cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

DW Amharic

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Show more
Advertising posts
41 969Subscribers
+5224 hours
+2537 days
+1 45330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Show all...
ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ አሻቀበ

በአማራና ትግራይ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች በተከሰተ ግጭት ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ያለፈው ሰኞ አስታውቋል። እንደ ድርጅቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፤ በተለይ ሴቶችና ህጻናት የሚገኙበት ሁኔታም አሳሳቢ ነው።

Show all...
«ከብልጽግና ፓርቲ ጋር የውህደት ውይይት አልጀመርኩም» ህወሓት

ከብልፅግና ጋር የሚያገናኘው የጋራ አጀንዳው የፕሪቶርያው ውል መሆኑን የገለጸው ህወሓት ውሉ በሙሉ እንዲተገበር አጋዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብልፅግና ፓርቲና ህወሓት በመቐለና አዲስአበባ መወያየታቸውን አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ህወሓትና ብልፅግና ፓርቲ በመገናኛ ብዙሐን እንደተባለው የጀመሩት ወደ ውህደት የሚመራ ውይይት የለም ሲል አስተባብሏል።

Show all...
የኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት የሰላም ጥሪ፣ ተስፋና ስጋቱ

ኢኒሼቲቭ ፎር ቼንጅ በተባለው ድርጅት ውስጥ የሚሰሩት አቶ ገረሱ ቱፋ የሰሞኑን የኦሮሚያ ሁኔታ በተስፋም በስጋትም እንደሚመለከቱት ያስረዳሉ።የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፖለቲከኛ መረራ ጉዲና አሁን በኦሮሚያም ይሁን በመላ አገሪቱ ግጭቶች የመባባስ እንጂ የመርገብ ምልክት አላሳዩም ብለዋል፡፡

Show all...
"እኛ ለትግራይ ዓለም ነን" ለትግራይ የእርዳታ ማሰባሰቢያ መርሐግብር

በትግራይ ለ2 ዓመት በተካሄደው ጦርነት ለደረሰው ሰብዓዊ ችግር ለመድረስ "እኛ ለትግራይ ዓለም ነን" የተሰኘ ዓለም አቀፍ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ተጀመረ።አስተባባሪው ኘሮፌሰር ሙሉጌታ ገብረእግዚአብሄር ለዶይቸ ቨለ እንደገለጹት፣በትግራይ ከተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት በኃላ የደረሰው ሰብዓዊ ቀውስ ፣አስቸኳይ እርምጃ ያስፈልገዋል።

Show all...
ያሻቀበው የዓለማችን የጦር መሣሪያ ግዥና ክምችት

በዓለም አቀፉ የሰላም ጥናት ተቋም መግለጫ መሠረት በ2023 ዓ.ም. ዩናይትድ ስቴትስ ቻይናና ሩስያ ዋነኛዎቹ የጦር መሣሪያ ሻጭ አገራት ናቸው። የሩስያ ወታደራዊ ወጪ በ24 በመቶ ማለትም በ109 ቢሊዮን ዶላር አድጓል።ዩክሬን ለጦር መሣሪያ ግዥ ያወጣችውና ከውጭ ያገኘችው ወታደራዊ እርዳታ በአጠቃላይ ከሩስያ ወታደራዊ ወጭ 91 በመቶው ያህል ሆኗል።

Show all...
ኢትዮጵያ የቅድመ ታሪክ የቡና መገኛ መሆኗን አዲስ የዘረመል ጥናት አረጋገጠ

አዲሱ ጥናት እንዳረጋገጠው አረቢካ የቡና ዝርያ የተገኘው ከ610,000 እስከ አንድ ሚሊዮን ዓመታት በፊት ባለው ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ደኖች ውስጥ ነው። ይህ የቡና ዝርያ ከዛሬ 300,000 ዓመታት በፊት በአፍሪካ ከነበረው ዘመናዊ የሰው ዝርያ /Homo sapiens/ በዕድሜ ቀደምት ነው።

-አዲስ አበባ ዉስጥ የሁለት ቤተሰብ አባላት በሚኖሩበት ቤት ላይ ዛሬ ማለዳ የተናደ ድንጋይና አፈር 7 ሰዎች ገደለ።የከተማይቱ ባለስልጣናትና የሟች ጎረቤቶች እንዳሉት የድጋይና አፈሩ ናዳ ከፍተኛ በመሆኑ ሰዎችን ማዳን አልተቻለም። -ኬንያን ያጥለቀለቀዉ ጎርፍ የርዕሰ ከተማ ናይሮቢ አዉራ መንገዶችን የደራሽ ወንዝ መዉረጃ አድርጓቸዉ አረፈደ።ጎርፍ ሰሞኑን ኬንያ ዉስጥ 32፣ ታንዛኒ 58 ሰዎች ሲገድል ቡሩንዲ ዉስጥ ከ100 ሺሕ በላይ ሕዝብ አፈናቅሏል። -ዓለም ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ፍፃሜ ወዲሕ የምትመራበት ሕግና ሥርዓት ከጥፋት አፋፍ ላይ መድረሱን አምንስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት እንደሚለዉ በመላዉ ዓለም የሚፈፀመዉ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየከፋ፤ ጥሰቱን ለማስቆም የሚደረገዉ ጥረት እየተዳከመ ነዉ። https://p.dw.com/p/4f9Lk?maca=amh-RED-Telegram-dwcom @dwamharicbot
Show all...
የሚያዚያ 16፣2016 የዓለም ዜና

