cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Gehad tube ገሀድ ቲዩብ

Acting is my life 😍 yha channel buzu adis negerochun yemtagegubet new endihumu ye YouTube gesachen ( ekunabe) layየሚሆኑበትና የሚማሩበት ቻናል

Show more
Ethiopia9 876Amharic8 733The category is not specified
Advertising posts
313Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ማንም ማድረግ የማይችለውን ሞትን ድል የነሳ የኛ ጌታ ብቻ ነው:: እነሆ ትንሳኤ እንኳን 🐑ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
Show all...
እውነት እና ፍቅር ተሰቀሉ ተሰቅለው አይቀሩም "ዳግም ይነሳሉ"
Show all...
ለፍጥረት ሁሉ የማይቻለውን ማንም ያላደረገውን መቃብር ፈንቅሎ ሞትን ድል አድርጎ ከሙታን ተነሳ የከፈለው ዋጋ አይቀልብን ዘንድ ይርዳን 🐑መልካም ትንሳኤ
Show all...
🌙🌙🌙 ሰዎች የሚረዳዱበት 💪 መተሳሰብ የሚበዛበት 😇ፍቅር የሚስተዋልበት 😘አንድነት የሚታይበት🤝 ቃላቁ ወር ደረሰ ለመላው 🕌የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ 🌙ረመዳን ፆም በሰላም አደረሳችው መልካም ፆም
Show all...
በእውነት እውነተኛ ታሪክ ነው። ሙሉ ሂጃብ ለብሳ  አረቄ እየጠጣች ነው።አልመረራትም። ከፊትለፊታችን ያሉት ሂጃብ ለብሳ ደሞ አረቄ ምትጠጣ ሴት ማየታቸው አስገርሟቸዋል። መጠቋቆማቸው ስላልጣማት ቤት እንቀይር እንዴ አለችኝ? ባክሽ ዝም በያቸው ጠጪ አልኳት። ትንሽ ፈገግ አለችና "ለዚኮ ነው ካንተ ጋር መሆን ደስ እሚለኝ አለችኝ። አረቄው እስኪገርመኝ ድረስ ስትጠጣው ፊቷ አይቀየርም። የውሃ ያህል ይለሰልሳታል። "ሲጋራ ይዝሀል" አለችኝ በአይኔ ከፊት ለፊቴ " ሲጋራ ማጨስ የተከለከለ ነው"እሚለውን አሳየዋት። ፈገግ ብላ ከአረቄዋ ተጎነጨች። ፈገግታዋ ላይ ነጭ ጥርሷን አየው ጥርሷ ውስጥ እንባ ይተያኛል። ከአይን እማይወርድ እንባ ጥርስ ላይ ይቀር ይሆን ስል አሰብኩ። 8አመት ሳውዲ አለችኝ። ያ መስማት የፈለኩት ታሪክን ልጀምርልኝ ነው መሰል። ይገርማል በፌስቡክ ነዋ ያወኩክ አለችኝ። ምነው ተረሳሽ እንዴ? ድጋሚ ፈገግ አለችና " በእጇ ደብል እንዲደግማት ጠቆመችው። ቀዳላት። "ማባሰድቅ ሆዕም ኩሉን ሸሉም አሌን" የፈረደበትን አረብኛ ቀላቀለችብኝ። እኔ ምን ማለት ነው ትርጉም ብዬ አልጠየኳትም። ያ የኔ ባህሪ አደለም። ባክህ ና ደጅ አስጭሰኝ ብላ ብርጭቆዋን ይዛው ወጣች።ተከተልኳት።ምትቀለቀል ነፍስን መከተል ደሞ ደስ ይለኛል።አብሮ ገደል ለመግባት ።ተያይዞ ለመሞት። በሩ ላይ ቆመን ሲጋራውን ፈልጌ  ለኩሼ ሰጠዋት። አጣጣመችው። ሲጋራው እሚጠጣ ነገር መሰለኝ።በዛ በጨለማ በሲጋራ ጉም የተከለለ አይኗቿን ፈለኳቸው። ወደ ግሮሰሪዋ ሚገቡ ሰዎች ለጉድ ያፈጡባታል እቺን የኦጋዴን ድመት። በአካል ከተገናኘን  4ተኛ ቀናችን ነው። የተለየ ጥያቄዎችን አለማቅረቤ ይበልጥ እኔን ማግኘት እንድትሻ እንዳደረጋት ገብቶኛል። ዛሬ ግን ቁጣ ቁጣ ሲላት ይታየኛል ፊቷ ላይ ትንሽ ብስጭትነት ደግሞ ሰማይ ያህል ሀዘንን አነበብኩ።ነፍሴ ብትጓጓም ለመስማት ቃል ሳልተነፍስ ተመለከትኳት። "ታውቃለህ 8 አመታትን ሳዑዲ ሳሳልፍ ወደ ሀገሬ መመለስ ከብዶኝ ነበር ።ሰዎቼ በግድ ነበር የያዙኝ።ያለኝን ገንዘብ እንኳን ግማሹን ወስደውብኝ ጓደኛዬ ጋር የተወሰነው ሸሽጌው ነበር።ወደ መቶሺ ገደማ፣....... " ለአፍታ ያህል ሲጋራውን ምጋ ወደ ሰማይ እፍፍፍ አለችና ትን እንዳለው ሰው ሳል ተናነቃት። ብላ ብላ እዛ አላህ ወዳለበት ሰማይ ሲጋራውን ማቡነኗ አስገረመኝ ።ይኸው ደሞ ትን አላት።ተቀበልኳት። "5ተኛ አመቴ ላይ ወንድሜ ጎንደር ሄዶ አልተመለሰም ምክንያቱን አላወኩም ነበር" እንባዋ ጉንጮቿን እየሰነጠቀ ይወርዳል።ሲቃ እንደተናነቀቃት ዞር ብላ አየችኝ።እንዳላየ ሆኜ የተቀበልኳትን ሲጋራ መጨረሻዋን ማቡነን ጀመርኩኝ ። "የእናቴ ሞት ግን አስደነገጠኝ።" ድምፅ የሌለው ለቅሶ ህመሙ እዛ አላህ ያለበት ድረስ መድረሱ አይቀሬ ነው። እናት ከሚለው ቃል ቀጥሎ ሞትን ስሰማ ነፍሴ ብርክ እንደያዘው ውስጤ ስትልፈሰፈስ ተሰማኝ ዞር  ብዬ ስመለከታት ነፍሷን በእንባዎቿ ስትሰቃይ ተመለከትኳት። "እናቴ ስትሞት ሀዘኔን ቅጥ አጣብኝ ነፍሴ ተሰቃየች ሁሉም ነገር ጨለመብኝ ታውቃለህ እናቴንኮ ልቀብራት አልቻልኩም።ላኖራት የተሰደድኩላት እናቴን ሳላያት ተለየችኝ።" ድምፇ እፍን ሲል ይሰማኛል። እንባዋን ጠረገችና ከአረቄው ትንሽ ተጎነጨች። "ሂጃብ ለብሼ አረቄ ይደብራላ, አላህ ያረፍ አለችኝ" ፈገግ ብዬ" ሳ አላህም እግዜርም ምንም አይሉሽም ።እንኳን እነሱ እኔም ተረድቼሻለው" "እናቴን ባለመቅበሬ ሀዘኔ በዝቶብኝ ነበር፣ ታውቃለህ ክብሬንኮ ያጣውት በግርድና ምሰራበት ቤት ተደፍሬ ነው። ዞር ብዬ ሳያት በእጆቿ ከንፈሯን እየነካች ኡስስስስ አለችኝ ሳላወራ ወደ አስፋልቱ ዞርኩኝ። እጇቿ የነኳቸው ከናፍርት ግን እጅግ ውብ ነበሩ። ለራሴ ፈገግ አልኩኝ። "ከ8 አመት በዋላ ሀገሬ ስመለስ ወንድሜ ጎንደር ሲሄድ መኪና ተገልብጦ መሞቱና ተቀባይ ስላጣ ብቻ አጥንቱ ተለቅሞ ጎንደር እንደተቀበረ ነገሩኝ። ያ ታናሽ ወንድሜ በደካማ ወገቤ አዝዬው እጫወት የነበረ። ከምበላው ወስጄ እማበላው አንድ ያለኝ ። ያ ታናሽ ወንድሜ ትምህርቱን ይማር ብዬ የተሰደድኩለት።" እንባዋን የገነትን ደጃፍ እሚረግጡት አራቱን አፍላጋት ይመስሉ ነበር።በጉንጬቿ ዙሪያ ቅዱሳን ሁሉ ጥማቸውን ሚቆርጡበት ይመስላሉ። ነፍሷን ከእዮር እስከ እራማ እስከ ኤረር የመልአክትን ምድር በሲቃዋ አዳርሳለች። ሁሉም ሀዘኗና ሲቃዋ ተሰምቷቸው ክንፎቻቸውን አጣጥፈው ሀዘን የተቀመጡ ያህል ተሰማኝ። ታውቃለህ አለች። ( ደሞ በወሬዋ መሀል ታውቃለህ ማለትን ትወዳለች) ታውቃለህ የእናቴ መሞት የወንድሜ መሞትን መስማት ነበር። አረቄዋን ስትጠጣ አልቆባት ነበርና ውስጥ ሄጄ ይዤ መጣው። ተቀበለችኝ ። አላህ ይቅር ይበለኝ አለች። ባይልሽም አታስቢ ተያይዘን ሲኦል እንገባለን አልኳት። ቀና ብላ አየችኝና" ቀውስ "አለችኝ ( አዎ ቀውስ ነኝ።እናንተም እስክታውቁኝ ነው) የእናቴ ቀብር ላይ ተደብቄ ሄድኩኝ።ሴት ልጅ ቀብር አትሄድም እሚለውን ጥሼ። እንባዋ ኩልል ይላል። እማያልቅ እንባ።የዳዊትን የፀፀት እንባን አስታወሰኝ። ህም ቤታችን አክስቴ ሽጣው ነበር። ሲጀመር ቤት ፈልጌ አልነበረም።ግን ለኔ እሚያስብልኝ አንድም ሰው ስላልነበረኝ ሀዘኔ በረታብኝ። ለካ ፀሀይ ወጥታም ይጨልማል። ታውቃለህ ጓደኛዬጋ ስደውል በመጀመሪያ አነሳችልኝና የኔ ስልክ መሆኑን ስታውቅ ዘጋችብኝ።(የፌዝ ሳቅ ሳቀች) ይገርምሀል በዛሁሉ አመት ካፈራውት መቶ ሺ ብር ዱዲ ሳንቲም( ጥፍሯን እያሳየችኝ) እችን ታህል አልተረፈኝም። አረቄውን ጠጣች ዞር ብዬ አየዋት ለካ እንደውሀ የቀለላት አረቄ ውስጧ ያለው ህመም አይሎባት ነው። "ሲምህን እንዳትቀይር እሺ ምናልባት አንድ ቀን እደውልልሀለው "አለችኝና በእጇ ላይ የቀረውን አረቄ ደፋችው። ለምን? አላልኳትም። ያ የኔ ፀባይ አደለም። የራሴን በአንድ ትንፍሻ ወስጄ የ5 ደብል ከፍለኩና የተከራየውላት ሆቴል እንድተኛ መሄድ ጀመርን። ትንሽ ሰክራለች። በመንገድ ላይ ከሌላ እራሷ ጋር እየተነጋገረች ነው መሰል ዝም ብላ  ትራመዳለች። ከዋክብት በሀዘኗ ምክንያት መሬት የተነጠፉ ይመስላሉ ነፍሴ ነፍሷን እየታከከች ሀዘኗን ታሰማኛለች።ሀዘኗ እንደ አርያም እማይመረመር ጥልቅ ይሆንባትና በገዛ እንባዋ ውስጥ ሰጥማ ስትቃይ ይሰማኛል። ዞር ብዬ ሳያት አጋጣሚ ተያየን።ቆመች።ቆምኩኝ። ከንፈሬን ለመሳም ተጠጋችኝ። ዝም አልኳት።  ያ ውብ ከንፈር ከንፈሬን ሲነካው ተሰማኝ። ሰከንድ አይሞላም ነበር።እኔ ግን ሺ አመታት የተቆጠሩ መሰለኝ። ዞር ብላ መንገዷን ቀጠለች።