cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Meleket Tube

መንፈሳዊ መረጃዎችን እንዲሁም ዝማሬዎችና የወንጌል ትምህርቶች በየእለቱ ከዚህ ገፅ ያገኛሉ። ኢየሱስ በክብር ይመጣል! Find us on more- https://linktr.ee/meleket_tube Contact us - @LiveMeleket_Bot

Show more
Ethiopia1 618The language is not specifiedReligion & Spirituality7 261
Advertising posts
12 379Subscribers
-324 hours
-297 days
-15430 days
Posts Archive
https://t.me/notcoin_bot?start=r_577266_33236117 🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift 🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
Show all...
#ካውንስሉ_አስቸኳይ_መግለጫ_ሰጠ በወንጌላዊያን አማኞች እና አብያተክርስቲናት ላይ እየደረሰ ስላለዉ ጥቃት ህዳር 27 ቀን 2016ዓ/ም መግለጫ_ሰጠ። 1-ባለፋት ዘመናት በተለይ በደርግ ዘመን የተወረሱ የቤተክርስቲያን ይዞታዎች በኢሕአዴግ ዘመን በከፊል ቢመለሱም እስካሁን ያልተመለሱ የኦሎምፒያ መሰረተክርስቶስ፣ የአዲስ ከተማ ገነት፣ የኢትዮጵያ ወንንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ብረት የሆነው የጉድ ሼፐርድ ማዕከል ፣ቄራ አካባቢ ያለው የብርሃነ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ፣እና ሌሎች እስካሁን ያልተመለሱ ይዞታዎች ሲሆኑ እነዚህ ይዞታዎች የቤተክርስቲያን ንብረት በመሆናቸዉ እንዲመለሱ ተጠይቋል። 2-የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ይዞታዋን ለቃ እንድትነሳ የከተማዉ አስተዳደር የወሰንኑ ቢሆንም የከተማዉ አስተዳደር እና የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እንዲሁም የካውንስሉ አመራሮች ሰፊ ዉይይት አድርገዉ የከተማዉ አስተዳደር ጉዳዩን እየመከረበት ይገኛል።የከተማዉ አስተዳደር የደረሰበትን ደረጃ በአጭር ጊዜ ግልፅ እንዲያደርግ ተጠይቋል። 3-የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ይዞታ ነጥቆ የራሱ ጽህፈት ቤት አድርጎት ይገኛል።እንዲሁም የቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን ይዞታ የሆነዉን የኩሪፍቱ የጸሎት ማዕከል በተመለከተም በማእከሉ ምንም አይነት የልማት ስራ ቤተ ክርስቲያን እንዳታከናወን በማገድ የቤተክርስቲያኑን ይዞታ ለመንጠቅ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝኝ ተገልጾ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከዚህ ህገወጥ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እና የወሰደዉን የቤተክርስቲያን ንብረት እንዲመልስ ተጠይቋል። 4-በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው የሸገር ከተማም የፈረሱ የወንጌላዊያን የእምነት ተቋማት ይዞታቸዉ እንዲመለስ እንዲሁም በከተማዋ ለ23 አብያተክርስቲያናት ከካቢኔ ቦታ ተወስኖላቸዉ ቦታቸዉን መረከብ ላልቻሉ በአፋጣኝ ካቢኔ የወሰነዉ ዉሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ተጠይቋል። 5-የመቃብር ስፍራን ጥሶ በመግባት እየተደረገ የሚገኘዉ አግባብ ያልሆነ ተግባር በአስቸኳይ እንዲቆም 6-በምዕራብ ኢትዮጵያ በቄለም ወለጋ ዞን በጊዳሜ ወረዳ ዘጠኝ ምእመናንን የአምልኮ ስነስርአት እየፈፀሙ ካሉበት ሌሊት ላይ ተወስደዉ መረሸናችው እጅግ አሳዛኝ እንደሆነና ለነዚህ ንፁሃን ፍትህ እንዲሰጥ ተጠይቋል። በአጠቃላይ ፍትህ ያስፈልጋል ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ሊከበሩ ይገባል ይህ ሁሉ እየሆነ ያለዉ የታችኛዉ የመንግስት አካል የመንግስትን ስልጣን በመጠቀም ጥቂት ግለሰቦች የግል አጀንዳ ይዘዉ የሚፈፅሙት ተግባር ነዉ። የፌደራል መንግስት ጣልቃ በመግባት ፍትህ ሊያሰፍን ይገባል ሲል የኢትዮዽያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል በመግለጫዉ አስታዉቋል።
Show all...
👍 14
ኢየሱስ ይፋዊ አገልግሎቱ እስኪደርስ ድረስ በየት ከተማ ውስጥ ነበር ሲጠብቅ የቆየው?Anonymous voting
  • ቤተሳይዳ
  • ገሊላ
  • ቅፍርናሆም
  • ናዝሬት
0 votes
16
አስደሳች ዜና! እንደ "ዴስፓሲቶ" እና "ጋሶሊና" በመሳሰሉት በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂው ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው የአለማዊ ዘፈን አቀንቃኝ የነበረው የፖርቶ ሪኮ ራፐር ዳዲ ያንኪ ህይወቱን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለመስጠት እንደወሰነ እና ከአለማዊው ሙዚቃ እራሱን እንዳገለለ አሳውቋል። "እንደ ሙዚቃ፣ ማህበራዊ ሚዲያ፣ መድረኮች፣ ማይክራፎን ኢየሱስ የሰጠኝ በእጄ ውስጥ ያሉኝ መሳሪያዎች ሁሉ አሁን ለመንግስቱ ነው ሲል ተናግሯል።" Join➴ @MELEKET_TUBE
Show all...
