው እግሩን ይቸነክሩበታል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል ለ288 ዓመታት አይሁድ ቀብረውት ስለነበረ እስከ አራተኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩት ክርስቲያኖች፥ክርስቶስ በየትኛው የመስቀል(መስቀያ) ግንድ ዓይነት እንደተሰቀለ ትክክለኛና አንድ አይነት መረጃ አልነበራቸውም።የንጉስ ቆስጠንጢኖስ(ኮንስታንቲኖፕል) እናት የሆነችው ቅድስት ሄለና(ኤለና:ኢለኒ) ባየችው ራዕይ መሰረት የክርስቶስን መስቀል የተቀበረበትን ቦታ ፈልጋ አግኝታና አስቆፍራ ካስወጣችው በኋላ ግን እውነተኛው የክርስቶስ መስቀል ታወቀ። በምዕራብና ምስራቅ በሮም መንግስት ግዛቶች ውስጥ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ነፃነትዋን በንጉስ ቆስጠንጢኖስ ከታወጀበት ጊዜ አንስቶም የምዕራብና የምስራቅ አብያተ ክርስቲያን ይህንን ቀን "የእውነተኛው መስቀል መገኘት-finding of the true cross" ብለው ያከብሩታል።በኛ መጋቢት 10 ይከበራል።
Show all...
#ትንሣኤ_ዘጉባኤ ⚠️የክርስቶስ መምጣት ቀርቧልና አለም ትገለበጣለች “ከበረሃ የመጣን ባሕታውያን ነን” የሚሉ ብዛታቸው... እውነተኛው በመፃሕፍት ያለው ሳይሆን ተለምዷዊው የሙታን ትንሣኤ ትምህርት “ #ሁሉም ሰው ሞቶ ይነሳል” የሚል ትምህርት በር ከፍቶላቸዋል።ስለዚህ ሲያስተምሩ “አለም ግልብጥብጥ ትልና ሁሉም ሰው ይሞታል ከዛ ክርስቶስ ይመጣል፡ክርስቶስ እንዲመጣ በአለም ያለው ሁሉም ሰው መሞት ግድ ነው ሞት መቅመስ አለበት!!” ይላሉ። መድረክ ያገኘ እንደራሱ እሳቤ ብዙ ያልተፃፈ መናገር ልማድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ግን እንዲህ አላስተማረችም!!ታድያ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ምን ይላል የሚለውን ስናይ:- ⚠️በርግጥ ጌታችን ኢየሱስ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ድርቅ፣ወረርሺኝና ጦርነት ለመምጣቱ #ምልክት እንደሆኑ ተናግሯል። በነዚህም ክስተቶች ሰው እንደሚሞትም የታወቀ ነው ነገር ግን ሁሉም ሰው ሞቶ ያልቃል አላለም።ይልቁን ክርስቶስ መጥቷል በዚህ አለ ቢሏችሁ እንዳታምኑ የመብረቅ ብልጭታ ለሁሉም እንደሚታይ እኔም ለሁሉ በግልጥ እየታየሁ በብዙ ክብር በደመና ነው የምመጣው ነበር ያለው። (ማቴ 24፥24-31) ስለዚህ ጌታችን ክርስቶስ ዳግመኛ እኪመጣ ድረስ የሰው ልጅ እየተባዛና እየሞተ ኑሮው ይቀጥላል። ሲመጣም ሞት ያቆማል የሞቱም ሰዎች ይነሳሉ በሕይወት የነበሩትም የማይሞቱ በአንድነትም ዘለአለማውያን ወደመሆን ይለወጣሉ።ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን የጌታችን ኢየሱስ መምጣትና የሙታን ትንሣኤ በሁለት መልእክታት አጠር አድርጎ በደምብ ገልፆታል። 📜1ኛ ቆሮንቶስ 15 ⁵¹-⁵² እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን #አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው #ይነሣሉ እኛም #እንለወጣለን ። ⁵³ ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና። ⁵⁴ ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ፦ ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል። 📜በተጨማሪም የተሰሎንቄ መልእክቱም ይህንን ያጠናክራል 1ኛ ተሰሎንቄ 4 ¹⁶ ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤ ¹⁷ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን። ¹⁸ ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። 📖መደምደሚያ:- የቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ትምህርት በአጭሩ ይህ ነው።ምድርና ሰማይ የሚጠፉት ከተነጠቅን በኋላ ነው።እስከዛው ፍጥረት ሁሉ እንዲህ አሁን እንዳለው ይቀጥላል። “በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።”
Show all...