cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot

Show more
Advertising posts
29 918Subscribers
-1124 hours
+337 days
+66630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

"እግዚአብሔር ያጽናናሽ" እግዚአብሔር ያጽናናሽ                  ዕንባሽን ያብሰው፣ ቤተክርስቲያን ሆይ                  እስከመጨረሻው፣ ካህንሽ በመቅደስ           ከበጎቹ ጋራ ስለታረደብሽ፣ እንደ ራሔል ዕንባ                  እግዚአብሔር ያስብሽ። ስለ ጌታ ፍቅር ማህቧተን ይዛ                       አክሊል ተቀዳጀች፣ በደሙ ከዋጃት ከክርስቶስ ጋራ                        እኖራለሁ አለች፣ የእምነት ሰማዕትነት ሲመጣ በገሃ፣ ይሻሙ ነበረ ከእሳቱ ለመንደድ።         አዝ= = = = = በዚህ በእኛ ዘመን ቅዱሳን ተሻሙ፣ አክሊሉን ለመውሰድ ከሁሉ ሊቀድሙ፣ የተክለሃይማኖት የክርስቶስ ሠምራ ሕፃናት ተነሱ፣ በመሞት ህይወትን ከእግዚአብሔር ሊወርሱ፣         አዝ= = = = = አሕዛብ አትድከም በመግደል አትጸድቅም፣ ነፍሰ ገዳይነት አሸንፎ አያውቅም፣ በበቀል ጭካኔ የሰው ልጅን ማረድ፣ እጅግ የወጣ ነው ከሃይማኖት መንገድ።         አዝ= = = = = ይቺ ቤተክርስቲያን የተገነባችው                              በደም ስለሆነ፣ በሞት ሕይወት ሊያገኝ                           ክርስቲያን ታመነ፣ ምድሪቱ ለእግዚአብሔር የተቀደሰች ናት፣ ሕዝቧም ሊወድቅ ቀርቧል እንደበግ መስዋዕት።                     በሊቀመዘምራን ይልማ ኃይሉ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
👍 21😢 5 2
ሚያዝያ ፲፩ ዝክረ ሰማዕታተ ሊብያ ዘጠነኛ ዓመት አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
20😢 4👍 3
ክዕወተ በርዕ ሥር እየሰደደ ሲሄድ ባለበት አይወሰንም፡፡ «አንደኛውኑ ዝሙት ይሻላል›› በማሰኘት ወደ ዝሙትና ግብረ ሰዶም ሊያመራ ይችላል፡፡ ገለልተኝነት፣ ብቸኝነትን መሻትና የሥራ ተነሣሽነትን ማጣት ደግሞ ሌላው የዚህ ክፉ ልማድ ጐጂ ገጽታ ነው። የመሰንጋት ሌላው አደገኛና ጐጂ ገጽታው ደግሞ ተስፋ መቁረጥና አጉል ጸጸት እንዲሁም ከንቱ ትሕትናን ማሳደሩ ነው፡፡ አጉል ጸጸቱ እንደ ይሁዳ ዓይነት ጸጸት በመሆኑ ኀፍረተ አካልን ተናዶ እስከ መቁረጥ ለ.ያደርስ ይችላል:: ይሁዳ ራሱን እስከ መግደል የደረሰው በአጉል ጸጸት ነውና፡፡ የሐዋ 1፥16-20፤ ማቴ 27፥3-5   አጉል ትሕትና ማለት ደግሞ በዚህ ክፉ ልማድ የተመረዙ ሰዎች ዘማርያን፣ ሰባክያን፣ መነኮሳትና በልዩ ልዩ አገልግሎትና መንፈሳዊ ሙያ የተሰማሩ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ:: መንፈሳዊ አገልግሎት ንጽሕናን የሚፈልግ በመሆኑ ኑሮአቸውና መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ሳይጣጣም ሲቀር «ማገልግል አይገባኝም!» በማለት ከትሩፋትና ከበጐ ሥራ ራሳቸውን