👏 18 8👍 5🙏 3😢 1
Godina Qellem Wallagaa, Aanaa Gidaamiitti ajjeechaa Amantoota irratti raawwate ilaalchise Ibsa WKWW Mekane Yesus Itiyoophiyaatiin kenname. Sadaasa 24-2016 ህዳር 25 ቀን 2016 የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በቄለም ወለጋ ዞን በተለይም በጊዳሚ አውራጃ በአባላቶቹ ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።
Show all...
👍 6😢 3 1
ራሴን ስመለከት እንዴት ልድን እንደምችል አይታየኝም ክርስቶስን ስመለከት እንዴት ልጠፋ እንደምችል አይታየኝም፡፡
ማርቲን ሉተር
Show all...
11
♦#የልሳን_(#የቋንቋ)#ስጦታ♦ =========================== 📌 1 ቆሮ 14:40 #ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን። 👉#ልሳን ማለት ምን ማለት ነው? -------------------------- ✍️አዲስ ኪዳን በተጻፈበት በግሪክ ቋንቋ ግሎሳ (γλῶσσα) የሚል ቃል ሲሆን “ልሳን" የሚል ፍቺ ይዟል። ይህም ምላስንና ቋንቋን የሚያመለክት ነው። ✍️ከዚህ የተነሳ ልሳን ማለት ቋንቋ ማለት ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ለክርስቶስ አካል(ለቤተክ) ጥቅም እንደወደደ እያካፈለ ለቅዱሳን ከሚሰጣቸው ከብዙ የፀጋ ሥጦታወች መካከል አንዱ ነው። 1ቆሮ 12:7 ✍️ በልሳን(በቋንቋ) መናገር መንፈስ ቅዱስ ከሚሰጣቸው ብዙ ስጦታወች መካከል አንዱ ሲሆን የሰው ልጆች በሚሰሙት እና በሚናገሩት ቋንቋ ያለ ሰዋዊ ጥበብ (ልምምድ ) በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት መናገር እና ቅዱሳንን ማነጽ ነው። ✍️ የፀጋ ስጦታ ነው ማለት ተቀባዮ በየትኛውም ሰዋዊ ጥበብ እና ልምምድ ሊያገኘው የማይችለው ከእግዚአብሔር የሆነ ነፃ ሥጦታ ነው። ✍️ የትኛውም የፀጋ(ነፃ) ስጦታ ለአካል (ለቤተክ) ጥቅም የሚሰጥ እንጂ ለግል ጥቅምና ለማፍረስ የሚሰጥ እንዳልሆነ ልብ ልንል ይገባል ። ❤#ስለ_ልሳን_መጽሐፍ_ቅዱስ_ምን_ይላል፦ =================== የልሳን የጸጋ ስጦታ በብሉይም ዘመን ትንቢት የተነገረለት የጸጋ ስጦታ ነው። 📌ኢሳይያስ 28 11፤ በባዕድ አፍ በልዩም ልሳን ለዚህ ሕዝብ ይናገራል፤ 12፤ እርሱም፡— ዕረፍት ይህች ናት፥ የደከመውን አሳርፉ፤ ይህችም ማረፊያ ናት፡ አላቸው፤ እነርሱ ግን መስማትን እንቢ አሉ።(ዘዳ 58:49-50) ✍️በአዲስ ኪዳን ስለ ጸጋ ስጦታዎች አስቀድሞ ያስተማረው ኢየሱስ ነው። በእርሱ የሚያምኑ ሁሉ የተለያዩ ምልክቶች(የጸጋ ስጦታወች) እንደሚከተሉአቸው ኢየሱስ ይናገራል፦ 📌 ማርቆስ 16:17 ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ #በአዲስ #ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ 🤔 ምልክቶች(የጸጋ ስጦታዎች) ቅዱሳንን የሚከተሉ እንጂ የሚቀድሙ እንዳልሆኑ አንባቢው ልብ ሊል ይገባል። 📌 ሐዋ. ሥራ 2:4- በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ #መንፈስም #ይናገሩ #ዘንድ #እንደ #ሰጣቸው #በሌላ #ልሳኖች(ቋንቋዎች) #ይናገሩ ጀመር፦ ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ። ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ፡— እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እኛም እያንዳንዳችን የተወለድንበትን የገዛ ቋንቋችንን እንዴት እንሰማለን? 🔥 ከተለያዩ ሀገሮች የመጡ አይሁዶች እና ወደ አይሁድ እምነት የተቀየሩ ሰዎች በዓለ 50ን ለማክበር በተሰበሰቡበት በተወለዱበት እና በሚኖሩበት ሀገር ከ 16 ባላነሱ በተለያዩ ልሳኖች(ቋንቋዎች) 120 የሚሆኑ አማኞች በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው የእግዚአብሔርን ታላቅ ስራ ተናግረዋል ብዙዎችም ወደ እውነት ተመልሰዋል። 📌 መንፈስ ቅዱስ እንደወደደ_እያካፈለ የጸጋ ስጦታን እንዴት እደሚሰጥ እና #ጌታ ኢየሱስ በጉባኤ ውስጥ ስርዓት ያለው አምልኮ ምን መምሰል እንዳለበት በሐዋርያው ጳውሎስ በኩል ለአብያተክርስቲያናት ሁሉ መመሪያ እና ድንጋጌ ይሰጣል፦ =========================== 📌 1 ቆሮንቶስ 12:10- 1 ለአንዱም ትንቢትን መናገር፥ ለአንዱም መናፍስትን መለየት፥ ለአንዱም በልዩ ዓይነት ልሳን መናገር፥ ለአንዱም በልሳኖች የተነገረውን መተርጎም ይሰጠዋል፤ ይህን ሁሉ ግን ያ አንዱ መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻው እያካፈለ ያደርጋል። ✍️ ለአንዱም ይላል እንጅ ለሁሉም እንዳላለ ልብ እንበል። ስለዚህ ሁላችንም ልንናገር አንችልም። 