cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Adiss merja

Adiss merja ለ እኛ for Comments Use @Besheta_bot 🙏 share ⓨⓣⓐ official 🌼ሼር ማድረግ አይረሳ 🙏

Show more
Advertising posts
1 628Subscribers
No data24 hours
+47 days
+4930 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

" ችግር አላየሁበትም " - ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሚኒስቴር ከአካውንቲንግ እና ፋይናንስ የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ ሲነሳ ለነበረው ቅሬታ " ገምግሜዋለሁ ምንም ችግር አላገኘሁበትም " ሲል ምላሽ ሰጠ። የአካውንቲንግ እና የፋይናንስ የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ተፈታኞች እንዲሁም የትምህርት ክፍላቸው እንዲሁም ኮሌጆች ፈተናው ዳግም እንዲገመገም ጥያቄ ሲያቀርቡ እንደነበር አይዘነጋም። የቀረበው ቅሬታ ፈተናው ከተዘጋጀው ብሉፕሪንት ጋር ተያያዥነት እንደሌለው፣ ይሸፍናል ከተባለው 15 ኮርስ የሸፈነው ከ4 የሚበልጥ እንዳልሆነ ፣ የመጡት ጥያቄዎችም በዲግሪ ደረጀ ለመረዳት የማይቻሉ ፣ ለፈተናው የተሰጠው ሰዓትም ከጥያቄው ጋር የማይገናኛ መሆኑ ይጠቀሳሉ። ለዚህም ትምህርት ሚኒስቴር አስፈላጊውን ማስተካከያ እንዲያደርግ እና ፈተናውን እንዲገመግመው ተማሪውን የሚመጥን ፈተና ድጋሚ አዘጋጅቶ በፍጥነት እንዲፈትን ተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቧል። የትምህርት ሚኒስቴር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጠው ቃል ፤ ስለተነሳው ቅሬታ እንደሚያውቅ ገልጾ ፈተናውን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መገምገሙን ነገር ግን በፈተናው ይዘት ላይም ሆነ አቀራረብ ላይ ችግር እንዳላየበት አሳውቋል። #ማስታወሻ፦ ከፈተናው ጋር በተያያዘ በተማሪዎች እንዲሁም በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ ትምህርት ክፍሎች / ኮሌጆች የቀረቡ ቅሬታዎች ፦ https://t.me/tikvahethiopia/79870?single https://t.me/TikvahUniversity/7740?single https://t.me/TikvahUniversity/7739?single @tikvahethiopia
Show all...
" የእኔ ልጆች እንደ ጧፍ በርተው ለሌሎች ብርሃን መሆን ከቻሉ ተመልሼ የማዝንበት ምንም ምክንያት የለኝም " - አባት ጌታሁን በላቻ በኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ዙሪያ በምትገኘው ሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ ውስጥ ከአራት ወራት በፊት ሁለት ህጻናትን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለችው የእንጀራ እናት ነጋሴ ከበደ የሞት ፍርድ ተፈረደባት። ጥፋተኛ ሆና በተገኘችው ግለሰብ ላይ ውሳኔውን ያስተላለፈው የሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ሐምሌ 19/ 2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ነው። የቡራዩ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ባልደረባ የሆኑት እና ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩት ዋና ሳጅን ቀነኒሳ ታደሰ ፤ "  እርሷን እና መሰሎቿን የሚያስተምር የሞት ቅጣት ውሳኔ ፍርድ ቤቱ በይኖባታል።  " ብለዋል። የሟች ልጆች አባት አቶ ጌታሁን ባልቻ ምን አሉ ? " አፈጻጸሙን ለሕግ አካላት እንተወዋለን። ለእኔ እንኳን ባይሆን ለሌሎች ህጻናት እና ለቀሪው ቤተሰብ፣ ይህ የተሰጠው ፍትህ ብርሃን ነው። ብይኑ ለሌሎች ጥሩ ማስተማሪያ ይሆናል። የተላለፈው የፍርድ ውሳኔ ያላጠበቁት ነበር። ከበፊት ጀምሮ የነበረው የሕግ መላላት እንዳለ ሆኖ በዚህች ሦስት ወራት ውስጥ የፍትህ ሁኔታው መድረሱ ለእኔ ደስ ብሎኛል። ሌሎች ህጻናት እንቅልፍ የሚያገኙበት፣ አሁን ትንሽ እፎይ የሚሉበት ሁኔታ ይፈጠራል ብዬ አስባለሁ። የእኔ ልጆች እንደ ጧፍ በርተው ለሌሎች ብርሃን መሆን ከቻሉ ተመልሼ የማዝንበት ምንም ምክንያት የለኝም። የውሳኔው ፍጥነት ደስ የሚል ነው። የሚመለከታቸው አካላትም ርብርብ አድርገውበታል። አፈጻጸሙ ግን ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጠው ጠይቃለሁ። " የሞት ፍርድ መፈረዱ ብቻ ሳይሆን አፈጻጸሙ ያላለቀ ከዚህ በፊት ውሳኔዎችንም እየጠቀሱ ጥርጣሬያቸውን ስለሚያነሱ ግለሰቦች አሉ። የፍርድ ቤቱን ውሳኔ እና ሕጉን ለሕዝቡ ተዓማኒ እንዲያደርገው አፈጻጸሙ መሆኑንም አጽንኦት በመስጠት ያስረዳሉ። ከዚህ ቀደም በሁለት ህጻናት ግድያ አንዲት ግለሰብ የሞት ፍርድ የተፈረደባት ቢሆንም በኢትዮጵያ ውስጥ የሞት ቅጣት ተፈጻሚ ከማይደረግባቸው አገሮች አንዷ ናት። ማስታወሻ ፦ ነጋሴ ከበደ ብሩ የተባለችው እንጀራ እናት የሁለት ህጻናትን አንገት ቀልታ በተኙበት ብርድ ልብስ በማልበስ ቤቱ ላይ እሳት ለኩሳባቸው አምልጣለች የተባለው ሚያዝያ 27/2015 ዓ.ም. ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ነበር። በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ልጆች አንደኛው የ13 ዓመት ወንድ ሲሆን፣ ሌላኛዋ ደግሞ የ4 ዓመት ተኩል ሴት ናቸው። ሁለቱም አንገታቸው ተቀልቶ መገደላቸውን ፖሊስ በወቅቱ አሳውቆ ነበር። Via BBC AMAHARIC @tikvahethiopia
Show all...
217 ፍሬ አልባሳትን በ40 ሚሊየን 67 ሺህ 748 ብር የገዙት አመራር እና ሰራተኞች ላይ የሙስና ተከስ ተመሰረተ። በሀገራችን ብዙ የሙስና ወንጀል ክስ ሰምተናል።  በሰማናቸው በብዙዎቹ የሙስና ክሶች አፋችንን ይዘን ተገርመናል፤ ደንግጠናል። ዛሬም በርካቶችን ያስገረመ አንድ የሙስና ወንጀል ክስ ተሰምቷል። ነገሩ እንዲህ ነው . . . የሙስና ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች፦ 1ኛ. የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር ሰለሞን ፍስሃ፣ 2ኛ. የተቋሙ የመንግስት የግዢ ዳይሬክተር ግሩም ወልዴ፣ 3ኛ. የኮሚሽኑ የለውጥ ስራ አመራር ዳይሬክቶሬት ባለሙያ ደረጄ ተፈራ፣  4ኛ. የኮሚሽኑ የሎጀስቲክስ ምዝገባና ቁጥጥር ባለሙያ ወንድሜነህ ምስጋናው፣ 5ኛ. የአደጋ ስጋት ትግበራ ቡድን መሪ እዮብ ታደሰ ካሳ ፣ 6ኛ. በኮሚሽኑ የህክምና ባለሙያዋ ሲስተር  አልማዝ ጌቶ፣ 7ኛ. የአደጋ መረጃ ሀርድ ዌርና ሶፍትዌር ባለሙያ መስፍን ለገሰ  8ኛ. ነጋዴ የሆኑት ንጉስ አማን ይባላሉ። የቀረበባቸው የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ከሆነ ፤ በሰኔ ወር  በ2014 ዓ.ም በጀት አመት ከአንደኛ እስከ ሰባተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች የግዢ ጨረታ ሂደት ውስጥ ይሳተፋሉ። ግለሰቦቹ በሂደቱ በስውር በመመሳጠር በወቅቱ በተደረገ የገበያ ዳሰሳ ጥናት የአልባሳቱ ዋጋ 46 ሺህ 923 መሆኑ የተረጋገጠ ተከሳሹቹ ግን " ብልዶዘር " የተሰኘ የእሳት አደጋ መከላከያ ልብስን  ከፍተኛ በሆነ ዋጋ በፍሬ 184 ሺህ 644 ብር ከ8ኛ ተከሳሽ ተጫራች ድርጅት ግዢ እንዲፈጸም ያፀድቃሉ። አጠቃላይ 217 ፍሬ አልባሳትን በ40 ሚሊየን 67 ሺህ 748 ብር በመግዛት በመንግስት ላይ በልዩነት 29 ሚሊየን 885 ሺህ 441 ብር ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል። የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ህግም በተከሳሾቹ ላይ የተሳትፎ ደረጃ ጠቅሶ የከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል። ክስ የተመሰረተባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። ከተከሳሾቹ መካከል 1ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች ያልቀረቡ ሲሆን ቀሪ ስድስት ተከሳሾች ግን ክሱ እንዲደርሳቸው ተደርጓል። መረጃው ከጋዜጠኛ ታሪክ_አዲኛ / ኤፍቢሲ የተገኘ ነው። @tikvahethiopia
Show all...
ተፈታኞች ከነገ ጀምሮ ይገባሉ። የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከነገ ሐምሌ 16 ጀምሮ ወደ ተመደቡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ይገባሉ። ተፈታኝ ተማሪዎች ከሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች ወደ ተመደቡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች የሚጓዙት በተዘጋጅላቸው ተሽከርካሪዎች ነው። ተፈታኞች ዩኒፎርማቸውን መልበስ ፤ ብርድልብስና አንሶላ ይዘው መገኝት ይጠበቅባቸዋል።  ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ የመሳሰሉ ደረቅ ምግቦችን ይዞ መግባት የሚፈቀድ ሲሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ ሞባይል፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ የመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ነው። ተማሪዎቹ ከቤታቸው ሲወጡ፦ - መታወቂያ ፣ - አድሚሽን ካርድ - የት/ቤት ዩኒፎርም መያዛቸውን እንዳይረሱ ፤ ወላጆችም ይህንን እንዲያስታውሷቸው ጥሪ ቀርቧል። ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በከፍተኛ የመንግሥት የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ይሰጣል። ፎቶ ፦ ፋይል @tikvahethiopia
Show all...
" ይሄ ለእኔ የሚገባኝ አይደለም። ግን ስላከበራችሁኝ እግዚአብሔር ይስጥልኝ " - እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) እጅግ ተወዳጇ አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተበረከተላትን የክብር ዶክትሬት በተመለከተ መልዕክት አስተላልፋለች። ምን አለች ? እጅጋየሁ ሽባባው ፦ " እምዬ ሀገሬ ፤ ውድ ሀገሬ ኢትዮጵያ እንዲሁም በጣም የምወዳችሁ የማከብራችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሰላም ሰላም ሰላም ብያለሁ። በአክብሮት የሰጣችሁኝን የአክብሮት ዶክትሬት በጣም በትልቅ ደስታ ነው የተቀበልኩት ፤ በጣም አመሰግናለሁ፤ እግዚአብሔር ይስጥልኝ። እኔ በጣም በጣም ነው የገረመኝ ታጭቼ ብገኝ እንኳን የሚያስደንቀኝ ነበር ተመርጬ ስለተነገረኝ በጣም ነው የማመሰግነው፤ እግዚአብሔር ያክብርልኝ። ፍቅራችሁ እንዲሁ አክብሮታችሁ ስለሆነ በእኔና በወገኖቼ ስም እንዲሁም በዚህ ሁሉ ደስ በሚላቸው ኢትዮጵያውያን ስም ከልቤ በጣም በጣም አመሰግናለሁ። እግዚአብሔር ህይወታችሁን ይባርከው ፣ የኢትዮጵያ ዛሬ ያሉትን #ተማሪዎች እንዲሁም የወደፊቱን ሁሉ እግዚአብሔር ይባርክ፣ ሀገራችንን መንፈስቅዱስ ይጠብቅልን። ያስቸግራል ለመግለፅ ደስታዬን ፤ በጣም አመሰግናለሁ፣ ፍቅራችሁና ክብራችሁ ከልክ ያለፈ ነው ፤ ለእኔ የሚገባኝ አይደለም። ግን ይሄን ሁሉ ስላከበራችሁኝ እግዚአብሔር ይስጥልኝ። የኢትዮጵያን ህዝብ እግዚአብሔር ይጠብቅልን ፤ ምስጋናዬ በጣም ከፍ ያለ ነው፤ በአካል ተገኝቼ አንድ ቀን እዛ መጥቼ አያችኃለሁ ፤ በሰላም ቆዩኝ ይሄንን አጭር መልዕክቴን ይቅር በሉኝ ፤ በደንብ አድርጌ ሌላ ቀን አመሰግናችኃለሁ ፤ እግዚአብሔር ይስጥልኝ። እጅጋየሁ ነኝ " @tikvahethiopia
Show all...