የሚያሸሹ አሉ:: ነገር ግን ክፉ ሥራን እንጂ የትሩፋት ሥራን መሸሽ በምንም መልኩ አይበጅም፡፡ ከአገልግሎት ጋር ሆነን ያላራቅነውን ክፉ ሥራ ከረድኤተ እግዚአብሔር ተለይተን ልናርቀው አንችልም፡፡ ውሣኔያችንን አየመረመርን ከበላዮቻችን ማለትም ከመንፈሳዊ አባቶች ጋር እየመከርን በምክረ ካህን በፈቃደ ካህን መኖርን መፍትሔ እናድርግ፡፡ ይኸውም ለጊዜው ነው እንጂ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ከዚህ ልማድ መለየት ብቻ ነው፡፡   በጋብቻ ሕይወት ውስጥ አንዱ ለሌላው ወገን ደስታና እርካታ ማሰቡ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የጋብቻ ግንኙነቶች ይበላሻሉ:: በጋብቻ መሃል ጭንቀትና ቅሬታም ይፈጠራል፡፡ ወጣቶች ከጋብቻ በፊት ያዘወትሩት የነበረው የፆታ ብልትን በመነካካትና በማሻሸት ለመርካት የመሞከር ተግባር ወይም ሴጋ ስለ ራስ ደስታና እርካታ ብቻ የማሰብ ልምድን ያሳድግባቸዋል:: ይህ ልምድ ደግሞ በጋብቻ ውስጥ የሚገኘውን ደስታ አደጋ ላይ ይጥለዋል፡፡ ምክንያቱም ስለራስ እርካታ ብቻ በማሰብ በባልና በሚስት መሃል መተሳሰብ እንዲጠፋ ስለሚያደርግ ነው፡፡ ይህ ችግር ትክክለኛውን መፍትሔ አያግኙለት እንጂ በዓለማዊያኑ ዘንድ በስፋት ለውይይት ይቀርባል፡፡ በመንፈሳዊያን ሰዎች ዘንድ ደግሞ ምንም በሰፊው ባይወያዩበት በጋብቻ ውስጥ ለሚፈጠሩ የግጭት መነሻዎች ዋነኛ ሲሆን የሚመነጨውም ከትዳር በፊት ይዘወተር ከነበረ ክዕወተ ዘርዕ (ሴጋ) አማካኝነት ነው፡፡ አንተ ወጣት ይህ ክፉ ልማድ እስከ ጋብቻ ዘልቆ እንዴት ሊጐዳ እንደሚችል ተረዳህን? ከ«ግብረ አውናን» እንዴት መላቀቅ ይቻላል? ሀ. ግብረ አውናን እንደ ማር ጠብታ ነው:: የማር ጠብታ ልብስ ላይ የወደቀ እንደ ሆነ በፍጹም የሚለቅ አይመስልም፤ ነገር ግን ትንሽ ለቅለቅ ያደረጉት እንደሆነ ወዲያውኑ ይለቃል:: ይህ ክፉ ልማድም እንደ ማር በቀላሉ ባይሆንም ከልብ በመጸጸት በጠንካራ መንፈስ ከተነሡ ሊያስወግዱት ይቻላል:: ተስፋ መቁረጥ ከሁሉ ይከፋልና በመጀመሪያ የሚያስፈልገው ሊወገድ የማይችል አድርጐ በመቁጠር ተስፋ አለመቁረጥ ነው:: ለ. መሰንጋት ልማድ ነው፡፡ ልማድ ደግሞ በልማድ ይሸነፋል፡፡ ጠንክረህ ከተነሣህ ይህን ተግባር በትዝታ ብቻ የምታስብበት ቀን ሩቅ አይሆንም:: ነገር ግን ከዚህ ልማድ ጋር ለመዋጋት ከመነሣትህ በፊት «ይህን ክፉ ልማድ ምን ያህል ከልቤ ጠልቼዋለሁ?» በማለት ራስህን ጠይቅ፡፡ መላልሰህ የምትሰናከለው ሳትጸጸት ቀርተህ ሳይሆን ጣዕሙ በልቡናህ ስላለና ጐጂነቱ ዘልቆ ወደ ልብህ ስላልገባ ነው:: ስለዚህ መፍትሔው በመጀመሪያ ጎጂነቱን አምነህ ይህን ኃጢአት መጥላት መጀመርህ ነው፡፡ ይህ ካልሆነና የዚህን ኃጢአት ጣዕም ከልብህ ሳታወጣ ልታርቀው ብትታገል የአምላክህን ረድኤት አታገኝም። እግዚአብሔር ከኃጢአት ከመለየታችን በፊት መራራነቷን ከልብ እንድናምን ይፈልጋልና፡፡ የኃጢአት ጣዕም ከልብ ካልወጣ ለጊዜው ከኃጢአት በልዩ ልዩ ምክንያት ብንለይ እንኳን ተመልሰን አንድ መሆናችን አይቀርም፡፡ ሐ. ይህን ክፉ ልማድ እንደ እሳት የሚያያይዙት የራስህ ተግባርና በዙሪያህ ያሉ ነገሮች ናቸው:: ከዚህ እኩይ ልማድ ለመላቀቀቅ ከፈለግህ «ተዐቅቦ›› ያስፈልግሃል፡፡ «ተዐቅቦ›› ማለት መከልከል መቆጠብ ማለት ነው፡፡ የምትከለክለውም ወደዚህ መጥፎ ሐሳብ ልቡናህን የሚስቡትን ነገሮች ከማየት፣ ከመስማት፣ ከመንካትና ከመሳሰሉት ነው:: ስለዚህ የሴቶችን ገላ በፊልምም፣ በአካልም ቢሆን በምንም መልኩ ከማየት ተቆጠብ። በመዋኛና በመጠመቂያ ቦታዎች ራስህን ጠብቅ የሴት ልጅን መልክና ቅርፅ መርዘህና አተኩረህ አትመልከት፡፡ ስለ ዝሙት የሚያሳስቡ ስዕሎችን፣ ጽሑፎችንና ወሬዎችን አጥብቀህ ሽሻቸው፡፡ ሥራህ ሁሉ አንተው እያራገብክ ለምን ይቃጠላል? ብሎ እንደ መጠየቅ እንዳይሆንብህ ተጠንቀቅ:: መ. ዘወትር ልቡናህ የሚጠመድበትን ነገር ፈልገህ አድርግ፡፡ ቦዘኔ አትሁን፤ ትጉህ ሠራተኛ ሁን:: ሥራህም በእንቅሳቃሴ የተሞላ ወይም አእምሮን ያለ ዕረፍት የሚያሠራ ይሁን። ነጋዴ ብትሆንና ገበያ ሲመጣ ሽጠህ ብትቀመጥ ከዚያ በኋላ ግን ቁጭ ብለህ ብትውል በሥራ ቦታ በመዋልህ ብቻ አእምሮህ እስካልተያዘ ድረስ በመንፈሳዊ ጎዳና ከተመለከትከው እየሠራኽ ነው አይባልም፡፡ በትርፍ ሰዓትህ የሚነበብ ወይም ሌላ የሚሠራ ሥራ ፈጥረህ ሥራ:: የዝሙት ማራገቢያው የአእምሮ ቦዘኔነት ነውና፡፡ ሠ. «ሁለት ሁለት አድርጐ ላካቸው» የሚለውን የወንጌል ቃል አስብ፡፡ በዚህ ክፉ ልማድ ተጠምደህ ሳለ ለብቻህ መሆንን አትወደድ፡፡ ቢቻልህ አኗኗርህና መኝታህ ከምታፍረውና ከምታከብረው ሰው ጋር ይሁን፡፡ ይህም ጓደኛህ ወይም ከቤተሰቦችህ አንዱ ሊሆን ይችላል:: ከብቸኝነት ይልቅ መወያየትን ይልቁንም መንፈሳዊ ውይይትን ዘወትር አድርግ፡፡ በጸሎት ከሚረዱህ መንፈሳዊያን መምህራንና አባቶች ጋር ጊዜ ማሳለፍን ውደድ፡፡ ከእነርሱ ጋር በመወያየትህ በጸሎታቸው እንዳይረሱህ ከማድረግ ጋር ለነፍስህ ወደብ የሚሆኑ ብዙ መንፈሳዊ ነገሮችን ትማራለህና፡፡ ረ. እንቅልፍ የያዘህ ስለ መሰለህ ብቻ ወደ መኝታ አትሂድ፡፡ በቂ ዕረፍት አግኝቼ የለምን? መኝታ ለምን አስፈለገኝ? ብለህ ራስህን ጠይቅ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ስትተኛ ውለህ እንቅልፍ ያምርሃልና፡፡ ነገር ግን ሰይጣን ሊፈትንህ ከሆነ በምትተኛበት ጊዜ እንቅልፍ ከአይንህ ይርቃል:: ተከትሎም ፈተናው ይመጣና ወደ ዝሙት ሕሊናህ ይሳባል፡፡ ሰውነትህንም በመደባበስ ፍትወትህን ለማርካት ትጥራለህ፡፡ ስለዚህ ከመተኛትህ በፊት በደንብ መድከምህንና ቶሎ ማሸለብ መቻልህን መርምረህ ተኛ፡፡ ሲ ጸሎት ማድረግንም አትርሳ የሚረሳ ነገር አይደለምና፡፡ ስትተኛም በጀርባህ ወይም በሆድህ አትተኛ:: ከዚህ ይልቅ በጎንህ ለመተኛት ሞክር፡ አመጋገብህ በልክ ይሁን ጾምን በተገቢው መንገድ ጹም፡ ቅዱሳት መጻሕፍትን አንብብ፡፡ የመንፈሳዊ ሙያ ባለቤት ከሆንክ የምታወቀውን ዜማ ድምፅ አወጥተህ አንጐራጉር፡፡ ያም ባይሆን የምትችለውን መዝሙር ዘምር። ሽ. እንዲህ ያለ ፈተና ሲነሣብህ አንድ ዓይነት የአካል እንቅስቃሴ (ስፖርት) ሥራ:: ወይም ወዲህና ወዲያ ተንቀሣቀስ፡፡ ከዚህም ሁሉ ይልቅ ደግሞ ከሆነልህ መስገድህ ይመረጣል:: ሽንትን መሽናትም ጥሩ መድኃኒት ሊሆንህ ይችላል:: በየጊዜው ጸበል መጠመቅንም ቸል አትበል፡፡ ነገር ግን ይህን በምታደርግበት ጊዜ ሕዋሳተ አንስትን ከማየት በእጅጉ ተጠንቀቅ፡፡
Show all...
👍 15 5
የተመከረ ሰው ምን ፈርቶ ከክፉ ሥራው ይመለሳል?    በኃጢአት ተግባር ላይ ያለ ሰው «ምን ይመጣብኝ ይሆን?›› እያለ ማሰቡ በውስጡ እግዚአብሔርን መፍራት እንዳለ ያሳያል፡፡ ምንም እንኳን ከኃጢአት መላቀቅ ባይችል ይህ ፍርሃቱ እንደ ጽድቅ ሊቆጠርለት ይችላል፡፡ ያላየውን እግዚአብሔርን መፍራት የማመን ምልክት ነውና፡፡ እግዚአብሔር የሚያመጣውን ፍርድ አስቦ መፍራት ከኃጢአት አንጽቶ እንደ ጻድቅ ሊያስቆጥር መቻሉን መጽሐፈ መነኮሳት በዚህ መልኩ ገልጾታል:: «ፍራህ እምእንታክቲ ምግባራት እንተ ትትኄበብ ከመ ባቲ መገሥጽ እስመ ዘከመዝ ግዕዙ ይትበልሃ ከመ ውእቱ የሐውር በአፍኣ እምፍኖታ» : «ቅጣትና ተግሣጽ እንደሚያስከትል ከጠረጠርከው ሥራ ሁሉ ተጠበቅ እንዲህ ሲፈራ የሚኖረው ሰው ከኃጢአት ውጭ ነው ይባላልና›› ማለት ነው:: ማር.ይስ.አን.16 ምዕ 1   ሰው ሁሉ ክእግዚአብሔር ጋር እንድ መሆን የሚችለው ከእነዚህ ከሦስቱ መንገዶች ቢያንስ እንኳን በአንዱ መጓዝ ከቻለ ብቻ ነው:: አንደኛው ያለ ምንም ምክንያት በራሱ ተነሣሥቶ እንደ አብርሃም ፈጣሪውን ፈልጎ ካመነ። ሁለተኛው እንደ ቅዱስ ጳውሎስ በግርማ እግዚአብሔር ተገልጾ ከተመለስ፡፡ ሦስተኛ ደግሞ በክፉ ሥራው ምክንያት የሚመጣበትን ቅጣት አስቦ ከፈራ ነው፡፡ የሐዋ 9፥6፣ ማር ይስ አን 3 ምዕ1 ለምሳሌ:- እንደ ቅዱስ ወቅሪስ፡፡ ቅዱስ ወቅሪስ መልከ መልካም ነበረ። ከዕለታት በአንድ ቀን ከሴት ጋር ተቃጠረ፡፡ በዚያችም ሌሊት ራእይ አየ፡፡ ራእዩም «እርሱ ታሥሮ ከብዙ እሥረኞች ጋር በንጉሡ ፊት ቆሞ እሥረኞቹ እያንዳንዳቸው በተራ ሲመረመሩ እርሱ ግን የቀጠርኳት ሴት ባሏ አሣሥሮኝ ይሆን? እያለ ሲጨነቅና ሲፈራ በዚህ ጊዜ ጠባቂ መልዐኩ ከወዳጆቹ አንዱን መስሎ መጥቶ ይህን ሥራ ሠርተህ እንዳታሲዘኝ ማልልኝና እኔ ልዋስህ እያለ ሲያስምለው›› ነበር። ከዚያ በኋላ ሄላኔ የምትባል ደግ ሴት ነበረች ወደ እርሷ ሄዶ ያየውን ራእይ ነገራት፡፡ እርሷም ተርታ ልብስ ለብሰህ አልባሌ መስለህ ፈጣሪህን አገልግለው ይምርሐል አለችው፡፡ እርሱም እንደነገረችው አድርጐ ከፈጣሪው ታርቋል፡፡ ማር ይስ አን 3 ምዕ 1 እንዲህ ከሆነ ፍርድን አስቦ መፍራት ጻድቅ ያደርጋል ቢባል ምን ይደንቃል?    ከክፉ ሥራ ለመመለስና ንስሐ ለመግባት ጥርጊያ ጎዳናው እግዚአብሔርን መፍራት ነው :: እግዚአብሔርን መፍራት ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ርኅራኄን እንደሚያስገኝ ከዚህ በታች የተጻፈው ታሪክ ያስረዳል:: የእግዚአብሔር ነቢይ ኤልያስ <<በእግዚአብሔር ፊት ክፉን ሥራ ለመሥራት ራሱን ለሸጠ>> ለአክዓብ የሚደርስበትን ቅጣት ሁሉ በነገረው ጊዜ አክዓብ «ልብሱን ቀዶ ገላውን ማቅ አለበሰ፥ ጾመም፣ በማቅ ላይም ተኛ ቅስስ ብሎም ሄደ፡፡›› ይላል:: በተለይ «ቅስስ ብሎ ሄደ» የሚለው ዐረፍተ ነገር የአክዓብን ፍርሐትና ድንጋጤ ያመለክታል:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር «ኤልያስ ሆይ አክዓብ እንደ ደነገጠ (እንደፈራ) ተክዞም እንደሄደ አየህን? በፊቴ የተዋረደ ስለሆነ በልጁ ዘመን በቤቱ ላይ ክፉ ነገር አመጣለሁ እንጂ በእርሱ ዘመን ክፉ ነገር አላመጣም።