📌 1 ቆሮንቶስ 14:27 ፤ በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም፤ የሚተረጉም ባይኖር ግን በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር። ✍️ ይህ የጌታ ድንጋጌ መሆኑን ልብ እንበል በጉባኤ መካከል ሁለት ቢበዛ ሶስት ደግሞ በየተራ እና ተርጓሚ ከሌለ አይቻልም። ታድያ አሁን በየቤተክርስቲያኑ እየሆነ ያለው ነገር ምንድነው ሁላችንም እንጮሀለን የሚለውን ከየት አመጡት። 📌 1 ቆሮንቶስ 14:13 ስለዚህ በልሳን የሚናገር እንዲተረጉም ይጸልይ። 📌 1 ቆሮንቶስ 14 11 እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል። 📌 1 ቆሮንቶስ 14 :16 እንዲያማ ካልሆነ፥ አንተ በመንፈስ ብትባርክ ባልተማሩት ስፍራ የተቀመጠው የምትለውን ካላወቀ እንዴት አድርጎ ለምስጋናህ አሜን ይላል? 📌 1 ቆሮንቶስ 14:26 እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ምንድር ነው? በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለእያንዳንዱ መዝሙር አለው፥ ትምህርት አለው፥ መግለጥ አለው፥ በልሳን መናገር አለው፥ መተርጐም አለው፤ #ሁሉ #ለማነጽ #ይሁን። ✍️ የትኛውም የጸጋ ስጦታ ዋና አላማው ቅዱሳንን ማነጽ እንጂ መዝረፍና መጉዳት አይደለም 📌 1 ቆሮንቶስ 14:39 ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ፥ በልሳኖች ከመናገርም አትከልክሉ፤ ነገር ግን #ሁሉ #በአገባብና #በሥርዓት #ይሁን። 📌 1 ቆሮንቶስ 14 33፤ እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና፤ በቅዱሳንም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲህ ነው። ❤ #ቅዱሳን_ሊጠነቀቁ_የሚገባቸው፦ ========================= ✍️ 1 #ቆሮንቶስ 3:18 #ማንም_ራሱን_አያታልል ..... 📌(1) ልሳን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እንጂ መንፈስ ቅዱስ አይደለም። 📌2) ልሳንን ሰዎች (አገልጋዮች) የሚሰጡት አይደለም ። 📌3) ልሳን ካልተናገርክ ምኑን ዳንከው በማለት የመድረክ አገልግሎት ለቅዱሳን መከልከል ተገቢ አይደለም። 📌4) ልሳን በልምምድም የሚገኝ አይደለም። 📌5) ልሳን ለሁሉም ሰው(አማኝ) የሚሰጥ አይደለም። 📌6) የኔ የመላእክት ልሳን ነው በማለት ራስንም ቅዱሳንን ማታለል ተገቢ አይደለም። 📌7) ሁላችንም ለ 10 ደቂቃ በልሳኖቻችን እናወራለን እያሉ የእግዚአብሔርን ጉባኤ መረበሽ መንፈሳዊነት አይደለ። 📌8)የኔ የማይተረጎም ልሳን(ቋንቋ) ነው በማለት እና ቋንቋ ያልሆነ ተደጋጋሚ ቃል በመደጋገም ቅዱሳንን ማወክ መንፈሳዊነትም መጽሐፍ ቅዱሳዊም አይደለም። 📌 1 ቆሮንቶስ 14 33፤ እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና፤ በቅዱሳንም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲህ ነው። 📌 1 ቆሮንቶስ 14 37፤ ማንም ነቢይ ወይም መንፈሳዊ የሆነ ቢመስለው ይህች የጻፍሁላችሁ የጌታ ትእዛዝ እንደ ሆነች ይወቅ፤ ፀጋ እና ሰላም ለሁላችን ይብዛ።
Show all...
👍 10 3
ትቤላ ኤልሳቤጥ ለማርያም ሶበሰማይኩ ቃለኪ አንፈራፀ እጓል በውስተ ከርስየ ወብፅይት አንቲ። እንተ ተአምኒ ዘነከሩኪ እፎኑ ይከውነኒ ከመትምፅኢ እሙ ለእግዚእየ። ሉቃስ ወንጌል 1:41-43
Show all...
2
#ይድረስ_ለወንጌል_አማኞች_በሙሉ.... (እባክዎ መልዕክቱን ሼር ያድርጉ) በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ኩሪፍቱ ማዕከል የቃለህይወት ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን የሁሉም ወንጌላውያን አማኞች ንብረት የሆነ፣ ብዙዎቻችን በግል እና በቡድን እየሄድን ለቀናት የፀለይንበት ስፍራ ነው። በዚህ ስፍራ ሄዶ ያልተገለገለ፣ ያልፀለዬ አማኝ ይኖራል ማለት ዘበትነው። በአዲሳባ ያሉ ሁሉም ቸርቾች ወጣ ብለው የሪትሪት፣ የፆምፀሎት ፣ የህብረት ጊዜ ማሳለፍ ሲፈልጉ የመጀመሪያም የመጨረሻም ተመራጩ ቦታ ይህ የኩሪፍቱ ቃለህይወት ነው። ይህ ስፍራ በከተማ አስተዳደሩ ከቸርች ተነጥቆ ለግለሰቦች ሊሰጥ መሆኑን በትናንትናው ዕለት ቸርቿ ይፋ አድርጋለች። ይህ የሁሉም አማኝ ቅርስ ከቤተክርስቲያን በግፍ ከመነጠቁ በፊት ሁላችሁም የወንጌል አማኞች ድምፃችሁን እንድታሰሙ ጥሪ እናቀርባለን። እባኮ መልዕክቱን ሼር ያድርጉ...
