cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Ethiopian lawyers association /ELA/

This is a discussion forum for all Ethiopian lawyers, including law lecturers, attorneys, judges, law students...

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
477Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ህግ የመተርጎም ተግባር በዘፈቀደ የሚካሄድ እንዳይሆን የህግ አተረጓጎ መርህዎች አስፈላጊ መሆናቸው ተጠቆመ *********************** የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ከብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ህግ የመተርጎም ተግባር በዘፈቀደ የሚካሄድ እንዳይሆን ጥንቃቄ የሚያስፈልግ በመሆኑነ ምክንያት የህግ አተረጓጎምን የሚመለከቱ መርሆዎች መኖር አስፈላጊ ናቸው ሲሉ በራዲሰን ብሉ ሆቴል በህግ ጉዳይ የተጻፉ መጽሐፍት ላይ በተዘጋጀ የትንተና እና የትችት መርሃ ግብር ላይ ገለጹ፡፡ በዳኝነት አካል አማካኝነት የሚከናወን ሕግ የመተርጎም ተግባር ሁለት ዋና ዋና ክንዋኔዎችን ያቀፈ ነው ያሉት ክብርት ፕሬዝደንቷ አንደኛው የተመረጠውን ሕግ ድንጋጌ ዳኝነት ሊሰጥበት ከተዘጋጀው ጉዳይ ፍሬ ነገሮች ጋር በማዛመድ ውሳኔ መስጠት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በህጉ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉ ቃላት እና ዓረፍተ ነገሮች የግልጽነት መጓደል፣ አሻሚነት፣ የመሳሰሉ ችግሮች ሲያጋጥሙ፣ ጥያቄ የተነሳበትን ጉዳይ በተመለከተ ከተሰጡ አማራጭ ሃሳቦች መካከል ሕጉ ከታለመለት ዓላማ ጋር አብሮ የሚሄደውን ሃሳብ በመምረጥ ውሳኔ መስጠት ነው በማለት አብራርተዋል፡፡ የመጽሐፍ ትንተና ፕሮግራሙ የጆናሲዮ አማካሪ ድርጅት ከመሰረት ስዩምና ጓዶቿ የህግ ቢሮ እና ከኢትዮጵያ የህግ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በጋራ በመተባበር የተዘጋጀ ነው፡፡ በመጽሃፍ ትንተና ፕሮግራም ላይ በአቶ ተስፋዬ ነዋይ “ሕግ እና አተረጓጎሙ” እና በአቶ አብርሃም ዮሐንስ “የአስተዳደር ህግ መግቢያ” በሚል ርዕስ በተጻፉ መጽሐፍት ላይ ትንተና ተሰጥቷል፤ ትችትም ቀርቧል፡፡ በህግና አተረጓጎሙ መጽሐፍ ላይ በፕሮፌሰር ጥላሁን ተሾመ እና በዶ/ር ጌታሁን ካሳ ትንተናና ትችት የቀረበ ሲሆን ሁለቱ የህግ ምሁራን መጽሃፉ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ በርካታ ጠቃሚና አወንታዊ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ፍሬ ነገሮችን የያዘ መሆኑን ጠቁመው አቶ ተስፋዮ ነዋይ ለተማሪዎችና ለተመራማሪዎች እዲሁም በህግ ዘርፍ ግንዛቤ ለሌላቸው አንባብያን አስተማሪና ሊጠቀስ የሚችል መጽሃፍ በመጻፋቸው እንኳን ደስ አለዎት በማለት ትንተናቸውን/ ትችታቸውን በሁለት እይታ በመክፈል አቅርበዋል፡፡ የተንታኞቹ የመጀመያሪያ እይታ በመጽሃፉ አደረጃጀትና አቀራረብ ላይ ትኩረት ያደረጉ ሲሆን ሁለቱም ተንታኞች መጽሃፉ የፊደል፤ የሰዋስው እና የይዘት አደረጃጀት ቅደም ተከተል መጠነኛ ችግሮች ያሉበት መሆኑን አንስተዋል፡፡ በሁለተኛው እይታቸው በመጽሃፉ ፍሬ ነገር ይዘት ላይ ትኩረት አድርገው ትንተና ሰጥተዋል፡፡ ከዚህ አንጻር መጽሃፉ ከህግ እና አተረጓጎም ጽንሰ ሃሳብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ያነሱ ሲሆን ይንንም መነሻ በማድረግ በሃገራችን የሰበር ችሎት ህግ አተረጓጎም ነባራዊ ሁኔታ አስረጅ የሚሆኑ ጉዳዮችን ለማሳየት ጥረት ማድረጉ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በማጠቃለያውም 11 የሚሆኑ መደምደሚያዎችን ማስቀመጡ ጸሐፊው ሊያስተላልፈው የሚፈልገውን መልእክት ያሳዩ ናቸውም ብለዋል፡፡ አጻጻፉ ከጽንሰ ሃሳብ ተነስቶ ወደ ተግባራዊ ማሳያዎች መምጣቱ ቅቡልነት ያለውና ተመራጭ የአጻጻፍ ስልት መሆኑን ከርእሰ ጉዳዩ ጋር ተስማነት ያለው መሆኑ ተነግሯዋል፡፡ በመጽሃፉ ይዘት ላይ ተንታኞቹ/ተቺዎቹ በመጽሃፉ ውስጥ ቢስተካከል ወይም ቢካተት ያሏቸውን ሃሳቦች የገለጹ ሲሆን አቶ ተስፋዬ በሁለቱ ትንተና አቅራቢዎቹ የተሰጡ የትችት አስተያያየቶችን ወስደው በሚቀጥላው ህትመት የማስተካከያ እና ተጨማሪ ሃሳቦች እንደሚያካትቷቸው ገልጸዋል፡፡ አቶ ተስፋዬ አያይዘውም መጽሃፉን የጻፉበት ዓብይ ምክንያት በርእሰ ጉዳዩ ላይ ከእሳቸው የተሻለ ሊጽፉ የሚችሉ ዳኞች፤ የህግ ባለሙያዎችና ምሁራን እንዲጽፉና በዘፍፉ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያሳርፉ ማነቃቃት ነው ብለዋል፡፡ የኢፊዲሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በትንተና እና ትችት መድረኩ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልእክት ይህንን የትችት መድረክ ያዘጋጁት የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያዎች ማህበር እና መሰረት እና ጓዶቿ የህግ ቢሮ ምስጋና ይገባችኋል ብለውል፡፡ እንደዚህ አይነት የህግ መጽሐፍት የሚተነተኑበትና የሚተቹበት መድረኮች በተደጋጋሚ መዘጋጀት የሚገባቸው መሆኑን ጠቁመው የህግ ባለሙያዎች ያካበቱትን እውቀት ለትውልድ እና ለህብረተሰቡ ለማካፈል በመጽሃፍ መልክ እንዲጽፉ እና ለዘርፉ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል፡፡ በመድረኩ የሶስቱም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሃላፊዎችና ተወካይ ዳኞች፣ ጠበቆችና የህግ መምህራን በአጠቃላይ የህግ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት #ለማንኛውም ጥያቄ አስተያየት👇👇 @Ethiolawblogbot @ashufish Share share ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇 ╔═══════════╗ ⚖ 👨‍⚖ @ethiolawblog ⚖ ⚖ 👩‍⚖ @ethiolawblog ⚖ ⚖ 👨‍⚖ @ethiolawblog ⚖ ╚═══════════╝
Show all...
ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ‼️ በወቅታዊው ጉዳይ ክላስ ተቋርጦ እንደነበር ይታወቃል ነገር ግን ትላንት በነገርናችሁ መሠረት የመማር ማስተማሩ ሂደት Day One Class One ዛሬ የሚጀምር መሆኑን እየገለፅን በተለያዩ ምክንያቶች ዝግጁ ያልሆናችሁ እንዲሁም ወደ ግቢው ያልመጣችሁ ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ እንድትገቡና ክላሱን እንድትከታተሉ እናሳስባለን። #ማሳሰቢያ ወደ ክላስ ስትመጡ ማስክና ሳኒታይዘር መያዘዎን አይዘንጉ ክላስ ከገቡ በኃላም ርቀተዎን ጠብቀው ይቀመጡ። https://t.me/joinchat/AAAAAFjmHytEWWbWoq3PAQ @ethiostudente
Show all...
♻️ 𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞 | ሼር ♻️