cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Grace7Alone!!

በዚህ channel የምናወራው፦" ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ፥ ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራትና ለክርስቶስ አካል ሕንጻ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ።" ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4:12-13 - መዝሙሮች -ግጥሞች for comments @bettyBezabih

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
178Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

God keeps us in His hand John 10:28-29 says: “And I give to them eternal life, and they shall by no means perish forever, and no one shall snatch them out of My hand. My Father…is greater than all, and no one can snatch them out of My Father’s hand.” All kinds of things may try to snatch us from the Father’s hand—sin, the world, difficulties, even Satan himself. But in these verses, the Lord Jesus assures us by saying that it’s impossible for us to be snatched away. No one and nothing is stronger than God. @oncesavedforeversaved
Show all...
✍ ኤሎሄ ~ ሀሌሉያ ************* ያ የተረገመ የተባረከ ቀን ለኛ የነፃነት ለሱ የሰቀቀን ለኛ የደስታ ለሱ የጭንቅ ቀን የፍስሀ የምጥ ሰአት የእርካታ የመጠማት የእስራት የአርነት የህማም ቀን የድህነት ቀን ሊሆነን....... በህመሙ ሊፈውሰን ኃጥያት ሆኖ ሊቀድሰን ወ'ቶ መ'ቶ ከአብ ጉያ ኤሎሄ አለ ሀሌሉያ . . . መቅረባችን መገፋቱ ድህነታችን ግርፋቱ ጥጋባችን ርሀቡ ባርኮታችን መሰደቡ ብርታታችን በመዛሉ መቆማችን በመስቀሉ ሊሆንልን........ በህመሙ ሊፈውሰን ኃጥያት ሆኖ ሊቀድሰን ወ'ቶ መ'ቶ ከአብ ጉያ ኤሎሄ አለ ሀሌሉያ . . . ተረግሞልን ተባረክን ተይዞልን ተለቀቅን ተጠልቶልን ተወደድን ምድር መ'ቶ ሰማይ ሄድን የሱን ነፍጎ ለኛ ቸረ የሱ ቆስሎ የኛ ሻረ በህመሙ ሊፈውሰን ኃጥያት ሆኖ ሊቀድሰን ወ'ቶ መ'ቶ ከአብ ጉያ ኤሎሄ አለ ሀሌሉያ . . . ያዳም ህይወት ተመለሰ የሱን ጥፊ ሞት ቀመሰ በራስ ቅል ላይ በጎልጎታ በትንሳኤው ሞት ተረታ ሲዖል በደም ድል ተነሳ ለሁላችን ህይወት በዛ በህመሙ ተፈወስን በንፁህ ደም ተቀደስን እኛም ገባን በአብ ጉያ ሀሌሉያ-ሀሌሉያ!! 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Show all...
✍ መሀይም ነሽ ለካ ********** አለም ሆይ ወዴት ነው ፣ መርማሪ ጠቢብሽ በእግዚአብሔር ሞኝነት ፣ ተሞኘ ጥበብሽ በጥበብሽ ብዛት ፣ ጌታን ያላወቅሽው የሌለ ሞኝ ነሽ ፣ ለካ እኔን ሞኝ ያልሽው የክብርን ጌታ ፣ አውቀሽውስ ቢሆን አትሰቅይውም ነበር ፣ እንዲህ ጉድ ለመሆን ቸነከርኩት ስትይ ፣ እየቸነከረሽ በደገሺለት ሞት ፣ እሱ እየገደለሽ ገደልኩት የምትይ ፣ መቃብር ሲዘጋ ትንሳዔ 'ማታውቂ ፣ መሀይም ነሽ ለካ ደሞ.......ደሞ ደቀ መዛሙርቱ ፣ ሰርቀውት ነው ብለሽ ውሸት ለማስወራት ፣ ገንዘብ እየከፈልሽ የ'የሱስን ከሞት ፣ መነሳት ስትክጂ ቀልድሽ ሆድ ያሳ'ማል ፣ አንቺ እኮ አትቀልጂ!! ኧረ ደሞ ደሞ መቃብር ጠብቁ ፣ ብለሽም ከፍለሻል አልተነሳም በሉ ፣ ብለሽም ከፍለሻል ተሰርቆ ነው በሉ ፣ ብለሽም ከፍለሻል ለካ የራስሽ ቀልድ ፣ አንቺንም አሞሻል በይ እግዜር ይማርሽ!! @oncesavedforeversaved
Show all...
#2_ተሰሎንቄ_1 3፤ ወንድሞች ሆይ፥ እምነታችሁ እጅግ ስለሚያድግ የሁላችሁም የእያንዳንዳችሁ ፍቅር እርስ በርሳችሁ ስለሚበዛ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን እንደሚገባ ልናመሰግን ግድ አለብን፤ 4፤ ስለዚህ በምትታገሱበት በስደታችሁና በመከራችሁ ሁሉ ከመጽናታችሁና ከእምነታችሁ የተነሣ በእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ስለ እናንተ ራሳችን እንመካለን። 5፤ #ስለ_እርሱ_ደግሞ_መከራ_ለምትቀበሉለት_ለእግዚአብሔር_መንግሥት_የምትበቁ_ሆናችሁ_ትቈጠሩ_ዘንድ_ይህ_የእግዚአብሔር_ቅን_ፍርድ_ምልክት_ነው። 6-7፤ ጌታ ኢየሱስ ከሥልጣኑ መላእክት ጋር ከሰማይ በእሳት ነበልባል ሲገለጥ፥ መከራን ለሚያሳዩአችሁ መከራን፥ መከራንም ለምትቀበሉ ከእኛ ጋር ዕረፍትን ብድራት አድርጎ እንዲመልስ በእግዚአብሔር ፊት በእርግጥ ጽድቅ ነውና። 8፤ እግዚአብሔርን የማያውቁትን፥ ለጌታችንም ለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የማይታዘዙትን ይበቀላል፤ 9-10፤ #በዚያም_ቀን_በቅዱሳኑ #ሊከብር፥ ምስክርነታችንንም አምናችኋልና #በሚያምኑት_ሁሉ_ዘንድ #ሊገረም ሲመጣ፥ ከጌታ ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ። 11-12፤ ስለዚህም ደግሞ እንደ አምላካችን እንደ ጌታም እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም በእናንተ ዘንድ ሊከብር እናንተም በእርሱ ዘንድ ልትከብሩ፥ አምላካችን ለመጥራቱ የምትበቁ አድርጎ ይቈጥራችሁ ዘንድ፥ የበጎነትንም ፈቃድ ሁሉ የእምነትንም ሥራ በኃይል ይፈጽም ዘንድ ስለ እናንተ ሁልጊዜ እንጸልያለን። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Show all...