Show all...
👍 23👏 2
#ቤቱ_ራሱ_ይናገራል፤ ለጸሎት ቤት እንጂ ለሌላ አልተፈጠርኩም ይላል። በአዲስአበባ ከተማ ከ1954 ዓም አንስቶ የመጀመሪያው የመሠረተ ክርስቶስ ጸሎት ቤት በደርግ ያለሕግ ወርሶ ግቢውን ትምህርት ቤት "#የአብዮት_እርምጃ" ብሎ ሰየሙት ጸሎት ቤቱን ግን የስፖርት መሥሪያ አደረጉት። #ቤቱ_የጸሎት_ቤት_ይሁን!! #MKCchurch @meleket_tube
Show all...
👍 16
የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናንን ወቅታዊ ሁኔታ በመሚመለከት ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን  መካነ ኢየሱስ የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፤ የድሬዳዋ ማህበረ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን ህንጻና ሌሎች ተያያዥ ህንጻዎች ያሉበትን ይዞታ ለሌላ አገልግሎት ለማዋል በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካብኔ የተላለፈው ውሳኔ ቤተ ክርሰቲያናችንን ብቻ ሳይሆን መላውን ህዝበ ምዕመን በእጅጉ አስደንግጧል፡፡ እናም ውሳኔው እንደገና እንዲጤን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ብርቱ ክትትል በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ የከተማው አስተዳደርም በተለይም ክቡር ከንቲባው ሁኔታውን በጥንቃቄና በሃላፊነት ስሜት እየተከታተሉ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ጋርም ለመምከር ቀጠሮ ተይዟል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳዩ የማይመለከተውና በየትኛም መንገድ ድርሻ የሌለው አንድ አካል፤ ችግሩ መፍትሔ እንዳገኘ አድርጎ በዛሬው ዕለት በራሱ ማህበራዊ ገጽ (Facebook) የተሳሳተ መረጃ አውጥቷል፡፡ ይህን የፈጸመው አካል ይህንን ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርም ጥብቅ ማሳሰቢያ የደረሰው መሆኑን እየገለጽን ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከምታውቀው ድረስ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ምንም ዓይነት ውሳኔ ያልተሠጠ መሆኑንና ለወደፊትም ቤተ ክርስቲያኒቱ በራስዋ አሠራር ኦፊሴላዊ መረጃ እስከምትሰጥ ድረስ ህዝበ ምዕመኑ በትዕግስትና በጸሎት እንዲጠባበቅ እናሳስባለን፡፡ እግዚአብሔር አገራችንን ይባርክ፤ ይጠብቃትም! የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ
Show all...
👍 2
የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ልትፈርስ ነው! የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ቤ/ክ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ፈርሳ እንድትነሳ መንግስት ወሰነ። ቤተ ክርስቲያኗ ያለፉትን 40 አመታት በስፍራው ህጋዊ የይዞታ ካርታ ኖሯት፣ መንፈሳዊ ስራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይሁን እንጂ የከተማ አስተዳደሩ ስፍራው ለሆቴል ግንባታ ይፈለጋል በሚል ምክኒያት ባስተላላፈው ውሳኔ መሰረት እንድትፈርድ ሲል ያስተላለፈው ውሳኔ ደብዳቤ ለክርስቲያንዜና ደርሶታል። በአሁኑ ወቅት ማህበረ ምዕመናኗ ባለ ይዞታነቷን ለማስጠበቅ ከዋናው ቢሮ ጋር እየሰራች ትገኛለች። በተጨማሪም የሃላባ ቃለ ህይወት ቤ/ክ እና የቢሾፍቱ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክንም በርካታ ስደቶች እየደረሰባቸው ይገኛል። እነዚህኑ ጉዳዮች በተመለከተ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ዛሬ ጥቅምት 12 ላይ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ©ክርስቲያን ዜና @meleket_tube
Show all...
😢 5👍 3 1🥰 1
/Purgatory
Show all...