ባለፈው ሳምንት በሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ቀሲስ በላይ መኮንን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡---አዲስ አበባ ዉስጥ የሁለት ቤተሰብ አባላት በሚኖሩበት ቤት ላይ ዛሬ ማለዳ የተናደ ድንጋይና አፈር 7 ሰዎች ገደለ።---ጎርፍ ሰሞኑን ኬንያ ዉስጥ 32፣ ታንዛኒ 58 ሰዎች ሲገድል ቡሩንዲ ዉስጥ ከ100 ሺሕ በላይ ሕዝብ አፈናቅሏል።-----ዓለም ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ፍፃሜ ወዲሕ የምትመራበት ሕግና ሥርዓት ከጥፋት አፋፍ ላይ መድረሱን አምንስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።

የፕላስቲክ ቆሻሻን ወደ ጥበብ የለወጠው የናይጀሪያ ቤተመዘክር/ሙዚየም/
Show all...
የተወደዳችሁ የዶቹ ቬለ አድማጮች እና ተከታታዮች የሚያዝያ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ስርጭታችን ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በፌስቡክ በቀጥታ ይደመጣል። ለዕለቱ ከተጠናቀሩ ዘገባዎች መካከል፤ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በሚገኙ ከተሞች በተነሳው ግጭት ከተፈናቀሉት መካከል በዋጃ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ወገኖች ስለሚገኙበት ሁኔታ፤ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ከብልፅግና ፓርቲ ጋር ለመዋሀድ ንግግር ጀመረ ስለመባሉ የኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት የሰላም ጥሪ ተስፋው እና ስጋቱ ፣ በአሜሪካን የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች፣ በትግራዩ ጦርነት ለተጎዱ የእርዳታ ማሰባሰቢያ መርኅ ግብር ይገኙበታል። ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ሀገር መሆኗን ስላረጋገጠው አዲስ የዘረመል ጥናትም የሚያስቃኝ ጥንቅር አለን። የዓለም ዜናን ጨምሮ ሁሉንም በሰዓቱ ተገንታችሁ እንድትከታተሉን ከወዲሁ የአክብሮት ግብዣችን ይድረሳችሁ። የዶቼ ቬለን የየዕለቱን የዜና እና የዜና መጽሔት ጥንቅሮች ከዩቲዩብ ቻናላችን ማግኘት እንደምትችሉ እናስታውሳችሁ። ትክክለኛው የዶይቼ ቬለ የዩቲዩብ ቻናል ከታች ያለው ሲሆን እስከዛሬ ሰብስክራብ ያላደረጋችሁ በማድረግ በዩቲዩብም ቤተሰብ እንሁን። ለሌሎችም ማጋራት አትርሱ። እናመሰግናለን። https://www.youtube.com/@dwamharic/videos
Show all...
... ለልማት በሚለው እቅድም ከአራት ኪሎ ጥይት ቤት ጀምሮ እስከ ፒያሳ ድረስ ነዋሪዎቹ እንደሚነሱ ተነግሯቸዋል ነው ያሉት። በተለይ በቀበሌ ቤት ነዋሪዎች ቤቶች እየተሰጣቸው ቤቶቹ እየፈረሱ እንደሆነም አመልክተዋል። የእሳቸውን ጨምሮም ከራስ አምባ ሆቴል ፊት ለፊት በታችኛው በኩል ያሉ አካባቢዎች የግል ቤቶች ግምትና ልዋጭ መሬት ለማዘጋጀት በሚል እስካሁን እንዳልፈረሱም ተናግረዋል። በዚህ መሀልም ላልተወሰነ ጊዜ በሚል ፈረሳው መቆሙን፤ ከመንግሥት አካላት ጋር በተደረገው ውይይትም ተማሪዎች የዚህን ወቅት ትምህርታቸውን እስኪያጠናቅቁ በሚል ለጊዜው ማፍረሱ እንደቆመ እንደተነገረም ነው ለዶቼ ቬለ የገለጹት። ሆኖም ግን ነዋሪዎች ከዛሬ ነገ ሊነሱ እንደሚችሉ በመስጋት ዕቃቸውን ሸክፈው በመጠባበቅ ላይ እንዳሉም አመልክተዋል። በተመሳሳይ በሰሜን ማዘጋጃና በሰሜን ሆቴን አካባቢ ነዋሪዎች እንደሚነሱ እንደተነገራቸው ለመረጃው ቅርብ እንደሆኑ የገለጹ የአካባቢው ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል። እንደ መረጃ ምንጩ፤ ከፋሲል ትምህርት ቤት ጀርባ፣ በሰሜን ማዘጋጃ አካባቢ እስከ ቀለበት መንገድ ድረስ ነዋሪዎች አካባቢው ፈራሽ መሆኑ እንደተነገራቸውም መረጃ እንዳላቸው ገልጸዋል። የቀድሞ ሰፈሮች መፈራረስ የነዋሪዎቹን ማኅበራዊ ግንኙነትና መስተጋብር ክፉኛ እንደጎዳው የሚናገሩ እንዳሉ ሁሉ ልማቱ ውሎ አድሮ ለሁሉም የሚጠቅም ሊሆን እንደሚችል የሚሞግቱ አሉ። እርስዎስ ምን ይላሉ?
Show all...