ምርጥ አጓጊ ተከታታይ ክፍል 1-10 በHD ትርጉም በተለይ From የሚለውን ተከታታይ አይተኸው ከሆነ ይሄ እንዳያመልጥክ https://t.me/ye1adey2family https://t.me/ye1adey2family https://t.me/ye1adey2family https://t.me/ye1adey2family
Show all...
በኢትዮጵያ🇪🇹 ለምዝገባ ሙሉ ውክልና የተሰጠው ብቸኛ ድርጀት👇👇 lol lord Lucifer's ☎️🆔 +251976826357💴📱💵 📱0976826357 ማየት ማመን ነው ይህው ባሉበት ቦታ ሁነው የአባልነት ጥያቂ የጠየቁ ሰወች ገንዘባቸውና አይዲያቸው ተቀብለዋል ብልህወች እየተቀላቀሉ ህወታቸወን እየቀየሩነው አተስ/ች ለመን ከሰወበታች የሰው አገልጋይ ሆነው እሰከመቸ ይጨቆናሉ ይሰቃያሉ አስኪ አንድ ግዚ ቆም ብለህ አስብ እስከመቸነው የምተሰቃይ አቆራጭ መንገድ እያለ ለምን ሞኝ ትሆናለህ አሁን ንቃ የአተን የቤተሰቦችህን ሂወት ቀይሩ :: ወስን ‼ወስን‼ ወስን ወስን‼ በቅድሚያ ለበግባት 100%ወስንክ/ሽ ከወሰኑ ባላችሁበት ሆናችሁ አባል መሆን ትችላለህ። 100% ሚስጥር የተጠበቀ ነው በቅድሚያ 1,መታወቂያ 2, ፎቶ 3, የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 4, አድራሻ 5, እና ለድርጅታችን #3600ብር. ክፍያ ከፍለው ይቀላቀሉን ተቀላቅላችሁ እንደጨረሳቹህ የሚሰጡ ጥቅሞች* 1➡ 500,000 የመጀመሪያ ክፍያ ይከፈልዎታል ETB በየ ስድስት ወሩ 2 ➡ 1,000,000ወርሀዊ ክፍያ ETB 3➡ ተአዋቂ ዝነኛ ዝፍኝ: አልያም አርሱወ የሚፈሉገት የዝና መንደር ይቀላቀላሉ 4 ➡►ማጂክ ሪንግ ቀለበት 5➡ ►የእጅ የወርቅ ሰአት 6➡ ►በመረጠበት ቀን የ 6 ቀን የፓሪስና ግሪክ ጉብኝት 🔴►ወደ ቸርቻቺን አባል ያልሆነ ሰው መምጣት አይቻልም። በዚህ መሥፈርት ተስማመቶ የሚላክለትን ፎርም እንደሞላ የምዝገባ ▬code ይሰጠዋል:: ያንን ቲን ነበር ለመሥዋት አቅራቢዉ በመላክ ክፍያዉን ይከፍላል። ክፍያዉን እንደከፈለም ፎርም በሞላበት የቴሌግራም አካዉንት 1➡ የባንክ ቡኩን በፎቶ 2➡ የሂሳብ ቁጥሩን 3➡ ያለበትን ቅርንጫፍ ያስመዘግባል። ያንን እንደጨረሰም በ (48ሰ (2) ቀን ጊዜ ዉስጥ የተመደበለትን የገንዘብ መጠን በ አካዉንቱ ገቢ ይደረጋል። ሌሎች የተቀመጡ ጥቅሞችን በቀጠሮ የሚረከብ ይሆናል። ◆ጥብቅ ማሳሰብያ◆ ▬በየ ሳምንቱ የሚከፈለዉ ገንዘብ የሚጨምረዉ አባሎቺን ወደ ወንድማማቺነቱ ሲቀላቅል ብቻ ይሆናል። # ገቢ የሆነለትን ገንዘብ ከ ባንክ ማውጣትና መጠቀም ይችላል። ከላይ በተጠቀሱት መስፈርቶች የማይስማማ ከሆነ የምዝገባ ፎርሙ አይላክለትም። የሚስማማ ከሆነ ደግሞ የምዝገባ ፎርም በመሙላት ቲን ነበር እስከሚሰጠዉ ይጠብቃል። የታላቁ ሉሲፈር አባል ለመሆን ስለመረጡን እናመሰግናለን። 🏫 አድራሻ ደብረ ዘይት (ቢሾፍቱ) ፍላጎት ያላችሁ ደውሉልን ☎+251976826357 251976826357 #ማሳሰቢያ_ብዙ_አጭበርባሪ_ግለሰቦች_እንዳሉ_ጥቆማዎች_ደርሰውናል_ስለዚ_አማኞች_እባካችሁ_ከአጭበርባሪ_ግለሰቦች_ራሳችሁን_ጠብቁ እንላለን።
Show all...
#ምርቃት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከነገ ረቡዕ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን ያስመርቃሉ። ተቋማት ለዓመታት ያስተማሯቸውን ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸው ፣ የክብር እንግዶች በተገኙበት ነው የሚያስመርቋቸው። ዘንድሮ ከተሰጠው የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ በምርቃት መርሃግብር ላይ ከመሳተፍ ጋር በተገናኘ በተመራቂዎች ዘንድ ጥያቄዎች የነበሩ ቢሆንም ትምህርት ሚኒስቴር ይህ ጉዳይ የተቋማቱ #የሴኔት ውሳኔ ጉዳይ መሆኑን ገልጾ ነበር። በዚህም መሰረት በተቋማት ሴኔት ውሳኔ ለምርቃት ብቁ የሆኑ / የምረቃ ፎርማሊቲ የሚያሟሉ ተማሪዎች የምርቃት ስነሥርዓት ላይ ይሳተፋሉ ፤ ነገር ግን ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃቸውን የሚወስዱት የመውጫ ፈተና ያለፉት ብቻ ናቸው። የተቋማት የምረቃ ቀን መቼ ነው ? ነገ ረቡዕ ተማሪዎቻቸውን ከሚያስመርቁ ተቋማት መካከል ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ይገኝበታል። የፊታችን ሐሙስ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ፦ - ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ ካምፓስ) ፤ ጊምቡ እና ሻምቡ በነጋታው። - ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ) ፤ በ15/2015 (ቡሬ ካምፓስ) - ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ - አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ) ፤ በነጋታው በሳውላ ካምፓስ - ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ - ጂንካ ዩኒቨርሲቲ - ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ - ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ - ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰመራ ዩኒቨርሲቲ - ዲላ ዩኒቨርሲቲ - እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ - ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)  በነጋታው (ዱራሜ ካምፓስ) - መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ - ቀብሪ ድሃር ዩኒቨርሲቲ - ወራቤ ዩኒቨርሲቲ - መቱ ዩኒቨርሲቲ - አምቦ ዩኒቨርሲቲ - ወልድያ ዩኒቨርሲቲ - ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ - አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቻቸውን ያስመርቃሉ። ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ካስመረቁ በኃላ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ከሐምሌ 16 ጀምሮ ይቀበላሉ ተብሎ ይጠበቃል። #tikvahethiopia @tikvahethiopia
Show all...
S
Show all...