​​የ16ኛው ክፍለ ዘመን ተሐድሶው ሲጀምር በኦክቶበር 31፣ 1517 ዓመተ እግዚ አንድ ብዙም የማይታወቅ መነኩሴ በአንዲት ትንሽ የጀርመን ዩኒቨርስቲ ውስጥ የመጽሐፍ ቅዱስ ፕሮፌሰር የነበረ ሰው በዩኒቨርስቲው ቅጥር ውስጥ በሚገኘው የቤተ ክርስትያን በሮች ላይ የተወሰኑ አናቅጽት የያዙ ወረቀቶችን ለጠፈ። እነዚያን ወረቀቶች በቤተ ክርስትያን አደባባይ ላይ የለጠፈበት ምክንያት የቤተ ክርስትያኑ አደባባዩ ለዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ እንደ ማስታወቅያ ሰሌዳ ያገለግል ስለነበር ነው። በለጠፈው ወረቀት ውስጥ 95 አናቅጽት (Thesis)ወይም አረፍተ ነገሮች ሰፍረዋል። የአናቅጽቱ ዋነኛ ትኩረትም ''የኃጢአት ይቅርታ ሰነድ'' ' indulgence  የመሸጥ ልምምድ ከጳጳሱ ፍቃድ የተሰጠውና ሰው 'ፑርጋቶሪ'/Purgatory (ነፍስ ወደ ገነትም ሆነ ሲኦል ከመውረዷ በፊት የምትሆንበት ስፍራ) ውስጥ በምድር በሕይወት እያለ ስላጠፋው ስለሃጢያቱ የሚቆይበትን ጊዜ (ወደ መንግስተ ሰማይ ከመግባቱ በፊት) በሚገዛው 'ኢንደልጀንስ' መቀነስ ይችል ስለነበረ ነው። ይህ 'ኢንደንጀልስ' በወረቀት የሰፈረና የቤተ ክርስትያንን ይሁንታ አግኝቶ መግዛት ለቻለ ሁሉ የቀረበ ነበር። ህዝቡም ኢንደልጀንሱን ይገዛ ዘንድ 'ቅቤ አቅልጥ' የሆኑ አሻሻጮች ነበሩ። ህዝቡ ለራሱ፣ ለዘመዱና ለወዳጁ ይገዛ ነበር፣ ለሞቱት እንኳን ሳይቀር። ሉተር 95 አናቅጽቱን ጽፎ ሲለጥፋቸው ዩኒቨርስቲ ውስጥ ባሉት ፕሮፌሰሮች መሃል ውይይት እንዲፈጥር በማሰብ ነበር። ነገር ግን ዘጠና አምስቱ አናቅጽት ከዊተንበርግ ፕሮፌሰሮች ከባቢ በዘለለ በመላው የጀርመን ግዛቶችና በጠቅላላው የካቶሊክ ቤተ ክርስትያን ዘንድ ታላቅ ሁካታን ለመፍጠር በቃ። በአጭር ጊዜ ውስጥም ብዙ ህዝብ የዚህን መነኩሴ ስም ማወቅ ጀመረ፣ በዊተንበርግ ዩኒቨርስቲ የሥነ መለኮት ዶክተሩን ማርቲን ሉተርን። ህዝብን በማወክና ባለመታዘዝ ቤተክርስትያን ከሰሰቸው፣ በጀርመን ንጉስ ፊትም ራሱን እንዲከላከልና ያደረገው ሃሰት መሆኑን አውቆ እንዲያስወግድ ታዘዘ። ያደረገው ስህተት መሆኑን ባለመቀበሉ ምክንያት የውጤቱን ስሜት 500 ዐመታትን ተሻግሮ ዛሬ እኛም ይሰማናል። እነዚህ የተሐድሶው ማኮብኮብያ የነበሩት የተወሰኑ የወረቀት ቁርጥራጮች እንዴት ይህንን የሚያህል  ትኩረትና ያልተጠበቀ አስደንጋጭ ውጤት አመጣ ብሎ ማሰብ አስፈላጊ ነው። በተመሳሳይም የማርቲን ሉተር አስተምህሮ ከእሱ በፊት ከተነሱት  ከነፒተር ዋልዶ፣ ጆን ዊክሊፍና ጆን ሁስን ከመሳሰሉ ተመሳሳይ አስተምህሮ ከሚከተሉት በላይ ገኖ የወጣበትን ምክንያት መጠየቅ ደግ ሳይሆን አይቀርም። ከሉተር መቶ አመት በፊት የነበረው ጆን ሁስ በተቃውሞ ምክንያት በእሳት ተቃጥሎ እየሞተ በነበረባት ሰዓት "በቀጣይ 100 አመት ውስጥ እግዚአብሔር አንድ ሰው አስነስቶ የማይቆም ተሐድሶን ያቀጣጥላል" ያለው ትንቢት ያለምክንያት አልነበረም። ከላይ ላነሳናቸው ጥያቄዎች መልሱ የሚገኘው በወቅቱ የካቶሊክ ቤተ ክርስትያንና ምዕራብ አውሮጳ የነበሩበት ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ነው። በ15ኛው ክፍለ ዘመን የተከወኑ ሁነቶች ተሐድሶ እውን እንዲሆን በር ከፋች ነበሩ። ሶስት መሠረታዊ ነገሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። የመጀመሪው የእውቀት ከቤተ ክርስትያን ቁጥጥር ውጪ መሆን ነው። የእውቀር መስፋፋት ቤተክርስቲያን በእውቀትና ትምህርት ላይ የነበራት ሙሉ ተጽእኖ እንድትነጠቅ አድርጓታል። በዚያ ላይ የማተሚያ ማሽን መገኘቱ እውቀት በቀላሉ ተደራሽ እንዲሆን አስተዋጽኦው ከፍ ያለ ነበር። በርግጥ ተሐድሶው የተቀጣጠለው በታተሙ ወረቀቶች ነበር። ሁለተኛው የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊዉ የሃይል ሚዛን ለውጥ ማድረጉ ነው። አውሮጳ የተለያዮ የንግድ መስመሮችን ያገኘችበትና ሃብት በብዛት ወደ መንግስታት የገባበት ወቅት ነበር። መንግስታት ከሮም ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በላይ በለጠጋ በመሆናቸውና ሃብታቸውን ማጋራት ባለመፈለጋች ኢኮኖሚያዊ ቅራኔ ነበራቸው። ተሐድሶው የተራ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ብቻ ሳይሆን የገናና መንግስታትና የመሃከለኛ መደብ ልሂቃን ጥያቄ ጭምር በመሆኑ ስኬትን አገኘ። ሦሥተኛው ምክንያት የቤተክርስትያን መሪዎች ከእረኝነት ይልቅ አምባገነን ገዢነታቸው ማየሉ ተሓድሶው እንዲሳካ መደላድል ፈጥሯል። ቤተክርስቲያን ትኩረቷን ከመንፈሳዊ አገልግሎት ይልቅ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ አድርጋ ነበር። በመንፈሳዊነት ስም ገንዘብ መሰብሰብ ባህልና ልማድ ሆኖ ነበር። ስለዚህ…የነዚህን ምቹ አጋጣሚዎችን ስናይ እንዲያው ዝም ብሎ አጋጣሚ ሳይሆኑ መለኮት ቤተ ክርስቲያንን ከወደቀችበት ለማስነሳት ጽዋው እንደሞላ ያሳየናል። ነገሮችን እያሰናሰኘ ሁኔታዎችን እያስማማ ተሓድሶውን በትክክለኝ ጊዜ አምጥቷታል። ለዚህም ነው ይህ ተሐድሶ እግዚአብሔር በትክክለኛው ጊዜ ለቤተክርስትያን የላከው ነው የሚባለው። በዚህም ተሐድሶ ምክንያት እግዚአብሔር የመላ አለሙን ፊት ቀይሮታል። የእኛም ዘመን የመላሸቅ ጥልቀት ተሓድሶን እንድንሻ የሚያደርገን ይመስለኛል። እኛም ተሐድሶ ያሻናል! #ተሐድሶ #ክርስትና #የትሩፋን_ናፍቆት አማኑኤል አሰግድ @meleket_tube
Show all...
