cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ወንጌል ይለዉጣል📖

ወንጌል ይለዉጣል ትምህርቶች የእግዚአብሔር ቃል የዝማሬ ግብዣ እና ሌሎችም እራሳችንን እንድናይ የሚያደርጉ ፅሁፎች የሚቀርቡበት gospel channel contact us @kalu_hayal_new @enchanted_nuha

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
201Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ፊል18 ላይ #አለቅሳለሁ ይለናል ይህን ጨካኝ ሰው ያስለቀሰው ነገር ለመስቀሉ ጠላት የሆነው ምልልሳቸው ነው ይህም ምልልስ ለሰው ፅድቅን ሚያመጣ ሳይሆን #ሞት የሆነ መጨረሻ ስላለው ነው።19 አንድ አባባል አለ "ለመኖር ስትል ብላ እንጂ ለመብላት ስትል አትኑር" ሚል ሆዳችን ጌታ ከሆነ ለሱ እንገዛለን በጣም ሚከብደው ቃል እዚህ ክፍል ላይ "ክብራቸው በነውራቸው ነው" ሚለው ነው ዛሬ ላይ እንደ ክብር የያዝነው ነገር ምንድነው እግዚአብሔር ነውር ያለው እኛ ግን ክብራችንን አውልቀን ክብር ያረግነው ነገር ምንድነው መፀሐፍ ሮሜ 8:33 ላይ"የሚያፀድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኮንንስ ማነው?"ይላል ስለዚህ እግዚአብሔር የኮነነውን ነገር ክብራችን ሊሆን ይገባልን እንደ እነዚህ ያሉትን ሰዎች "አሳባቸው ምድራዊ ነው" ይላቸዋል ከምድር ያላለፈ ሰው ደግሞ የሰማዩን ክብር አያይም እግዚአብሔር ያለው ይሁን ለማለት ለእርሱ ፈቃድ የተገዛን ሰዎች መሆን ይገባናል እግዚአብሔርን ለሚወዱ እንዳሳቡም ለተጠሩ ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ ይላል ፍቅራችን ሚታየው በአክብሮታችን ነው የዛኔ ታማኝ ከሆነው ጌታ የእምነታችንን ፍሬ እንቀበላለን ስለዚህ ለክርስቶስ ሕይወት እንጨክን!
Show all...
ገላ 5 ላይ "ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በስጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፣ ስለዚህም #የምትወዱትን.ልታደርጉ.አትችሉም።" ይላል መንፈስ እንዲበረታ ብረት አናነሳም 2ቆሮ 3"መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን" ይላል የክርስቶስን መልክ ለመምሰል መንፈስ በሆነው ጌታ መንፈሳችንን ልናበረታ ይገባል የዛኔ የምንወደውን የጌታን ሀሳብ እናደርጋለን የእግዚአብሔር ሀሳብ ደግሞ ፍፁምን ደስ የሚያሰኝ ነው ምክንያቱም ነገርን በጊዜው ውብ አርጎ ስለሚሰራ…
Show all...
በዘመንክ አንድ ነገር ፈፅሞ አጥብቀህ ያዝ እሱም ክርስቶስን። እሱ የሌለበት ስኬት ተድላ ፌሽታ ሁሉ ከንቱ ነው። ጳውሎስ በፊልጲ 3፥9 ላይ [[በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጉድፍ እቆጥራለው፤]] ይላል ለምን ስንለው 10-11 [[ .እርሱንና .የትንሳኤውን.ኃይል እንዳውቅ #በመከራውም.እንድካፈል ፥ ወደ #ሙታንም.ትንሳኤ.ልደርስ ቢሆንልኝ #በሞቱ .እንድመስለዉ እመኛለሁ።]] ስለ እኛ ደግሞ አንድ ፍርሃቱን እያለቀሰ ይመክረናል 18[[ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና]] 19[[መጨረሻው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።]] ይለናል ጳውሎስ ብዙ የሚመካበት ነበረው ብዙ ለኑሮዉ ለስጋው ሚመች ነገር ነበረው ስለ ድህነቱ ሲል ግን ሁሉን እንደ ረብ እንደ ከንቱ እንደ ቆሻሻ ቆጠረው ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶች ሆነው ይመላለሳሉ ይለናል ምክንያቱም መሰቀል አልፈለጉም በሞቱ አልመሰሉትም ስጋቸውን አልሰቀሉም ስለዛም ነው ከትንሳኤዉ ማይካፈሉት የሰው ሆዱ አምላኩ ሊሆን አይገባም ምክንያቱም ስጋ አይጠግብም ሁሌም አምጣ ሁሌም ለኔ ነው ሚለው …
Show all...