›› በማለት በይቅርታ ወደ አክዓብ መመለሱን ተናግሯል:: 2ነገ 20፥27 ሰው በክፉ ሥራው «ምን ይመጣብኝ ይሆን?» እያለ ሲፈራ እግዚአብሐርን መፍራቱ እንጂ ሌላ አይደለም:: ከላይ የተጠቀሰው የአክዓብ ታሪክ እግዚአብሔርን መፍራት የሚያስገኘውን ታላቅ ጥቅምና በእግዚአብሔርም ዘንድም ያለውን ተወዳጅነት ያስረዳል፡፡ ሰይጣን ደግሞ ሰው እግዚአብሔርን በመፍራቱ ብቻ እንኳን የሚያገኘውን ጥቅም ያውቃልና የዓለምን ምሁራን አስነሥቶ በልዩ ልዩ ጐዳና ፍርሐተ እግዚአብሔርን ከሰው ልብ የሚያርቅ ንግግር ያናግራቸዋል፡፡ አንድ ጊዜ ፍርሐትና የበደለኝነት ስሜት ጤናን ሊያቃውስ እንደሚችል ሌላ ጊዜ ደግሞ ፍርሐት በራስ የመተማመን ጉድለትና የብቃት ማነስ ምልክት እንደ ሆነ በማስረዳት ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት በፍርሃት እንዳይመላለሱ ለማድረግ ይጥራሉ፡፡ እኛ ክርስቲያኖች ግን ምንም ከበደል መራቅ ባይቻለን ፍርድን አስቦ መፍራታችን ብቻ እንኳን ዋጋ ያለው መሆኑን እንረዳለን፡፡ ሰይጣን በውጫዊ ማንነታችን ሰልጥኖ ኃጢአት ቢያሠራንም ፍርድን አስበን መፍራታችን በውስጣችን የምንገዛው ለእግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታል፡፡ ውጫዊው ኃላፊና ፈራሽ ሲሆን ውስጣዊው ግን ዘለዓለማዊ ነው፡፡ በውጫዊው ሰውነት ከመገዛት በውስጣዊው መገዛት በብዙ ይበልጣል:: እንዲሁም በአፍኣዊ ማንነታችን ኃጢአት እየሠራን ለሰይጣን ከምንገዛው ይልቅ በውስጣችን ለእግዚአብሔር የምንገባው አገዛዝ ይበልጣልና መጨረሻችን የእግዚአብሔር መሆን ነው:: ስለዚህ «ለእግዚአብሔር በፍርሐት እንገዛ›› መዝ 2፡11 ብንበድልም ፍርሐትን ከልባችን አናርቃት። «ግብረ አውና>>ን መፈጸም ሰው መግደል ሊሆን ይችላል?   ብዙ ሰዎች ዘር ሲክፍሉ ወይም ሲፈሳቸው ይልቁኑም አውቀው ያደረጉት ከሆነ «ሰው እንደ መግደል ይቆጠርብኝ ይሆን?» እያሉ ራሳቸውን መጠየቃቸው አይቀርም፡፡ በእርግጥ ግብረ አውናንን እየፈጸሙ ዘርን ማፍሰስ ሰው እንደ መግደል ይቆጠር ይሆን?    ወንድና ሴት ሩካቤ ሲያደርጉ ከወንድ ዘር ከሴት ደግሞ ደም ተከፍለው ተዋሕዶ ባደረጉ ጊዜ ተከፍሎዋ እንደ የብርሃን ፋና ይሁን እንጂ በዚያው ጊዜ ነፍስም አብራ ትከፈላለች:: ነገር ግን ሴቶች በየወሩ ደም ሲያዩ ወንዶችም ዘር ሲወጣቸው ነፍስ እንደ ማጥፋት አይቆጠርባቸውም። እንዴት? ምሥጢሩ እንዲህ ነው:- እነሆ እሳት በእንጨት ውስጥ መኖሩ የታወቀ ነው:: ሆኖም አንድ እንጨት ከሌላ ጋር ሳይሳበቅ ለብቻው እሳት መፍጠር አይችልም:: እሳት በእንጨት ውስጥ ይገኛል ቢባልም ቅሉ እንጨት መስበር እሳት እንደ ማጥፋት አይቆጠርም:: እንጨት ምሳሌነቱ እንደ ሴት ደምና እንደ ወንድ ዘር ሲሆን እሳት ደግሞ እንደ ነፍስ ነውና፤ ሴቶች ለብቻቸው የሚያስገኙት ደም ወንዶችም ለብቻቸው የሚከፍሉት ዘር ነፍስን ሊያስገኝ ስለማይችል ሰው እንደ መግደል ሊቆጠር አይችልም:: ሰው የሚባለው ራሱ አራት ባሕርያተ ሥጋ ሦስት ባሕርያተ ነፍስ ያሉት ፍጥረት ነውና፡፡ ስለ ነፍስና ሥጋ በአጠቃላይ ስለ ሰው ተፈጥሮ የበለጠ ለመረዳት በዚሁ መጽሐፍ የመጀመሪያ ክፍል የሕይወት አጀማመር የሚለውን ንዑስ ክፍል ያንብቡ፡፡ ግብረ አውናንን የሚፈጽሙ ሰዎች በተያያዥ ሊከሠትባቸው የሚችለው ቀጣዩ ጥያቄ ደግሞ ሩካቤ ሥጋ ፈጽመው የማያውቁ ከሆነ ‹‹ከዚህ በኋላ ድንግል ልባል እችላለሁ?» የሚል ነው፡፡ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሚሆን ሐሳብ ስለ ሴቶች