6👍 3
ቄስ አለሙ ሼጣ ማረፉ። ህብረቱ በጉዳዩ ላይ ይህን ብሏል.. "የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረትን ከመጋቢት 1999 ዓ.ም እስከ ኅዳር 2008 ዓ.ም በዋና ጸሐፊነት የመሩት ቄስ ዓለሙ ሼጣ በዛሬው ዕለት ወደ ሚወዱትና ወዳገለገሉት አምላካቸው ዕቅፍ ተሰብስበዋል። ኅብረቱን በታማኝነትና በጥበብ በመምራት በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ የነበሩት ወንድማችንና አባታችን ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም ድካም በማረፍ ሞቶ ወደ ተቤዣቸው ጌታ ክብር ገብተዋል። የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት፣ በወንድማችን፣ በሥራ ባልደረባችንና በአባታችን እረፍት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን እየገለጸ፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸውና ለመላው ወንጌላውያን አማኞች መጽናናትን ይመኛል።" @meleket_tube
Show all...
😢 22👍 1
ቅዱስ ቃሉን የመተርጎም ዋጋ: ዊልያም ቲንዴል .. ከዛሬ 487 ዐመታት በፊት በዛሬው ዕለት መጽሐፍ ቅዱስን ከላቲን ወደ እንግሊዘኛ በመተርጎሙ ምክንያት በአደባባይ በቋሚ እንጨት ታስሮ ዊልያም ቲንዴል እንዲቃጠል ተደረገ።  ቅዱሱን መጽሐፍ በአገሬው ቋንቋ ስለተረጓመ ብቻ በአደባባይ ጭካኔያዊ ግድያን ተገደለ። እጃችን ላይ ያለው መጽሐፍ ቅዱስ እጃችን ላይ እንዲገባ ብዙ ሰማዕትነት ተከፍሎበታል። ዊልያም ቲንዴል መጽሐፍ ቅዱስን ከዋናው እብራይስጥና ግሪክ ቋንቋ ወደ እንግሊዝኛ በመተርጎሙ ምክንያት ለእስር፣ ለእንግልትና መከራ ተዳርጓል። በወጣትነት እድሜው ታዋቂ የኦክስፎርድ ተመራማሪና የነገረ መለኮት ሊቅ ሆኖ ከመኖር ይልቅ የበራለትን የቅዱሱን ቃል እውነት ለሁሉም ለማሳወቅ ሲል ተሳዳጅ ሆነ። የማይነቀነቀውን የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ስልጣንን ቃሉን ሁሉም እንዲያነበውና ወደ ጸጋው እውነት እንዲመለስ በማለት በቅዱሳት መጽሐፍ ትርጓሜ ነቀነቀው። በዚህም ምክንያት በ30 ዐመቱ የሞት ፍርደኛ በመሆን ወደ ቤልጀም ተሰደደ። ስደቱ መከረኛና እስር የበዛበት ነበር። በዚያም ውስጥ ሆኖ ግን ትርጉሙን ከማጠናቀቅ ወደ ኋላ አላለም። ለአስራ ሁለት ዐመታትም በስደት ከተንገላታ በኋላ በዚህ እለት (6 October 1536) ብራሰልስ ከተማ አደባባይ ላይ በቁሙ በእሳት አጋይተውት በ41 ዐመቱ አንቀላፋ። #ተሐድሶው #ዊልያም_ቲንዴል በአማኑኤል አሰግድ @meleket_tube
Show all...
11👍 6
የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን መንፈሳዊ ማህበራዊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታን በተመለከተ ሃገራዊ የጸሎት አዋጅ አወጀች። ቤተክርስቲያኗ ለሁሉም የመሰረተ ክርስቶስ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ባስተላለፈችው መልዕክት  የጥቅምት አራቱ እሁዶች የንስሃ እና የምልጃ ጸሎት እንዲደረግበት መወሰኑን ገልጻለች። በዚህም መሰረት በምደሪቱ ላይ ስለፈሰሰው የሰው ደምና የጠፋው የሰው ነፍስ በዚህም ምክኒያት ለደረሰው መከራና ስቃይ ሁሉ እግዚአብሄርን ምህረት መለመን እንዲሁም እግዚያብሔር አምላክ በህዝቡ መካከል መከባበርን መቀባበልን እና መፈቃቃርን እንዲሰጥ ጦርነትና መገዳደል ቆሞ ሰላም እንዲሆን ምዕመናኑ በትጋት እንዲጸልዩ ጥሪ አቅርባለች። @meleket_tube
Show all...
