cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Show more
Advertising posts
1 316 430Subscribers
+1 46524 hours
+8 1677 days
+27 77930 days
Posts Archive
#ጋና #ፀረግብረሰዶም ባለፈው ወር መጨረሻ #የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ጠንካራ ይዘት ያለው " የፀረ-ግብረሰዶም " ረቂቅ ህግ አፅድቋል። ረቂቅ ህጉ በክርስቲያኑ ፣ በሙስሊሙ እና በጋና ባሕላዊ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ያለው ነው። ወደ ተግባር እንዲገባና ህግ ሆኖ እንዲወጣ ግን የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ-አዶን ፊርማ እየጠበቀ ነው። በጋና አሁንም ቢሆን ግብረሰዶማዊነት እስከ 3 ዓመት ድረስ ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። በአዲሱ ረቂቅ ህግ ላይ ቅጣቱ ጠበቅ እንዲል የተደረገ ሲሆን ፦ - በማንኛውም መንገድ ግብረሰዶማውያንና እንቅስቃሴያቸውን ማስተዋወቅ - የግብረሰዶም ስብስብ መፍጠር - ግብረሰዶማውያንን ስፖንሰር ማድረግ - ግብረሰዶማውያንን እና የሚያደርጉትን ማንኛውም እንቅስቃሴ በምንም መልኩ መደገፍ እስከ አምስት (5) ዓመት ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። ምዕራባውያኑና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ ተቋሞቻቸው የጋና ፓርላማ ያፀደቀውን ረቂቅ ህግ ክፉኛ ነው የተቃወሙት። የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እስካሁን ያልፈረሙበት ሲሆን ረቂቅ ህጉን የሚደግፈው ህዝብ " ምነው ዘገዩ ? " የሚሉ ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋና መገናኛ ብዙሃን ላይ ተመልክቷል። የሀገሬው ሰው ፕሬዜዳንቱ #እንዲፈርሙ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርዳታ ሰጪ ምዕራባውን ፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዳይፈርሙበት እያሳሰቡ ናቸው። ጋና ጠንካራ ነው የተባለውን የፀረ-ግብረሰዶም ህግን ወደ ተግባር ምታስገባው ከሆነ በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ ከዓለም ባንክ የምታገኘውን 3.8 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ልታጣ ትችላለች ተብሏል። @tikvahethiopia
Show all...
👏 1
#ጋና #ፀረግብረሰዶም ባለፈው ወር መጨረሻ #የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ጠንካራ ይዘት ያለው " የፀረ-ግብረሰዶም " ረቂቅ ህግ አፅድቋል። ረቂቅ ህጉ በክርስቲያኑ ፣ በሙስሊሙ እና በጋና ባሕላዊ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ያለው ነው። ወደ ተግባር እንዲገባና ህግ ሆኖ እንዲወጣ ግን የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ-አዶን ፊርማ እየጠበቀ ነው። በጋና አሁንም ቢሆን ግብረሰዶማዊነት እስከ 3 ዓመት ድረስ ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። በአዲሱ ረቂቅ ህግ ላይ ቅጣቱ ጠበቅ እንዲል የተደረገ ሲሆን ፦ - በማንኛውም መንገድ ግብረሰዶማውያንና እንቅስቃሴያቸውን ማስተዋወቅ - የግብረሰዶም ስብስብ መፍጠር - ግብረሰዶማውያንን ስፖንሰር ማድረግ - ግብረሰዶማውያንን እና የሚያደርጉትን ማንኛውም እንቅስቃሴ በምንም መልኩ መደገፍ እስከ አምስት (5) ዓመት ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። ምዕራባውያኑና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ ተቋሞቻቸው የጋና ፓርላማ ያፀደቀውን ረቂቅ ህግ ክፉኛ ነው የተቃወሙት። የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እስካሁን ያልፈረሙበት ሲሆን ረቂቅ ህጉን የሚደግፈው ህዝብ " ምነው ዘገዩ ? " የሚሉ ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋና መገናኛ ብዙሃን ላይ ተመልክቷል። የሀገሬው ሰው ፕሬዜዳንቱ #እንዲፈርሙ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርዳታ ሰጪ ምዕራባውን ፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዳይፈርሙበት እያሳሰቡ ናቸው። ጋና ጠንካራ ነው የተባለውን የፀረ-ግብረሰዶም ህግን ወደ ተግባር ምታስገባው ከሆነ በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ ከዓለም ባንክ የምታገኘውን 3.8 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ከፍተኛ ገንዘብ ልታጣ ትችላለች ተብሏል። @tikvahethiopia
Show all...
በሀገራችን አንዳንድ መልካም የስራ ስነምግባር የጎደላቸው ፣ ከአሸከርካሪዎች ጉቦ ካልተቀበሉ ቀኑ መሽቶ የማይነጋ የሚመስላቸው ፣ አንዳንዴም ሆን ብለው ምክንያት ፈልገው የቅጣት ወረቀት ለመፃፍ በኃላም #ጉቦ ለመቀበል የማይፈነቅሉት ድንጋይ የሌላቸው ፣ ፀሀዩ በረታብኝ ፥ ዝናቡም አካፍብኝ ብለው የሚጠለሉ የትራፊክ የፖሊስ አባላት እንዳሉት ሁሉ ፦ - ለስራቸው ታማኝ - ህግን አክባሪ - ቅን አገልጋይ - ፀሀይ ፣ ዝናብ ሳይሉ ህዝብን አክብረው የሚሰሩ በርካታ የትራፊክ ፖሊስ አባላት አሉ። ለእነዚህ አይነት ህዝብን አክብረው ምንም አይነት ሁኔታ ሳይገድባቸው ለሚሰሩ የትራፊክ ፖሊስ አባላት #ምስጋና ይገባል። በሀገራችን ካሉ ከተሞች አንዷ በሆነችው የሰላም ተምሳሌቷ #ድሬዳዋ ❤️ የትራፊክ ፖሊስ አባላቶቿ በተለያየ ጊዜ በመልካም ስነምግባራቸው ስማቸው ተደጋግሞ ይነሳል። ትላንትና በከተማው ከባድ ዘናብ ዘንቦ በነበረበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ እንዳይከሰት አንድ የትራፊክ ፖሊስ አባል በዝናብ ውስጥ ሆኖ ስራውን ሲያከናውን የሚያሳይ የተቀረጹ ቪድዮዎች እና ፎቶዎች ብዙዎች በማህበራዊ ሚዲያ ሲያጋሩት ውለዋል። @tikvahethiopia
Show all...
#አስቸኳይ “ አጋቾቹ ወደ ታች ዘቅዝቀው እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ‘1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን #ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን’ አሉኝ ” - የታጋች እናት በሊቢያ ደላሎች የታገተው የሀዋሳው ተወላጅ ኢትዮጵያዊ ወጣት ጌድዮ ሳሙኤል፣ በአጋቾቹ ልዩ ልዩ ድብደባዎች እየተፈጸሙበት እንደሚገኝ ፣ አጋቾቹ ወጣቱን ለመልቀቅ 1.7 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ፣ ገንዘቡ በፍጥነት ካልገባ “ እንገድለዋለን ” በማለት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሰጡ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። የታጋቹ እናት ወ/ሮ ገነት ጥላሁን ይግለጡ በሰጡት ቃል፣ “ አጋቾቹ ወደ ታች ዘቅዝቀው እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ‘1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን’ አሉኝ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እባካችሁ ልጄን ታደጉኝ ” ሲሉ እያለቀሱ ጠይቀዋል። “ በሄደ በ17 ቀኑ ከሊቢያ ስልክ በጓደኛው አማካኝነት ተደወለልኝ። ስልኩን ሳነሳ ‘ሊቢያ ላይ ተይዟልና 950 ሺሕ ብር ተጠይቋል’ ብሎ ጓደኛው ነገረኝ ” ያሉት የታጋቹ እናት፣ “ ከዚያ ወዲያውኑ ደግሞ ሊቢያዎቹ እየገረፉት ምስል ላኩልኝ። አካውንትም ላኩልኝ ‘ገንዘብ ላኪ’ ብለው ” ሲሉ አስረድተዋል። አክለውም፣ “ እንደገና ለ3ኛ ጊዜ መደኃኒት ሰጥተውት እንደ እብድ እያደረገው ቪዲዮ ላኩልኝ። እንደገና ለ4ኛ ጊዜ ደግሞ ወደ ታች #ዘቅዝቀው #እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ከዚያ ‘ተሽጧል 1.7 ሚሊዮን ብር አምጭ’ ብለው ደወሉ። ቪዲዮ እያሳዩም ‘1.7 ሚሊዮን ብር ታመጫለሽ አታመጭም?’ አሉኝ ” ብለዋል። በዚህም “ እኔ የለኝም ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጉልበቴ ስለሆነ ለምኘ፣ እርዳታ አሰባስቤም እከፍላለሁ አልኳቸው። ለ5ኛ ጊዜ እንደገና #ፀጉሩን ላጭተው የሆነ #ውሻ አስመስለው ምስል ላኩልኝ። ከዚያ በኋላ በቃ ‘የጨመረሻ ቀን ብለው’ ደወሉ። ልጄም በጣም #እያለቀሰ ‘አስለቅቂኝ’ አለኝ። እነርሱም ‘ነገ #አርብ 1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን በፊት ለፊትሽ ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን ” አሉኝ ሲሉ አንብተዋል። አጋቾቹ ‘ብር ላኪ’ ሲሏቸው ባለማወቅ የመፍትሄ መንገድ መስሏቸው የላኩትን አካውንት በሕግ እንዳሳገዱ፣ በዚህም አጋቾቹ የወጣቱን ስቃይ እንዳበዙት፣ ከታገተ ከአንድ ወር በላይ እንደሆነው፣ ገንዘቡ እስኪሟላ ተጨማሪ ቀን መጠየቃቸውን የገለጹት እናት፤ “ ፌደራልም ሊቢያና ሱዳን ድንበር ላይ የሊቢያ መግቢያ ላይ ነው የታገተው ብለው ነገሩኝ ” ብለዋል። ወ/ሮ ገነት፣ ምርመራውን ይዞታል የተባሉ የፌደራል ፓሊስ አባል የአጋቹን አካል ቢደርሱበትም በሕግ በኩልም መፍትሄ እንዳላገኙ አስረድተዋል። ያላቸው አሁናዊ የምርመራ ሂደትን በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው መርማሪው የፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን በጽሞና ከሰሙ በኋላ “ መልስ መሰጠት የሚችለው እንደ ተቋም ስለሆነ በተቋሙ በኩል ኦፊሻል ደብዳቤ ይዘው በአካል መጥተው አመራሮችን ማነጋገር ይችላሉ ” ከማለት ውጪ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም። ሆኖም ስለጉዳዩ በደብዳቤ ጠይቀን ምላሹን በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል። እናት አጋቾቹ ከጠየቁት ውስጥ እስካሁን የተሰበሰበው ወደ 350 ሺሕ ብር ብቻ እንደሆነ አስረድተው “ ሀዘን ላይ ነኝ። በቅርቡ ልጄ ሞቶብኛል። አሁን ደግሞ ይሄ ደረሰልኝ ብዬ፣ አሁን እንደዚህ ሆነብኝ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ረድቶኝ ልጄን እንዲያስለቅቅልኝ በትህትና እጠይቃለሁ ” ሲሉ ተማጽነዋል። ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ የወ/ሮ ገነት ጥላሁን ይግለጡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000523577402 ሲሆን ሌሎችም የሂሳብ ቁጥሮች ከላይ ተያይዟል። በስልክ ልታገኟቸው የምትፈልጉ 0916848184፣ 0911720985 ደውሉላቸው። @tikvahethiopia
Show all...
#Update ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል መልሶ መገናኘት መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል። አብዛኛው የአዲስ አበባ ክፍል እና የተቀሩት የሀገሪቱ ክፍሎች መልሰው ኃይል ማግኘት እንደቻሉ ተገልጿል። የተቀሩትን አካባቢዎች መልሶ ለማገናኘት ጥረቱ መቀጠሉ ተነግሯል። @tikvahwthiopia
Show all...
ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል። በሲስተም ላይ በገጠመ ችግር ኃይል መቋረጡን ያስታወቀው ተቋሙ  ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው ብሏል። የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ መሆኑን የገለጸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፥ ችግሩን በመቅረፍ ዳግም ሲስተሙ ተመልሶ እስኪገናኝ ድረስ በትዕግስት ጠብቁ ሲል አስታውቋል። #NB: ተቋሙ ይህንን መረጃ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ከደቂቃዎች በፊት ያወጣው ሲሆን አሁን ላይ በአንዳንድ አከባቢዎች የተቋረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል መመለሱን ማረጋገጥ ችለናል። @tikvahethiopia
Show all...
#እናት እናት ፓርቲ ፥ " መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አባቶችንና ምእመናንን አሰቃቂ ግድያ በማስቆም ከደሙ ነጻ መሆኑን በአስቸኳይ ሊያረጋግጥ ይገባል " ብሏል። ይህን ያለው ከሰሞነኛው የዶዶላው ግድያ በኃላ ባወጣው መግለጫ ነው። " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ባለፋት ሶስት አስርት ዓመታት እጅግ በጣም አሰቃቂ ጥቃት ደርሶባቸዋል " ያለው ፓርቲው " በተለይም ባለፉት 5 ዓመታት በቤተክርስቲያኗ እና ምእመናኗ ላይ እየተፈጸመ የሚገኘው ግፍ እና አሰቃቂ ግድያዎች ክፉኛ ተጠናክረው ቀጥለዋል " ሲል ገልጿል። ፓርቲው ፥ በዶዶላ ከተማ ባለፈው ሰኞ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ  ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ መርጌታ፣ 2 ልጆቻቸው እና ባለቤታቸውን ጨምሮ ከ2 ወራት በፊት ሥርዓተ ጋብቻቸውን የፈጸሙ ሙሽሮች (አንድ ዲያቆን ከባለቤቱ እና ታላቅ እህቱ ጋር) በአጠቃላይ 7 ንጹሐን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ካህናትና ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ በታጣቂዎች መገደላቸውን አመልክቷል። በተጨማሪም በቀን ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ 4 ንጹሐን ዜጎችም በታጣቂ ኃይሎች መገደላቸውን ገልጿል። ሌሎች ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 7 ሰዎችም በዶዶላ አጠቃላይ ሆስፒታል ሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ጠቁሟል። ፓርቲው ፤ " ከዚህ ማብቂያ ካጣው አሰቃቂ ግድያ ጋር በተያያዘ መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አባቶችና ምእመናንን አሰቃቂ ግድያ በማስቆምና መንግሥታዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ከእነዚህ ንጹሐን ደም  ነጻ መሆኑን በአስቸኳይ ሊያረጋግጥ ይገባል " ብሏል። @tikvahethiopia
Show all...
" 11 ንፁሃን ነው የተገደሉት " - የዶዶላ ከተማ አስተዳደር በዶዶላ ባለፈው ሰኞ ዕለት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በተፈፀመ ጥቃት 11 ንፁሃን ሰዎች መገደላቸውን የከተማው አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል አረጋግጧል። የከተማው አስተዳደር ለሬድው ጣቢያው " በዕለቱ በድንገት በተፈፀመ ጥቃት 11 ሰዎች ሞተዋል። በጥይት ተመተው የተጎዱም አሉ። ከጥቃቱ ጀርባ በገደብ አሳሳ ፣ አዳባ፣ በክልል ደረጃም ታጥቆ የሚንቀሳቀሰው የሸኔ ቡድን አለ የሚል መላምት አለ ግን ምርመራ እየተካሄደ ነው " ብሏል። ይህ ሁሉ ሰው #ሲገደል የፀጥታ ኃይሉ ለምን በስፍራው አልደረሰም ? ለሚለው ጥያቄ የከተማ አስተዳደሩ ፤ " ጥቃቱ የተፈፀመው በደነባ ክ/ከተማ ደብረ ቅዱሳን ጻድቁ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ነው። ይህ ሆን ብሎ የሃይማኖት አባትን እና ልጆቻቸውን የገደለው እርስ በእርስ ግጭት እንዲነሳ ለማድረግ ነው ብለን እንገምታለን። በጣም ታስቦበት የተፈፀመ ግድያ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥቷል። ንፁሃኑ ግድያው የተፈፀመባቸው በቤታቸው እያሉ #በጥይት ተተኩሶባቸው እንደሆነና መንግሥት ግድያውን እንደሚያወግዝ የከተማ አስተዳደሩ ገልጿል። ለመሆኑ የጥቃቱ ፈፃሚዎች ተይዘዋል ? ለሚለው ጥያቄ ፥ የዶዶላ ከተማ አስተዳደር " ክትትል እየተደረገ ነው " የሚል ምላሽ ለሬድዮ ጣቢያው ሰጥቷል። ይህ የአስተዳደሩ ምላሽም አንድም የተያዘ ሰው እንደሌለ የሚጠቁም ነው። በዶዶላ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ 2 የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪና የዓይን እማኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል። ነዋሪው ፤ አንድ መሪጌታ ከእነባለቤቱ እና ከሁለቱ ልጆቹ ጋ፣ አንድ ዲያቆን ከእነባለቤቱና እህቱ ጋር መገደላቸውን ፤ የመርጌታው ሁለቱ ልጆቹ ሲገደሉ የ1 ዓመት ከ5 ወር ህፃን ብቻ መቅረቱን ገልጸው ነበር። @tikvahethiopia
Show all...
ኮንሰርት፣ ባዛር ሲያዘጋጁ ፊልም/ቲያትር ሲያቀርቡ የሚታይ የሚጎበኝ ሲኖርዎት የመግቢያውን ትኬት እኛ እንሽጥልዎት! https://www.facebook.com/combanketh https://t.me/combankethofficial ********** በሲቢኢ ብር መተግበሪያ የትኬት ሽያጭ አገልግሎት በቀላሉ ሚሊዮኖች ጋር ይደርሳሉ! #CBE #cbebirr #apps #digitalbanking ************* የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ማስፈንጠሪያ፡ • ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr • ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
Show all...
2
🔥ደማቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወደ ሜዳ ሊመለስ ነው🔥 አንድ ቡድን መርተው ቢያውቁም ፔፕ ጋርዲዮላ እና ሚካኤል አርቴታ ባላንጣ ሆነው ሊሰለፉ ግድ ሆኗል 🏆አስተማሪው ከ ተማሪው ጋርለዓመቱ የመጨረሻ ጊዜ ይገናኛሉ! 🎉ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ! 🎉ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ደንበኝነትዎን ሲያሳድጉ... እኛም ቀጣዩን ፓኬጅ ለአንድ ወር እንጋብዝዎታለን! የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ! https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2 #PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET #StepUp
Show all...
#እንድታውቁት አዲስ አበባ ከተማ ከ4 ኪሎ እስከ ፒያሳ ባለው መስመር የራስ መኮንን ድልድይ እየተሰራ በመሆኑ የመንገድ ግንባታው እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ፍጹም መቆም የሚከለክሉ የትራፊክ ምልክቶች ተተክለዋል። በስራ መግቢያ እና ከስራ መውጪያ ሰዓትም በአካባቢው ላይ በመንገድ መዘጋጋት ህብረተሰቡ እንዳይጉላላ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ተብሏል። በዚሁ መሰረት ፤ " ፍጹም መቆም የሚከለክሉ " ምልክት የተተከለባቸው ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ መታሰቢያ የሚወስድ ዋና መንገድ እና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች፣ አድዋ ሙዚዬም ዙሪያ እና ማዘጋጃ ዙሪያ ከዛሬ መጋቢት 19/2016 ጀምሮ ጥብቅ ቁጥጥር ይጀመራል ተብሏል። በአካባቢው በግዜያዊነት ለተሽከርካሪ ማቆሚያ አገልግሎት የሚውል የአድዋ ሙዚዬም "ሰርፌስ ፓርኪንግ" አገልግሎት መስጠት ስለጀመረ አሽከርካሪዎች እንደ አማራጭ መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል። በመንገድ ግንባታ ስራ ፦ - ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ - ከአራት ኪሎ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ፣ አማራጭ መንገድ ከአራት ኪሎ-አባድር  - ከደጎል አደባባይ ትራፊክ መብራት ወደ 4 ኪሎ - ከቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ራስ መኮንን ድልድይ - ከደጃች ውቤ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ - ከአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ - ከባሻወልዴ ችሎት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ - ከቀበና ወደ ፒያሳ የሚመጡ አሽከርካሪዎች መንገዱ ግንባታ ላይ መሆኑን ተገንዘበው ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል። በአካባቢው ያለውን የትራፊክ ፍሰት መጨናነቅ ለመቅረፍ ፤ አማራጭ #ማስተንፈሻ የሚሆን መንገድ በተለምዶ ከቀይባሕር ኮንደሚንየም ወደ ደጎል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ዛሬ ከሰዓት ለተሽከርካሪዎች ክፍት ይሆናል ተብሏል። መረጃው የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ነው። @tikvahethiopia
Show all...
" ... ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣ እንመክራለን " - የአማራ ክልላዊ መንግሥት የአማራ ክልል መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፤ " የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ " ሲል #አስጠነቀቀ። የክልሉ መንግሥት ፥ በአሁን ሰዓት የወልቃይት  ጠገዴ ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ህዝብ ለረጅም ዓመታት በ " ህወሓት " በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረው የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተመለሰበት እንደሆነ ጠቁሟል። ህዝቡም እንደማንኛውም የሀገሪቱ ሕዝብ ሁሉ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነት መብቱ ሊቀለበስ የማይችል ነው ብሏል። " የፕሪቶሪያው የሠላም #ስምምነት ከመፈረሙ በፊት ጀምሮ የአማራ ክልል እንደሌሎቹ ዞኖችና የልማት ትሩፋቶች ሁሉ የአካባቢው ሕዝብም #በትምህርቱም_መስክ ተጠቃሚ እንዲሆን አድርጓል " ሲል ገልጿል። ክልሉ ፤ እንደሌሎቹ አካባቢዎች የነዚህ አካባቢ ህፃናትም የመማር መብታቸው እንዲከበር ግዴታውን መወጣቱን ገልጿል። የትምህርት ስርዓቱን ሰበብ በማድረግ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ እንዳወጣ ጠቁሟል። ይህም " ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም " ሲል ተችቷል። የአማራ ክልል መንግሥት ፥ " ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሀገራችንን እና ሁለቱን ክልሎች ወደ #ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት በመቆጠብ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር  እንዲሁም አንድ ሀገር ለመገንባት ለሚፈለገው ዘላቂ ሠላምና ለሕዝቦች አንድነት መጽናት በሚበጅ ሐሳብና ተግባር ላይ እንዲያተኩር እንመክራለን " ብሏል። ሙሉ መግለጫ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/86444 @tikvahethiopia
Show all...
#Update የአማራ ክልል ይፋዊ ምላሽ ሰጠ። * " የዛቻና የጠብ አጫሪነት የሆነውን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መግለጫ ተመልክተነዋል " - የአማራ ክልል የአማራ ክልል መንግሥት ዛሬ ሀሙስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ ፤ " የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም የአማራ ክልል ተማሪዎች መማሪያ መጻህፍትን እንደሰበብ ተመርኩዞ ያወጣውን የዛቻ እና የጠብ አጫሪነት መግለጫ ተመልክተናል " ብሏል። የጊዚያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የትምህርት ስርዓትን በማጣቀስ " የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል " ሲል ያወጣው መግለጫ በተሳሳተ ካርታ ወደ አማራ ክልል ተካተዋል ያላቸውን አካባቢ ሕዝቦች ታሪካዊ እውነታን፣ ተጨባጭ ማስረጃዎችን እና ነባራዊ ሐቅን የካደ፣ አሳሳችና  የጠብ አጫሪነት ፍላጎትን የተሸከመ መግለጫ ነው ሲል ገልጿል። #በትናንትናው እለት ደግሞ ከነበረበት አካባቢ በመንቀሳቀስ የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደልና በማሰቃየት ላይ ይገኛል ሲል የአማራ ክልል ከሷል። (ሙሉው መግለጫ ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
Show all...
" እየመጣችሁ ላላስፈላጊ እንግልት እንዳትዳረጉ " - የቤቶች ልማት እና አስተዳደር የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ለጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝግበው እየጠበቁ ያሉ ነዋሪዎች ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ በተለይ #በቲክቶክ እየተለቀቀ ባለ የተሳሳተ መረጃ ምክንያት ወደ ቢሮ መጥተው እንዳይንገላቱ ጥሪ አቀረበ። ቢሮው ፥ " ' የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝግባችሁ እየተጠባበቃችሁ ያላችሁ ብቁ መሆን አለመሆናችሁን ባምቢስ በሚገኘው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ 5ኛ ፎቅ መታችሁ እንድታዩ ' በሚል የተለቀቀው መረጃ የተሳሳተ ነው " ብሏል። ተመዝግበው እየተጠባበቁ የምትገኙ ነዋሪዎችም ላተፈለገ እንግልት እንዳይዳረጉ ጥሪ አቅርቧል። " ተመዝጋቢዎችም ሆነ ሌሎች ነዋሪዎች የተቋሙ ባልሆኑ ማህበራዊ ሚዲያዎችም ሆነ ግለሰቦች በሚያናፍሱት ወሬ እንዳትታለሉ " ብሏል። @tikvahethiopia
Show all...
#SamiTech አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!! @samcomptech በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን። የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114 https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
Show all...
#ሴጅ_ማሰልጠኛ የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 21 2016 ዓ.ም 7ኛ ዙር የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ (Computer Programming) ስልጠና ይጀምራል። 👉 100 % በተግባር የተደገፈ ስልጠና 👉 መሠረታዊ የኮምፒውተር ትምህርትን አካቶ የሚሰጥ 👉 C++, Java እና Python ፕሮግራሞች ከፍ ባለ ደረጃ (Advanced Level) በጋራ የሚሰጡበት ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute
Show all...
2🤔 1
" ቲክቶክ እንዲታገድ ለካቢኔው ጥያቄ አቅርቢያለሁ " - የኢራቅ ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር የኢራቅ የኮሙኒኬሽን ሚኒስትር ሂያም አል-ያስሪ ' ቲክቶክ ' የተሰኘው የአጫጭር ቪድዮ ማጋሪያ መተግበሪያ እንዲታገድ ለሀገሪቱ ካቢኔ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተናገሩ። " የኢራቅን የማህበራዊ ህይወት ትስስር እየሸረሸረው ነው " ያሉት ሚኒስትሯ የእግድ ጥያቄውን በቅርቡ ካቢኔው እንደሚያየውና እንደሚነጋገርበት ገልጸዋል። " መተግበሪያው ማህበረሰቡን የሚጠቅም የረባ ትምህርታዊ ጠቀሜታ የለውም ሙሉ በሙሉ መዝናኛ ላይ ያተኮረ ከምንም በላይ የኢራቅን ህዝብ ባህል፣ እሴት አጠቃላይ ትስስርን የሚሸረሽሩ ይዘቶች የሚሰራጩበት ነው " ብለዋል። የኢራቅ ፓርላማ እንዲህ ያለው መተግበሪያ እንዲታገድ ድጋፍና ትብብር ማድረግ እንዳለበት ጠቁመዋል። @tikvahethiopia
Show all...
#Update ከፍተኛ የሆነ የተኩስ ልውውጦችን ሲያስተናግዱ በቆዩት በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ እና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች ውስጥ ካለፉት 3 ቀናት ወዲህ አንጻራዊ የሚባል #ሰላም መኖሩን የአካባቢውን ነዋሪዎች ዋቢ በማድረግ ቪኦኤ ዘግቧል። በሰሜን ሸዋ ዞን ፤ የአጣዬ ከተማ አስተያየት ሰጭዎች ፣ በአካባቢው አንጻራዊ ሰላም መኖሩን አመልክተዋል። ለደኅንነታቸው ሲሉ ወደ አጎራባች ቀበሌዎች የተፈናቀሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ግን በአሳሳቢ ችግር ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡ በተመሳሳይ፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ አንጻራዊ ሰላም መኖሩን ነዋሪዎች ጠቁመዋል። አልፎ አልፎ ግን የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማ አመልክተዋል፡፡ አንድ የሰንበቴ ከተማ ነዋሪ ፥ " መንገድ ዝግ ነው መንቀሳቀስ አልቻልንም። የጅሌ ጥሙጋና የአርጡማ ፋርሲ ወረዳዎች ተቆራርጠናል። ተረጋግቷል የሚባለው በሁለቱም ወረዳዎች መንግሥት ሰላም አስፍኖ መንገዶች ሲከፈቱ ነው። አሁን መንገድ አልተከፈተም ሰውም ችግር ውስጥ ነው " ብለዋል። ነዋሪዎች ዘላቂ የሆነ ሰላም እንዲመጣ የፌደራል መንግሥቱ መፍትሔ እንዲያፈላልግ ነዋሪዎቹ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ጥሪ አቅርበዋል። ሰሞኑን በነበረው የተኩስ ልውውጥ የሰው ህይወት ጠፍቷል፣ የአካል ጉዳት ደርሷል፣ ንብረት ወድሟል። @tikvahethiopia
Show all...
#Update #ራያ ° “ ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር ° “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል ” - የተጎጂ ቤተሰብ በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ተቀሰቀሰ የተባለውን ተኩስ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ሆነው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የአካባቢ ከፍተኛ አመራር ከትላንት ወዲህ ያለውን ሁኔታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል። እኚሁ አመራር ፤ “ ዛሬ አፍሪካ ህብረት መጥተው ማን ስምምነቱ እንደጣሰ ተመልክተዋል። አፍሪካ ህብረት እያንዳንዱን ችግር አይተውታል ” ብለዋል። “ ዛሬ ተኩስ የለም። የያዙት ቦታ አሁንም አለቀቁም። ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል። መከላከያ ያለውን እውነታ አስረድቷቸዋል ” ሲሉ አክለዋል። “ የሞተውን ዛሬ በክብር ቀብረነዋል። ማቹ ተፈራ ፍቃዱ ይባላል። የሁልግዜ ለምለም ቀበሌ ነዋሪ ነው። ቀብሩም ከቀኑ 7፡00 በጎልአጆ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል። ሪፈር የተላኩ አልተመለሱም ” ሲሉ ተናግረዋል። በተኩሱ ጉዳት ደርሶባቸው ሪፈር ተጽፎላቸዋል ከተባሉት ሁለት ቁስለኞች መካከል የአንዱ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል። በአላማጣ አዋሳኝ በኩል ድንበር ላይ ቆሞ እያለ ነው በእነርሱ (በህወሓት) በኩል ጥቃት የደሰበት” ብለዋል። “ በጣም ከፍተኛ ጉዳት አለው ሁለቱም እጆቹ ከኋላውም ቀላል ጉዳት ደርሷል። ግን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሁለቱ እጆቹ ላይ ነው። ወደ ደሴ ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎለት እንደገና ደሙ አልቆም ሲል ወልዲያ ሆስፒታል ከትላንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ (መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ/ም) 7፡00 ገብቶ ነበር። ከዚያ በኋላም ወደ ግል ክሊኒክ ገብቷል። ሁለቱም እጆቹ ላይ ስለሆነ በጣም ስቃይ አለው ” ሲሉ አክለዋል። " በድንበራችን ላይ መጥተው ነው ጥቃህት ያደረሱት" ብለው፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትከረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የትግራይ እና የአማራ ክልል አዋሣኝ ቦታ የሚገኙ የስራ ኃላፊዎች በራያ በተፈጠረው ጉዳይ እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ይገኛሉ። በትግራይ ክልል በኩል ያሉ አመራሮች ሰሞነኛውን ተኩስ የከፈቱት የአማራ ክልል ታጣቂዎች እንደሆኑ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። " ግጭቱም ሆን ተብሎ  ፦ - የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ለማደናቀፍ - የትግራይ ማህበረሰብ ተወካዮች ከጠቅላይ ሚንስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ያደረጉት ውይይትና የአማራ እና የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንቶች በፕሪቶሪያ ውል አተገባበር ዙሪያ የፈጠሩት መድረክን ተከትሎ 'ውሉ ተግባራዊ ይሆናል' የሚል ስጋት ስለፈጠረባቸው ነው " ብለዋል። " አሁንም የአማራ ክልል ታጣቂዎች ለቀጣይ ትንኮሳ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ደርሰንበታል " ብለዋል። የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ውል እንዲከበርና የአማራ ክልል ታጣቂዎች በኃይል ከያዟቸው የትግራይ አካባቢዎች እንዲወጡ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። እስካሁን ድረስ በሁለቱም በኩል በክልል ደረጃ ስለ ጉዳዩ ያወጡት መግለጫ የለም። የፌዴራል መንግሥትም ያለው ነገር የለም። መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ ነው። @tikvahethiopia
Show all...
ፎቶ ፦ በኢትዮጵያ ታላቁ የጎዳና ላይ #ኢፍጧር ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት ተከናውኗል። Photo Credit : Abel Gashaw #ኢፍጧር #ረመዷን @tikvahethiopia
Show all...
217😡 94🥰 20😭 17🕊 12🙏 6👏 5😢 2
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!