ድንግልና በሚያትተው ንዑስ ክፍል «ድንግል ነኝን?» በሚለው ርዕስ ሥር የሰፈረ በመሆኑ እንዲያነቡት ተጋብዘዋል፡፡    «ግብረ አውናን» የሚያስከትለው ጉዳት    ግብረ አውናን (ሴጋ) ውጥረትን ለፈጠረ አንድ ችግር የተሳሳተ አማራጭን መጠቀም እንደመሆኑ መጠን በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ብርታትና ጥንካሬን የሚጠይቁ መንገዶችን እንድንሸሽ ያለማምዳል:: ይህ ማለት ደግሞ እጅግ ሲበዛ ሰነፍ እንድንሆን ያደርጋል ማለት ነው::    ግብረ አውናን ኃጢአት እንደ መሆኑ መጠን በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ቅጣትን ያስከትላል፡፡ በዚህ ዓለም ቅጣቱ እንደ አውናን ከመቀሠፍ ሊጀምር ይችላል፡፡ ዘፍ 38÷9 ሰላም ማጣት፣ ቁጭት፣ ጸጸት፣ ጭንቀት፣ መረበሽ፣ ንጹሕ ያለ መሆን ስሜትና የመሳሰሉት የግብረ አውናን እንጻራዊ ጉዳቶች ተደርገው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
Show all...
👍 11 2🥰 2
ቀ. ሰውነትህ ሲበላህ ይልቁኑም ወደ አባለ ዘርዕ አካባቢ ከሆነ ትኩረት ሰጥተህ አታስበው፡፡ ምክንያት እንዳይሆንብህ ተጣጥበህ ንጹሕ ለመሆን ሞክር፡፡ የበላህን ቦታ ግን በምንም መልኩ አትከከው፡፡ ማከክ ሰውነትን ከማቁሰል በቀር ይህን ለመሰለ ፈተና መፍትሔ አይሆንምና፡፡ ከዚያ ይልቅ መጽሐፈ መነኮሳት «ግበር ትእምርተ መስቀል በሕሊናከ ውስተ መካነ ደዌከ› ፤ ‹ሕመም ወይም ማላከክ በተሰማህ ቦታ ላይ በሕሊናህ የመስቀል ምልክት ሥራ» ይላልና። በሚያሳክክህ ቦታ ላይ በሕሊናህ አማትብበት፡፡ በሕሊናም ማለቱ የሚያይህ ሰው ነገር እንዳይመራመርኽ ለማድረግ ነው፡፡ በተረፈ ግን አጥብቀህ ጸልይ፡፡ ሁላችንንም እግዚአብሔር ይርዳን! በቀጣይ ምዕራፍ አምስት <<ምትረተ አስኪት>> በሚል ይቀጥላል..... ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ። @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot

29👍 6👏 1
ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)       ምዕራፍ ፬/4 ክፍል ፪/2 ...........................................................   «ግብረ አውናን»ን በተመለከተ አሳሳች ሐሳቦች     ግብረ አውናንን በተመለከተ ከተለያየ አቅጣጫ የሚሰነዘሩ ሐሳቦች አሉ:: ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ምንም እንኳን በቀጥታ ድርጊቱን ለማበረታታት የተነገሩ ባይመስሉም ብዙዎችን ከዚህ ክፉ ልማድ እንዳይወጡ ለማሰር ኃይል ያላቸው ናቸው:: ከእነዚህም ሐሳቦች መካከል ጥቂቶቹ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል:: ሀ) ብዙ ሰዎች «አውናን የተቀሠፈው ዘሩን በማፍሰሱ ሳይሆን ለወንድሙ ዘር ማቆምን  ስላልወደደ በምቀኝነቱ ነው» በማለት መሠረት የሌለው ሐሳብ ይሰነዝራሉ፡፡ በእርግጥ አውናን ለወንድሙ ዘር ላለማቆም ማሰቡ ምቀኛ ያሰኘዋል:: ያስቀሠፈው ዋና ምክንያት ምቀኝነቱ ነው ማለት ግን ስሕተት ነው፡፡ ምቀኝነት ሊያስቀሥፍ የሚችል ኃጢአት ቢሆንም አውናን የተቀሠፈው ግን «ዘሩን በማፍሰሱ» እንጂ በምቀኝነቱ አይደለም።
Show all...