እንግዲህ ጳውሎስ በዚህ መፀሐፍ <<ፍለጋ የሌለውን የክርስቶስን ባለ ጠግነት>> ውረሱ እያለን ነው ኤፌ3፥8 ኤፌሶን 1፥3 [[[3 በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።]]] ስለዚህ ባለጠግነት ከማውራታችን በፊት ስለ በረከቱ ምንነት ማወቅ ያስፈልጋል 👇 ይህ ባለጠግነት እንደዘመኑ የብልፅግና ሰባኪያን ምድር ምድሩን የሚያስናፍቅ ገንዘብ ገንዘብ ሚሸት አይደለም ክብር ዝና ሀብት አያስናፍቅም አንዳንድ ሰዎች መንፈሳዊነት የሚመስል ምኞት አላቸው አትመኝ የሚለውን ቀይረውት <<ሀይልን በሚሰጠኝ>> በሚመስል ጥቅሳዊ ምኞት ውስጥ ተጠምደዋል ይሄ ኃጢአት ነው ምክንያቱም ጥረን ግረን እንድንበላ እና እንድናገኝ ታዘናል <<ሊሰራ የማይወድ አይብላ>> ነው ቃሉ 2 ተሰ 3፥8-10 እዚህ ጋር ዋናው መርሳት የሌለብን ነገር እግዚአብሔር የእጃችንን የጉልበታችንን ፍሬ እንደሚባርክ ነው የሰማዮ አባታችን በረከት አያልቅበትም ምክንያቱም እርሱ ባለጠጋ ነው እየሰጠ ይሞላለታል ስለዚህ በምድርም መቶ እጥር እናፈራለን ማለት ነው በበረከቱ ይባርከናል ነገር ግን ጳውሎስ በዚህ መልእክት ሊነግረን የፈለገው ስለዚህ በረከት ሳይሆን ስለ <<መንፈሳዊ በረከት>> ነው። በዚህ ውስጥ 1 በማን 2 የት 3 በምን ያህል 4 ማን የሚሉትን ሃሳብ እናያለን 5ምስጋና ((1)) በማን <<በክርስቶስ>> በማለቱ ይህ በረከት በክርስቶስ በኩል የሚገኝ መሆኑን ያስረዳል ፡ አማኝ በክርስቶስ ያመነ እለት የእግዚአብሔር መንግስት መራሽ ሆኗል በክርስቶስ ያመንን እለት አብ በልጁ አበልፅጎናል ((2)) የት <<በሰማያዊ ስፍራ>> ክርስቲያን ዜግነቱም ሀገሩም ተስፋውም አባቱም ልቡም በሰማይ ነው ለዛም ነው ሀብትን በሰማይ እንድናከማች መ.ቅ ሚነግረን ስለዚህ አምላካችንም በሰማያዊ በረከት በክርስቶስ አበልፅጎናል ((3)) <<በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ>> ሁሉ የሚለው ቃል የሚቀር ነገር እንደሌለ ያሳያል ይህ በረከት መንፈሳዊ ዓለም ውስጥ ያሉትን በረከቶች ሁሉ ይዟል እዚህ ላይ ገላ 5:22 ላይ ያሉትን የመንፈስ ፍሬዎች እና የፀጋ ስጦታዎች ማንሳት ተገቢ ነው ይነበብ👇 ዕብ 2፥4 ሮሜ 12፥6-8 1ጴጥ 4፥10-11 1ተሰ 5፥19-22 1ቆሮ 12፥4-11 : 28-31 ፤ 13፥1-3 ፤ 14፥16-40። ከምንም በላይ እግዚአብሔር በክርስቶስ ድነትን ሰቶናል በመዳናችን ደግሞ የመንፈስ ቅዱስን ማደሪያዎች ሆነናል በመሰረቱ ክርስቲያን የሁለት ዓለም ሰው ነው በምድር እያለ በሰማይም የሚኖር ነው <<ከክርስቶስ ጋር አስቀመጠን>> ስለሚል 🤔እስኪ ሰማይ ላይ ያለውን አለም 1min ጨፍነን እናስበው የበጉ ዙፋን፡ አምልኮት፡ አክሊል፡ መላዕክት፡ ቅዱሳን፡ በጉ ብርሃን የሆነበት ክርስቶስን ምናይበት የመንግስተ ሰማይ ዉበትና አኗኗር … እናስበው እስኪ ያልወረስነው ምናለ… ((4)) ማን የሚለውን ስናይ የበረከታችን ምንጭ ምን እንደሆነ ይነግረናል <<የጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት>> ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰው እና ፍፁም አምላክ ነው በዚህም በፍፁም ሰውነቱ እግዚአብሔር አምላኩ ነው ፡ በፍፁም አምላክነቱ ደግሞ እግዚአብሔር አባቱ ነው ። ስለዚህ የበረከታችን ምንጭ አባታችን ነው ልጅነትንም ያገኘነው በክርስቶስ ነው፡ አንድ አባት ለልጁ ማያወርሰው ነገር የለም ከሚጎዳው ነገር ውጪ ሁሉ ለልጁ ነው እንግዲህ አባታችን ያለውን እንይ ((5)) ምስጋና ሐዋርያው ይባረክ እያለ እግዚአብሔርን ሲያመሰግን እናያለን የማመስገናችንም ምክንያት <<በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ>> ስለመባረካችን ነው። አንድ ጠቅላይ ሚኒስተር ወንበሩ ላይ ተቀምጦ አይኖርም ስራውን ሁሉ ይሰራል ነገር ግን እሱ ከወንበሩ ላይ ስለተነሳ ስልጣኑን አያጣም የትም አገር ቢሄድ ያ ወንበር የሱ እንደሆነ እርግጥ ነው እኛም በምድር ላይ በተለያየ ሁኔታ ልንኖር እንችላለን አንድ ግን እርግጠኛ ምንሆንበት ነገር ከልጅነት ስልጣናችን ማንም እንደማይነቀንቀን ነው ምድር ላይ እያለን ሰማይ ላይ ስላለው ሕይወታችንና ቦታችን እርግጠኞች ነን ምክንያቱም ከአባታችን የበረከት ባለጠግነት ሁሉ ተካፋዩች ስለሆንን ስለዚህ ስለ መንፈሳዊ በረከቶች ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ሁሉ አመስጋኞች መሆን አለብን አመስጋኝ ብቻ ሳይሆን እንደ ደሀ ሳይሆን እንደ ባለጠጋም አኖር አለብን እርሱን በይቀን ማንቀበለው አለቀብኝ ምንባለው ነገር የለም ምንድነው የነፍሳችን መሻት መዘመር ነው እሱን እንጠይቅ መስበክ ነው መፀለይ ነው ትንቢት ነው አጋንንት ማስወጣት ነው… በምድርስ ምንድነው ሰርተን ያልሆነልን የሁሉም ጥያቄ መልስ አንድ ነው አምላክና አባት የሆነውን እግዚአብሔርን በክርስቶስ መጠየቅ የዛኔ ከባለጠግነቱ ያጠግበናል 🙏God bless You 🙌 እንግዲህ እንደ ባለጠጋ እንኑር
Show all...