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍርሃትን አውጥታ በምትጥለው ፍጽምት በሆነች ፍቅር አፈቀረን። በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙም ከታሰርንበት የባርነት ሰንሰለት ፈታን- ይኸውም የሀጢያት ባርነት ነው።ሕማማችንን ተቀበለ፤ ደዌያችንን ተሸከመ። እኛንም ዋጀን። 1 ዮሐንስ 4 18፤ #ፍጹም_ፍቅር_ፍርሃትን_አውጥቶ #ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም። ኤፌሶን 1 7፤ በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ #በደሙ_የተደረገ #ቤዛነታችንን_አገኘን_እርሱም_የበደላችን_ስርየት። ኢሳይያስ 53 4፤ በእውነት #ደዌያችንን_ተቀበለ_ሕመማችንንም_ተሸክሞአል፤ ሃለሉያ🙏🙏🙏🙏 ✝️@oncesavedforeversaved
Show all...
✅Experiencing the blood of Jesus✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 📌Hymn by Watchman Nee📌 ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ Why should I worry, doubt and fear? Has God not caused His Son to bear My sins upon the tree? The debt that Christ for me has paid, Would God another mind have made To claim again from me? Redemption full the Lord has made, And all my debts has fully paid, From law to set me free. I fear not for the wrath of God, For I’ve been sprinkled with His blood, It wholly covers me. For me forgiveness He has gained, And full acquittal was obtained, All debts of sin are paid; God would not have His claim on two, First on His Son, my Surety true, And then upon me laid. So now I have full peace and rest, My Savior Christ hath done the best And set me wholly free; By His all-efficacious blood I ne’er could be condemned by God, For He has died for me!
Show all...
° አሁን የእግዚአብሔር መግባቢያ ቋንቋው ጸጋ ነው!! ° ጸጋው ለሁላችን፥ ለሁሉም ነገራችን በቂ ነው!! ❝እርሱም፦ ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ።❞  —2ኛ ቆሮ 12: 9 እግዚአብሔር የሰጠን #ጸጋ ለሚያስፈልገን ነገር ሁሉ #በቂ እንደሆነ ያምናል!! ጳውሎስ 3 ጊዜ ቢጸልይም የተመለሰለት መልስ አንድ ነው!! "ጸጋዬ ይበቃሃል" የሚል። ጸጋው ብቻውን ከፍ ያደርጋል። አሁን የእግዚአብሔር መግባቢያ ቋንቋው ጸጋ ነው። እርሱም፦ ክርስቶስ ኢየሱስ እና በእርሱ የሆነው!! ክርስቶስ ከበቂ በላይ የሆነ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው። እግዚአብሔር በክርስቶስ ለእኛ የሠራው ሥራ ሁሉንም ያሟላ ነው። እግዚአብሔር የሰዎችን ጉዳይ የፈታው #በክርስቶስ ነው። በጸሎት ብዛት እግዚአብሔርን መልስ አናስቀይረውም!! ጸጋው ለሁላችን፥ ለሁሉም ነገራችን በቂ ነው!! 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 @oncesavedforeversaved
Show all...
✍ የነፍሴ ምኞት ************ ሕይወት ሕይወቴ ነው ፣ መንገድ አድራሻዬ ጥሜን ቆራጭ አለት ፣ ሕያው እንጀራዬ ኢየሱስ እያልኩኝ ፣ ብገጥም ባዜመው አልረካ አልጠማ ፣ አልራብ አልጠግበው አይለቀኝ አይርቀኝ ፣ አይጥል አይተወኝም ከ'ርሱ ውጭ ልሻ ፣ ልመኝ አልመኝም ❤❤❤❤❤ ኢየሱስ ❤❤❤❤❤ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 👉👉Join it👈👈 ✝️ @oncesavedforeversaved ✝️ @oncesavedforeversaved
Show all...
✍ ዘጠና ዘጠኙን በጎች ትቶ አንዷን ፍለጋ የሚሄደው ዘጠና ዘጠኙ በጎች እንደማይጠፉ አውቆ እንጂ አንዷን አግኝቶ ዘጠና ዘጠኙን ለማጥፋት አይደለም!! 📌 በኢየሱስ እረኝነት ተገኝቶ ከመንጋው ጋር የሚቀላቀል በግ እንጂ ከመንጋው ተለይቶ የሚጠፋ በግ የለም!!
Show all...