👍 5 5
ሰው የራሱን የግል አስተያየት ወደ ጎን አድርጐ እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ለሕዝቡ የሚናገረውን ማድመጥ ከፈለገ አውናን የተቀሠፈበትን ዋና ምክንያት መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ ምቀኝነትና ዘርን ማፍሰስ በጣም ይለያያሉ:: ምቀኝነት የልቡና ሐሳብ ነው:: ዘርን ማፍሰስ ግን በግልጽ የሚታይ ተግባር ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ አውናን የተቀሠፈበትን ምክንያት ሲገልጽ «ሥራውም በእግዚአብሔር ዘንድ ክፉ ሆነበት» ይላል እንጂ ‹‹ምቀኝነቱ›› አይልም:: ታዲያ የአውናን ክፉ ሥራው ምን ነበር ዘሩን በምድር ላይ ማፍሰሱ አልነበረምን? ምቀኝነት በሥራ የሚገለጥ የልቡና ክፋት እንጂ በራሱ «ሥራ» አይባልምና፡፡    ከላይ እንደተብራራው አውናን የተቀሠፈው ዘሩን በማፍሰሱ ሳይሆን በምቀኝነት ብቻ እንደሆነ አድርጐ መናገር መሠረት የሌለው የሰይጣን ትርጓሜ ከመሆኑም ባሻገር «ዘርን ማፍሰስ›› አያስቀጣም ወይም ሊያስቀሥፍ አይችልም እያሉ እንደማወጅ ነው፡፡ እንዲህ ማለት ደግሞ የእግዚአብሔርን ፍርድ ፈርቶ ከክፉ ሥራው ለመለስ ያለውን ወጣት ለምን ትመለሳለህ ግፋበት እንጂ እያሉ እንደመምከር ይቆጠራል፡፡ ክፉን ነገር እንደማያስቀጣ አድርጐ መተርጐም ተሳስቶ ማሳሳት ነውና ሊታረም ይገባል:: በዚህ የተሳሳተ ሐሳብ ተወግተው ክፉውን ልማድ እንደ በጐ ይዘው የሚማቅቁትን ወጣቶች ቤት ይቁጠራቸው፡፡ ለ) በመሰንጋት ራስን በራስ ለማርካት የመሞከር ተግባር በብዙ ወጣቶች ዘንድ የተለመደ ሆኗል:: ይህ ድርጊት ፆታና ዕድሜ አይለይም:: በአጠቃላይ ሲታይ ወንዶች ከሴቶች ቀደም ባለ ዕድሜ ቢጀምሩም ሴቶችም ከዚህ ተግባር ውጭ አይደሉም:: ጥናቱ በኛ ሀገር አይካሄድ እንጂ አንድ በአሜሪካን ሀገር የተደረገ ጥናታዊ ጽሑፍ እንደሚያመለክተው ከሆነ ከአጠቃላይ ወጣት ልጃገረዶች ሁለት ሦሥተኛው እጅ ከአጠቃላይ ወጣት ወንዶች ደግሞ ዘጠና አምስት በመቶ የሚሆኑ ወጣቶች የተለያየ ርዝማኔ ላላቸው ጊዜያት «በማስተርቤሽን› ልማድ ይያዛሉ፡፡ ይህ አኀዝ ለወንዶች ሙሉ በሙሉ እንደማለት ነው:: ከሁሉ የሚያስደንቀው በሰባዎቹ ውስጥ ከሚገኙ አሮጊቶች ሠላሳ ሦስት እጅ ከሽማግሌዎች ደግሞ አርባ ሦስት እጅ የሚሆኑት አሁንም በዚሁ የመሰንጋት (ራስን በራስ ማርካት) ተግባር ውስጥ መገኘታቸው ነው፡፡ (ኢንካርታ ብሪታኒካ ኢንሳይኮሎፒዲያ 2004) በኛም አገር ቁጥሩ ይህን ያህል አይጋነንን እንጂ ብዙ ወጣቶች በዚህ ክፉ ልማድ መመረዛቸው በተለያየ መንገድ ይሰማል:: ከዚህ የተነሣ አንዳንድ ሰዎች «ይህ ድርጊት ጤናማነትን ስለሚያመለክት የሚያሳስበው በዚህ መንገድ የማይጓዙ ሰዎች ሕይወት ነው» እስከ ማለት ደርስዋል::    በዓለም ላይ ሴጋን መፈጸም በብዙኀኑ ዘንድ የተለመደ በመሆኑ ብቻ ድርጊቱ እንደ ተገቢና ጤናማ የሰውነት ተግባር ሊቆጠር አይችልም፡፡ ወጣቶችም በዚህ ሐሳብ በመሳሳት በድርጊቱ የተለከፉ ከሆነ ለመላቀቅ ከመጣጠር ይልቅ «ለካ እኔ ብቻ አይደለሁም!» እያሉ መጽናናት አይገባቸውም:: ይህን