ኤፌሶን ምዕራፍ 1 [[1 በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ፥ በኤፌሶን ላሉት ቅዱሳን በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምእመናን፤]] be ቁ 1lay ሐዋርያው በማን ፈቃድ የማን ሐዋርያ እንደሆነ ይናገራል ጳውሎስ እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት ሹመቱን ከሌሎች እጅ አልተቀበለም ወንጌልንም ከሰዎች አልተሰበከም ሐዋ9 lay ክርስቶስ ተገልጦለት ነው ወደዚህ ጥሪ የገባው ይህም አስቦበት ሳይሆን የእግዚአብሔር እቅድና ፈቃድ ነበር ምክንያቱም እሱ የአሕዛብ ሐዋርያና ፀረ ክርስቲያን ወሪ የነበረ ሰው ነበር ነገር ግን የእ/ር ፈቃድ የክርስቶስ ሐዋርያነት ስለነበር ተቀይሯል ምንም ያህል አሳዳጅ ቢሆንም ከእ/ር እቅድ ማምለጥ አይቻልም ፥ <<የኢየሱስ ክርስቶስ>> በማለቱም የክርስቶስ ሰራተኛ መሆኑን ያሳያል ሌላው የሚፅፍላቸውን ሰዎች <<ቅዱሳን>> ይላቸዋል እኚ ሰዎች የመጀመሪያ ታሪካቸው ሲታይ አሕዛብ የነበሩና ጣኦት የሚያመልኩ ሰዎች ነበሩ በዛም ብዙ የዝሙት ስራ ይደረግ ነበር በከባድ ተፅእኖ ውስጥ የነበሩና ከዛም በስተጀርባ ክፉ ኃይላት እንደነበሩ መፀሐፍ ይናገራል (1፥19-20 ፤ 2፥1-2 ፤ 3፥10 & 6፥11-12) ታዲያ እነዚህ ሰዎች ቅዱሳን የሆኑት እንዴት ነው ስንል ቀደም ሲል የስጋቸውን እና የልቦናቸውን ፈቃድ የሚያደርጉ የነበሩ በበደላቸው የሞት ፍርድ የተገባቸው ነበሩ ነገር ግን በክርስቶስ በማመን የእግዚአብሔርን ምህረት የተቀበሉ ከስጋም ስራ ያመለጡ ሆነዋል ፤ በቀደመው ሥርዓት ቅዱስ የሚለው ስም ለሰዎች የሚሰጣቸው በሃይማኖት ተቋማት ሲሆን ቃሉም የሚፈታው <<ቅዱስ በሆነ ሕይወት ይፋዊ እውቅና ያገኘ>> በሚለው ሃሳብ ነበር ፡ የሞተ ሰውም እንደዛ ለመባል ያሰው በባህሪው እና በአኗኗሩ ነቀፋ የሌለበት ቢያንስ 2ተአምራትን ያደረገ መሆን ነበረበት ። ታዲያ እነዚህ ሰዎች ቅዱሳን የሆኑት እንዴት ነው ካልን በባሕሪም ይሁን በአኗኗር (ሐዋ 19) ፈፅሞ ተቃራኒዎች የነበሩ ቢሆንም ግን የቀደመው ህይወታቸዉ አሁን ላለው ህይወታቸዉ ምስክር ሊሆን አይችልም ምክንያቱም የተለያየ ዓለም ዉስጥ ነበሩ ያኛው አለም የኃጢኃት ዓለም ሲሆን ይሄኛዉ ደግሞ የፅድቅ ዓለም ነው <<ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው አሮጌው ሁሉ አልፏል>> ያረጀ እና የተናቀ ያለፈ ሕይወታቸው ነበር ያኛው ዛሬ ላይ በክርስቶስ ስራ በማመን ቅዱሳን ሆነዋል ላለፈው ሕይወት የሞቱና በአዲስ ሕይወት የተነሱ ሆነዋል ቅዱስ ለመባልም ነውር በሌለው የህይወት ኃይል ተነስተዋል ስለዚህ ኩነኔ የለባቸውም ፤ ሌላው <<በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት>> የሚለው ቃል እነዚህ ሰዎች አሁን ላይ በዓለም ስርዓት የሚኖሩ ሳይሆኑ በክርስቶስ የሕይወት ዓለም ውስጥ መሆናቸውን እና በክርስቶስ ማመናቸዉን ያስረዳል <<ቅዱስ>> <<የተለየ>>። <<ምእመናን>> ወይም ሌላ ትርጉሙ <<የታመኑ>> በክርስቶስ ኢየሱስ ያሉትን የሚያመለክት ነው ሰዎቹ የዳኑት ታማኞች ስለሆኑ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ስላመኑ እና ስለዳኑ ነው። [[2 ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።]] ከአባታችን እ/ር ከጌታም ኢየሱስ <<ፀጋ>> የግሪክ ሰላምታ <<ሰላም>> የአይሁድ ሰላምታ ነው፤ በኤፌሶን መፀሐፍ ጳውሎስ 12 ጊዜ ፀጋ የሚል ቃል ጠቅሷል <<ፀጋ>> <<ለማይገባቸው ሰዎች እግዚአብሔር ያሳየውን ቸርነት>> ያሳያል <<ሰላም>> ከእ/ር የሚገኝ የመንፈስ እረፍትና መረጋጋት ነው። ቁ፫ <በረከት> ይቀጥላል
Show all...