17👏 4👍 3
ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት አስተምህሮ፣ ልምምድና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥነ-ምግባር በተቃረነ መንገድ በመጓዝ የሚታወቀው "ነቢይ" ዑርበርት ኤንጅል፣ ኢትዮጵያ ገብቷል፤ ግለሰቡ ከመሰሎቹ ጋር በመሆን ሕዝቡን ለማጭበርበር የተዘጋጀ በመሆኑ፣ ለቃሉ እውነት የቆመ ወንጌላዊ አማኝ ሁሉ ድርጊቱን በጽኑ ሊቃወም ይገባል። የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት። @meleket_tube
Show all...
በመድረኮቻችን ኢየሱስ ይሰበክ #kaluproject @MELEKET_TUBE
Show all...
በሕይወት ዘመናችሁ በአስቸጋሪ ኹኔታ ውስጥ በገባችሁ ጊዜ እንዲህ ማለትን ልመዱ። በመጀመሪያ፥ “እዚህ ቦታ ያቆመኝ እግዚአብሔር ራሱ ነው። በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ ያለሁትም በእርሱ ፈቃድ ነው”በሉ። ቀጥሎ፥ “በዚህ ውስጥ እያለሁ እግዚአብሔር በፍቅሩ ይንከባከበኛል፤ ልጁ እንደ መኾኔም መጠን፥ እንድመላለስበት ባሠመረው የሕይወት ልክ ለመኖር እንድችል በዚህ የፈተና ወቅት ጸጋውን ይሰጠኛል”በሉ። በዚያ ላይ፥ “መከራውን ወደ በረከት ይለውጥልኛል፤ እንድማር የሚፈልገውን ነገር እንድቀስም እኔን ከማስተማሩ ጐን ለጐን ሊሰጠኝ የሚፈልገውን ጸጋ በእኔ ውስጥ እንዲሠራ ያደርገዋል”በሉ። በመጨረሻም፥ እንዲህ በሉ፥ “የእርሱ ትክክለኛ ጊዜ ሲደርስ ካለሁበት ኹኔታ ውስጥ መልሶ ሊያወጣኝ ይችላል። እንዴትና መቼ የሚለውን ግን የሚያውቀው እርሱ ነው።” ስለዚህ፥ “አኹን ባለሁበት ያለሁት (1) በእግዚአብሔር ቀጠሮ፥ (2) በጥበቃው ተከብቤና (3) በእርሱ ሥልጠና ሥር ሲኾን፥ (4) የምቈየውም እርሱ እስከ ወሰነው ጊዜ ድረስ ነው” በሉ። — አንድሪው መሪይ (መጋቢ ሰሎሞን አበበ ገብረ መድኅን እንደተረጎመው)
Show all...
ዘማሪ በረከት ተስፋዬ ሊያዘጋጀው ያቀደወን የመዝሙር ኮንሰርት መሰረዙን አሳወቀ። በማህበራዊ ገጹ ላይ ይህን አስነብቧል:- "የተወደዳችሁ እህቶቼና ወንድሞቼ የአምልኮ ኮንሰርት ለማዘጋጀት እንቅስቃሴዎችን እያረኩ ነበር ነገር ግን የቀጠና ሁለት ሙሉወንጌልን አዳራሽ ስጠይቅ ከቀናቶች ቆይታ በኋላ ዛሬ አለመፈቀዱን ተነግሮኛል። ለመዝሙር ኮንሰርት እንደገና መፈቀዱን ሰምቼ ስለነበር በጣም አዝኛለዉ። ሙሉ ወንጌል ቤቴ ነበር። ለአዳራሽ ይከፈል የነበረዉ ክፍያ 100,000ሺህ ብር ነበር። አሁን ሀገራችን ላይ ካለዉ የኑሮ ዉድነት አንፃር ደህናና በጎ ነበር። ሚሊኒየም አዳራሽ 1.5 million ብር ለአዳራሽ ያስፈልጋል። እንዲሁም ለተለያዩ ወጪዎች እስከ 2,5 million ይፈጃል። እናብ ከዚህ በፊት እንዳረኩት ወንድሞችን አስቸግሬ መኪና ሸጬ ማድረግ አልችልም። በርግጥ በክፍያ ባደርገዉ ከጠቀስኩት ገንዘብ በላይ ማግኘት እችላለዉ። ነገር ግን በቀን አንዴ ለመብላት ለተሳነዉ የሀገሬ ምስኪን ነገሩ ተገቢ ቢሆንም ህሊናዬ አይፈቅድም ስለዚህ የአምልኮ ኮንሰርቱን ትቼዋለዉ ከትልቅ ይቅርታ ጋር። ወደ መደበኛ አገልግሎቴ ሰሞኑን እመለሳለዉ ዘመናቹ ይባረክ። ጌታ ቤተክርስቲያንንና ሀገሬን ይባርክ።" ዘማሪ በረከት "መምህሩ" የተሰኘ የዝማሬ አልበም መልቀቁ ይታወቃል። @MELEKET_TUBE @MELEKET_TUBE
Show all...