አላወራዋትም። የያዝኩላት ሆቴል ስንደርስ ክፍሏ አስገባዋት። ውስጤን ሀዘኗ ክፉኛ አቁስሎታል  እስከመቼውም አይሽርም። ኪሴ ውስጥ የነበረውን ብር ሁሉ አውጥቼ አልጋው ላይ አስቀመጥኩትና በዝምታ ክፍሉን ለቅቄ ወጣውኝ። የያዝኩት የራሴ ክፍል ውስጥ  ገብቼ ተኛው። እንዴት እንደተኛው አላውቅም። ጠዋት ነፍሴ ቀሰቀሰችኝ እቺ ችኩል ነፍስ። እንደተነሳው ወደ ክፍሏ ሄድኩኝ። እሷ የለችም። ያች ምትሰቃይ ነፍስ የለችም። ምንም ነገር አላልኩኝም። አውቅ ነበር ይህች ነፍስ ጠዋት እንደማትኖር ከጠቀማትም ብዬ ነበር ያለኝን እርዝራዥ የሰጠዋት። ሲምህን እንዳትይር ማለቷ ትደውል ይሆን ብዬ እንድጠብቅ ዛሬም ድረስ አድርጎኛል። ብቻ ደህና ነኝ እንድትል በየመንገዱ ስትንከራተት ዛሬም ድረስ ይሰማኛል። የእንባዋን ዘለላ ሰዎች ሲረግጡት ...... አይኖቼ በየመንገዱ ላይ ይዋልላል ምናልባት ያ ሰዎች እሚረግጡትን እንባ አገኘው ይሆን  ብዬ..
Show all...
😔
🌙🌙🌙 ሰዎች የሚረዳዱበት 💪 መተሳሰብ የሚበዛበት 😇ፍቅር የሚስተዋልበት 😘አንድነት የሚታይበት🤝 ቃላቁ ወር ደረሰ ለመላው 🕌የእስልምና እምነት ተከታዮቾ እንኳን ለ 🟦🌙ረመዳን ፆም በሰላም አደረሳችው
Show all...
🕌
ደስታህን ፍለጋ ሰዎችን አትከተል ምክ ንያቱም እነሱ የሚሄዱት ወደ እራሳቸው ደስታ ነው  አንተም እንግዲህ🤔
Show all...
💪
"ልብስህን  ከቆሻሻ እንደምትጠብቅ ሁሉ ልብህንም ከተንኮል፣ ከክፋት፣ ከትዕቢት፣ ከሃሜት፣ ከቅናት እና ከምቀኝነት ጠብቅ፡፡ የቆሸሸ ልብስ ይቀየራል ፤የቆሸሸ ልብ ግን አንተን ይቀይርሀል፡፡"              💞 #መልካም_ጾም 💞
Show all...
... ስንት ንጉስ ሄደ በዋዛ ፈዛዛ ምኒልክ ብቻ ነው ሞቶም የሚገዛ‼️ "ቢገፉት የማይወድቅ፤ ምኒልክ ተራራ ኖሮም የሚከበር፤ሞቶም የሚፈራ።! ምኒልክ ዛሬም ንጉስ ነው!!!
Show all...
ሆቴል ትገባና ጥብስ ታዛለህ.... ደም ግፊት ምናምን ካለብህ እንደው ምናልባት 'ጨው እንዳይገባበት' ትል ይሆናል! 'ቅባት አይብዛበት' ብትልም አሳማኝ ነው! እንደሁኔታው ሽንኩርት የማይወድም ስለሚኖር 'ሽንኩርት እንዳይገባበት! ብትል ሰዎች ይረዱሃል! 'እስቲ አንድ ጥብስ አምጡልኝ! #ስጋ እንዳይገባበት!' ካልክ ግን ብራዘር ደም ግፊትህን ብቻ ሳይሆን የአእምሮ ጤና ምርመራም እንድታደርግ ነው የምመክርህ!                ✧♡✧ ሚኒልክ የሌለበት አድዋን ሳስብ የመጣልኝ ሃሳብ ነው!             ••✧♡✧•• ክብር በብሔርና በሐይማኖት ሳይከፋፈሉ እነሱ ወድቀው ይቺን ሀገር ላቆሙልን ጀግኖች አባቶቻችን።           ══••✧♡✧••══ @Joel_26g gehad tune
Show all...