አለመደሰት አልችልም። እውነተኛ ደስታ ከውስጥ ወደ ውጭ የሚፈስ ነው፡፡ ከመንፈሳችን ይነሳና ነፍሳችንን አጥለቅልቆ ወደ ውጭ ይወጣል( ፊታችን የፈካ እንዲሆን ያደርጋል):: የእውነተኛ ደስታ መነሻ ስፍራው አካባቢ አይደለም፡፡ ብዙ ሰዎች ይጠይቁኛል፤ "አስቸጋሪ ሁኔታዎችና ማይመች አካባቢ ውስጥ ሆነህ እንኳ ምትደሰትበት ሚስጥሩ ምንድነው?" ይሉኛል፡፡ መልሴ፡ "የደስታዬ ምንጭ( source) አካባቢዬና ሁኔታዎቼ አይደሉም" የሚል ነው፡፡ ጳውሎስ፡ የፊልጵስዩስ ክርስቲያኖችን "# ሁልጊዜ # በጌታ ደስ ይበላችሁ" ነው ያለው፡፡ የሚገርመው፡ ጳውሎስ ይሄን መልዕክት የተናገረው እስር ቤት ውስጥ ሆኖ ነው፡፡ ሰው፡ እስር ቤት ውስጥ ሆኖ እንዴት "#ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ" ሊል ይችላል? ...አዎን፡ ይቻላል! እውነተኛ ደስታ ከውስጥ-ወደውጭ( Inside-out) ነው የእኔ ደስታ የተመሰረተው ከውስጥ ወደ ውጭ እንጂ ከውጭ ወደ ውስጥ አይደለም። በአመት 365 ቀን 12 ወር 8760 ሰአት 525600 ደቅቃ 31536000 ሰከንድ 892160000 ማይክሮ ሰከንድ ደስተኛ ብቻ ነኝ አለመደሰት አልችልም ።
Show all...
በአፍጋኒስታን ነገ ከሰዓት በኋላ የሞት ፍርድ ለተፈረደባቸው 229 ክርስቲያን ሚስዮናውያን ጸልዩ ሊጎዱ ነው ብዙ ሰዎች መጸለይ እንዲችሉ እባክዎን ይህንን መልእክት በተቻለ ፍጥነት ያስተላልፉ። ይህ መልእክት የተላከው በጁዲት ካርሞና ሚስዮናዊው በአፍሪካ ከሚገኘው ከቺዋዋዋ ነው። መላው ፕላኔት በጸሎት አንድ ሆነ። እርስዎ ማስተላለፍ ከቻሉ እባክዎን በአፋጣኝ ጸሎት እኛን ይቀላቀሉ ፣ ምክንያቱም አክራሪ እስላማዊ ቡድኑ በኢራቅ ውስጥ ትልቁን የክርስቲያን ከተማ ኳራጎሽን ሰለተቆጣጠሩት አሁን በመቶዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያን ወንዶች ፣ ሴቶች እና ልጆች ሊገደሉ ባሉበት ሰአት የጸሎት ሽፋን እየተጠየቀ ነው። እባክዎን አንድ ደቂቃ ወስደው ጸልዩላቸው። ለሚችሉት ሁሉ መልዕክቱን ያስተላልፉ። ኳራጎሽ ቀድሞውኑ ብዙ ጊዜ ተወስዷል። ፀሎት ጠይቀውናል እባክዎን ለሌሎች ያስተላልፉ።
Show all...
. ክርስቲያን ነኝ በረከት ተስፋዬ || Gospel Song sʜᴀʀᴇ◈📲JOIN📲◈sʜᴀʀᴇ 🔰ኢየሱስ እንደቃሉ ይመጣል sʜᴀʀᴇ◈📲JOIN📲◈sʜᴀʀᴇ 💡 𝑱𝑶𝑰𝑵 @jesusfollowing ⚠️ 🗣 መዝሙር ለመላክ ✉ @ushisha 😐
Show all...
. የመጨረሻ ቃልኪዳን ንጉሴ || New song ⏰9:26Min 📥26.6MB 🔰ወንጌል ክርስቶስ ነው🔰 Share 📲 Share 📲 Share 💡 𝑱𝑶𝑰𝑵 @jesusfollowing ⚠️ 🗣 መዝሙር ለመላክ ✉ @ushisha 😐
Show all...
. የመጨረሻ ቃልኪዳን ንጉሴ || New song ⏰-9:26Min📥-5.4MB
Show all...
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!