​​"ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል!" ብዙ አማኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣው ለመዝናናት ነው። ሌላውም ሰው ጆክ ሲያምረው፣ መሳቅ ሲፈልግ የእኛን ቪዲዮዎች ነው የሚያየው። በኢየሱስ ስም፣ በልሳን፣ በጸሎት ከት ከት ብሎ ይስቃል። እኛም አብረን እንስቃለን። ምንም ስለማይመስለን ቪዲዮውን እየተቀባበልን እንስቃለን። የእግዚአብሔር ስም መቀለጃ ስለሆነ የሚያየው አይፈራው፣ የሚሰማን አይፈራው። እኛም አላከበድነው በሚገባ አላሳየነው፣ አልገለጥነው፣ አላመጣነው...። የአብዛኞቻችን አገልጋዮች ዓላማ ራሱ ሰውን ማዝናናት ነው፤ "ምን ብናገር አዝናናዋለሁ ነው።" የብዙ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን፣ የስብከትና የአገልግሎት ምርጫ "የት ብሄድ ያልተካበደ ነገር እሰማለሁ"፣ "መዝናናት አገኛለሁ" የሚል ነው። ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል። ተዉ እንጂ ብዙም ሩቅ ባልሆኑ ዓመታት፣ የዛሬ ሰልሳ ዓመት ወደ ኃላ "ሪዋይንድ" ብታደርጉ አማኞች የሚፈራ ምገስ ነበራቸው። ሰዎቹ ዛሬም በሕይወት ስላሉ ሄዳችሁ ጠይቋቸው። በቤተ ክርስቲያናቸው ደጃፍ ማለፍ እንኳ ያስፈራ ነበር። ሕይወታቸው ግርማ ነበረው። መልዕክታቸው አስደንጋጭ ነበር። ለማስደንገጥ ብለው ሳይሆን እግዚአብሔር በመካከላቸው ነበር። እዚያ ለመቀለድ አትሄድም፤ ንሰሐ እንጂ ጆክ ትዝ አይልህም። አጋንንት ይወጣል፣ ሰዎች ይፈወሳሉ። የእግዚአብሔር ቃል፣ የክርስቶስ ወንጌል ይሰበካል። ይኼ ሁሉ የሚሆነው ፐርፌክት ፍጹማን ክርስቲያኖች ስለሆኑ አይደለም። ግን የኢየሱስን ስም አስከባሪዎች ነበሩ። አሁን ቢያንስ ስሙ በሆነ መንገድ ይከበር ዘንድ ብንጸልይስ? ቢያስፈልግ ኮሜዲያኖቹን በጊዜ ቢወስደን፤ ይኼም እኮ አንዱ መንገድ ነው። ወይም ደግሞ ጥግ አስይዞን የሆኑ ሌሎች ሰዎች ቢያመጣ፣ እኛ ዕድሉን አልጠቀም ስላልን ሌላን ትውልድ ቢያስነሳልን፣ ስላላየናቸው እንጂ እግዚአብሔር ስሙን የሚያስከብሩለት ልጆች አሉታ!... በዚህ ዘመን ወንጌል የምንሰብክበት ብዙ መድረክ አግኝተን፣ ሚዲያ ተመቻችቶልን አልተጠቀምንበትም። በየሰዉ ቤት የጌታን ስም ተሸክመን ለመግባት እንደዚህ ዘመን ዕድል ተሰጥቶን ያውቃል እንዴ? እኛ ግን ጆካችንን ይዘን ገባንበት፤ እግዚአብሔርን መሳለቂያ አደረግነው። ስለዚህ ወገኖቼ በአሕዛብ መካከል የተነቀፈው ማንነቱ የቀለለው ስሙ መልሶ እንዲከብድ በየትኛውም መንገድ ምክንያት ለመሆን መጸለይ አለብን። ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ @MELEKET_TUBE @MELEKET_TUBE
Show all...
#ተፈፀመ የተወዳጇ ዘማሪት እና አገልጋይ ሂሩት በቀለ የቀብር ስነስርዓት ተፈጸመ። የቀብር ስነስርዓቱ ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድ የጥበብ አፍቃሪያን በተገኙበት ተፈፅሟል። ዘማሪቷ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ በአለማዊ ሙዚቃና በመንፈሳዊ መዝሙሮች አገሯንና ህዝቧን ማገልገሏ በህይወት ታሪኳ ላይ ተገልጿል። ተወዳጇ ዘማሪት የሰባት ልጆች እናት የአስር  ልጆች አያትና የሰባት ልጆች ቅድመ አያት ነበረች። ተወዳጇ ባደረባት ህመም ምክንያት በህክምና ስትረዳ ቆይታ ባሳለፍነው ግንቦት አራት ከዚህ ዓለም ድካም አርፏ ሁለት አስርት አመታት በላይ ወዳገለገለችዉ ጌታ ሠሰብሰቧ ይታወሳል። @MELEKET_TUBE @MELEKET_TUBE
Show all...
———————————————————————————————
Show all...
ዘሪቱ ከበደ ሰው ሁሉ የተፈጠረበትን ክቡር ዐላማ፣ ፈጣሪው ያየለትን ድንቅ ሕይወትና ያንንም ከመኖር ከልክሎት ያለውን ጕድለቱን፣ እንዲሁም ከጕድለቱ ሊያወጣው የሚችለውን ብቸኛ መፍትሔ አውቆ በዚያ ቢጠቀም እጅግ መልካም ነው። ከዚህ አማራጭ ውጭ ያለው በኀጢአት በተገዛ የዓለም ውሸት ውስጥ ለዘላለም መጥፋት ነው። ከሞት ሕይወት እጅግ የተሻለና ሊወዳደር የማይችል ነው። ሕይወትም እራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በኢየሱስ የሆንን እኛ በሕይወት ነን፤ ማንም እርሱን በሕይወትነቱ ቢያውቀው በሕይወት ይኖራል። ሊያውቀው ባይወድድ ግን በሞት ይቀራል፤ መጨረሻውም ለዘላለም ከእግዚአብሔር የመለየት ቅጣት ይሆናል። “ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት አንኳ ሕያው ይሆናል፤ ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ …” (ዮሐንስ 11፥25-26)። #ኢየሱስወይስሞት #ሕይወትኢየሱስነው @meleket_tube
Show all...
ነብይ ተብለክ እንደዚህ አይነት አገልግሎትና መልካም ስም ይዘህ እንዴት ቸርች አልከፈትክም?
Show all...
በልባችን ፅላት የተፃፈ፣ በመንፈሳችን በውስጥ ሰውነታችን የተቀረፀ የማይሰረቀው ታቦታችን የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ... @meleket_tube
Show all...