cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ABAY NEWS

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
141Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#COVID19Ethiopia ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 4,747 የላብራቶሪ ምርመራ 612 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 390 ሰዎች አገግመዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 73,944 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 1,177 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 30,753 ደርሷል። @Abaynews
Show all...
በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኙ 40 ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተማሪዎች መገኘታቸው ተገለፀ! በዚህም የተነሳ አዲሱ የትምህርት ዘመን ሲጀመር በሺህዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ራሳቸውን አግልለው ይቆያሉ ተብሏል። #1 ዩኒቨርስቲ ኦፍ አብሪስቲዊዝ የኮቪድ-19 ስርጭት ለመግታት በሚል የገጽ ለገጽ ትምህርትን አስቀርቷል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ ተማሪዎች ለገና እረፍት ወደ ቤታቸው መሄድ እንደሚችሉ ተናግረዋል። #2 ስኮትላንድ ውስጥ ተማሪዎች ለገና እረፍት ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲሄዱ ማድረግ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ ተገልጿል። ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ከመጀመራቸው በፊት የገጽ ለገጽ ትምህርት እንደሚኖር ተነግሯቸው የነበረ ቢሆንም ፤ አሁን ግን በወረርሽኙ ምክንያት ተቋማት ትምህርት በኢንተርኔት አማካይነት ወደ መስጠት አዘንብለዋል። #3 በማንችስተር ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ለ14 ቀናት በኢንተርኔት አማካኝነት እንደሚማሩ ተገልጿል። 127 ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ተደርጎላቸው ቫይረሱ እንዳለባቸው ሲረጋገጥ 1,700 ተማሪዎች ደግሞ ለ2 ሳምንት ራሳቸውን አግልለው እንዲቀመጡ ተደርጓል። #4 በግላስኮ ዩኒቨርስቲ 172 ተማሪዎች ኮሮና ሲገኝባቸው 600 ተማሪዎች ራሳቸውን አግልለው እንዲቀመጡ ተወስኗል። #5 - በኩዊንስ ዩኒቨርስቲ ቤልፋስት ውስጥ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው በመረጋጋጡ የተወሰኑ ተማሪዎች ራሳቸውን ለይተው እንዲቆዩ ተደርጓል። በርካታ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ቅይጥ በሆነ ስልት እንደሚያስተምሩ ታውቋል። ይህም በኢንተርኔትና በገጽ ለገጽ የሚሰጥ ትምህረትን ጎን ለጎን መስጠትን ያካትታል ተብሏል። ምንጭ ፦ BBC @Abaynews
Show all...
አመሻሹን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ በሆነው የፌስቡክ ገፁ የቦርዱ አመራር አባል የሆኑት ዶክተር ጌታሁን ካሳ በዛሬው እለት በገዛ ፈቃዳቸው ሃላፊነታቸውን መልቀቃቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ ለኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማስገባታቸውን አስታውቋል። @Abaynews
Show all...
ከእስር ቤት ሊያመልጥ የሞከረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ! በአንኮበር ወረዳ አንኮበር ፖሊስ ጣቢያ ሰው መግደል ወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እየተጣራበት የሚገኘው ደስታ አለሙ የተባለው ግለሰብ ከእስር ቤት ግድግዳ ፈርፍሮ ለማምለጥ ሲሞክር ጥበቃ ላይ በነበሩ የፖሊስ ኦፊሰሮች በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ተጠርጣሪው በትላንትናው ዕለት ከምሽቱ 3፡30 ላይ ድርጊቱን መፈፀሙንና በዚህ ላይም የምርመራ ፋይል ተከፍቶ መዝገቡ እየታየ መሆኑን የአንኮበር ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል። Via Ankober Communication @Abaynews
Show all...
#UPDATE በመተከል ዞን በተከሰተው የፀጥታ ችግር ውስጥ እጃቸው ያለባቸው እና በቸልተኝነት ኃላፊነት በአግባቡ ባልተወጡ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች ላይ የክልሉ መንግስት ህጋዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገልጿል። እርምጃ ከተወሰደባቸው 45 አመራሮች ውስጥ አንድ የአመራር ሽግሽግ የተደረገ ሲሆን ሌሎቹ በሙሉ ከኃላፊነት እንዲነሱ ተወስኗል። ከመካከላቸው 10ሩ አመራሮች በህግ እንዲጠየቁ እና ምርመራ እንዲጣራባቸው ተደርጓል። ምንጭ፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብልፅግና ፓርቲ @Abaynews
Show all...
የዩኒቨርሲቲዎች ዝግጅት ምን ይመስለል ? #WolitaSodoUniversity - ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ ከንክኪ ዉጪ የሆነ የእጅ መታጠቢያ ተማሪዎች በብዛት በሚገኙበት አከባቢ ለማኖር ተዘጋጅቷል። የንፅህና መጠበቂያ ሳኒታይዝር ፣ ሳሙና እና ዉኃ ተደራሽ የማድረግ ሥራም ይሰራል። - የካፌ ዝግጅትን በተመለከተ ሁለቱም የተማሪዎች መመግቢያ አዳራሾች ጥገና እና በዘመናዊ ማሽን እየተተካ ነዉ፡፡ - ዶርምን በተመለከተ ካራኒታይን የሆኑ መኝታ ቤቶች የዲስ ኢንፌክት ስራ ከዛሬ ጅምሮ ይካሄዳል፡፡ የዶርምና አከባቢም ፅዳት በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡ - ከኮሮና ጋር በተያያዘ ጥግግትን ከመቀነስ አንፃር በአንድ ዶርም 3 ተማሪ የመመደብ ስራ ለመስራት ዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ - አካዳሚክ ጉዳዮችን በተመለከተ ሁሉም መምህራን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአካዳሚክ ዘርፉም ልዩ ትኩርት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። #AmboUniversity - አምቦ ዩኒቨርሲቲው ካለው 4 ካምፓሶች አሁን ላይ የሀጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ (አዋሮ) በካሯንቲን ማዕከልነት እያገለገለ ይገኛል፡፡ - አምቦ ዩኒቨርሲቲ ዝግጅት ከጀመረ የቆየ ሲሆን ግቢዎችን ዲስኢንፌክት የማድረግ ሥራም ይሰራል ተብሏል፡፡ (ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ቅድመ ዝግጅት በየጊዜው እየጠየቀ እና እየተከታተለ ለተማሪዎች እንዲሁም ለተማሪ ወላጆች ያሳውቃል) @Abaynews
Show all...
መስከረም 18/2013 ዓ/ም አጫጭር የኮቪድ-19 መረጃዎች ፦ - ባለፉት 24 ሰዓት ህንድ ውስጥ ተጨማሪ የ1,040 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 82,767 ሰዎች በቫይረሱ ስለመያዛቸው ተረጋግጧል። - ሜክሲኮ በ24 ሰዓት 399 ሰዎችን አጥታለች። በሀገሪቱ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ አጠቃላይ ሰዎች 76,243 ደርሰዋል። - ግሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ስደተኛ የኮቪድ-19 ሟች ተመዝግቧል፤ ሟቹ 61 ዓመት ወንድ ሲሆን ከማልካሳ የስደተኞች መጠለያ ነው ፤ ህይወቱ ያለፈው በአቴንስ ሆስፒታል እንደሆነ ተገልጿል። - አፍሪካ ውስጥ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች አጠቃላይ ቁጥር 1,467,555 ደርሷል፤ ከነዚህ ውስጥ የ35,215 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 1,213,045 ሰዎች አገግሟል። - የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ዛሬ በኬንያ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው የሚመለሱበትን ቀን ያሳውቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። @Abaynews
Show all...