ተግባር ሞክረውትም የማያውቁ ከሆነ ለመሞከር ከማነሣሣት ይልቅ ጨርሶ የዚህን ክፉ ኃጢአት ጣዕም አለመቅመስ በሕይወታቸው ያለውን ፋይዳ ተረድተው ከመሞክር መታቀብ ይኖርባቸዋል::    በዓለማችን መፋታት፣ ዝሙት፣ መግደል፣ ውርጃ፣ ባዕድ አምልኮ፣ ውሸትና መሥረቅ በብዙ ሰዎች ዘንድ የተለመዱ ናቸው፡፡ ታዲያ እነዚህ ተግባራት በብዙኀኑ ዘንድ መተግበራቸው ትክክል ቢሆኑ ነው እንጂ ያሰኛቸዋልን? ሴጋ መፈጸምም እንደዚሁ ነው:: ከላይ በፊደል «ሀ» እንደተጠቀሰው ሐሳብ ሁሉ ሰዎች ለክፉ ሥራቸው አጋር እንዳላቸው እያሰቡ እንዲጽናኑ ሰይጣን የዘረጋው የጥፋት ወጥመድ «ብዙዎች የሚፈጽሙት ከሆነ እንዴት ኃጢአት ይሆናል?» የሚል ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን «ብዙዎች ኃጢአት ሲሠሩ አይተህ ከእነሱ ጋር አትተባበር ይላል፡፡›› ዘፀ 23÷2 ሐ) ብዙ የሕክምና ባለሙያዎችና የሥነ አእምሮ ጠበብቶች «ክዕወተ ዘርዕ» ብዙ ዓይነት ሥነ ልቡናዊና አካላዊ የጤና ችግር እንደሚያስከትል በአንድ ልብ ይስማማሉ፡፡ እንዲያውም የብዙዎችን ጓዳ ከሚያንኳኳው ከ‹‹ስንፈተ ወሲብ› ጀምሮ የኩላሊትና የልብ በሽታዎች ድረስ በሴጋ አማካኝነት ሊመጡ እንደሚችሉ በሰፊው ተዘግቧል፡፡ ሆኖም ግን የዓለም ጠቢባን ቃላቸው ወጥነት የሚጎድለውና ተለዋዋጭ ነው:: ስለዚህ አንዱ የካበውን ሌላው ሲንደው ይታያል፡፡    <<የዓለም ጠቢባን ቃላቸው ወጥነት ይጎድለዋል>> ለሚለው ሐሳብ ማስረጃ የሚሆነው ብዙ ምሁራን «ሴ.ጋ» ወይም ‹‹ማስተርቤሽን› ለልዩ ልዩ በሽታ ያጋልጣል ሲሉ ሌሎች ደግሞ በጭራሽ አያጋልጥም ማለታቸው ነው:: እንዲያውም ከእነዚህ መካከል ጥቂቶቹ «ሴጋ» ወይም ‹‹ማስተርቤሽን›› ለአንዳንድ በሽታዎች የመጋለጥ ዕድልን ይቀንሳል ሲሉ ይደመጣል፡፡ ለምሳሌ:- በሀገራችን ከሚታተሙት በርካታ የግል ጋዜጦች አንዱ የሆነው ሜዲካል ጋዜጣ በ1995 በመጨረሻዎቹ ሁለት ወራት ውስጥ ካሳተማቸው ጋዜጦች በአንዱ ላይ ‹‹ማስተርቤሽን» በካንሠር የመያዝ ዕድልን እንደሚቀንስ ጥናታዊ መረጃዎችንና የባለሙያዎችን አስተያየት ጠቅሶ አስፍሯል፡፡    እንደ የሕክምና ባለሙያዎች ሁሉ የሥነ አእምሮ ጠበብቶችም «አንድ ሰው ሴጋ በመፈጸሙ ምክንያት ጉዳት ሊያገኘው የሚችለው የአእምሮና የስሜት መረበሽን የሚያስከትል የበደለኝነት ስሜት የሚሰማው ከሆነ ብቻ ነው» በማለት ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ሐኪሞችና የሥነ አእምሮ ጠበብቶች እንደ ሌላው ሰው ሁሉ ለስሕተት የተጋለጡ፣ ደካማ ፍጡራንና ፍጽምና የሌላቸው በመሆናቸው አመለካከታቸው በየጊዜው ይለዋወጣል:: ማን ያውቃል? ዛሬ ጉዳት አያስከትልም ያሉትን ድርጊት ነገ አንድ ያልደረሱበትን ዕውቀት ሲያገኙ ጉዳት የሞላበት ነው ይሉት ይሆናል፡፡ ያን ጊዜ የዛሬ ቃላታቸውን ተቀብለው በክፉ ልማዱ ጸንቶ የተገኘ ወጣት መጨረሻው ምን ይሆን? በዓለም ጠቢባን ቃል ልቡን ከሚያሳርፍ ይልቅ በእግዚአብሔር ሕግና ሥርዓት ጸንቶ የሚኖር ሰው እንዴት የተመሰገነ ነው?    የዚህ መንፈሳዊ መጽሐፍ ዋና ዓላማ ዘርን በገዛ እጅ በማፍሰስ ስሜትን ለማርካት መሞከር ምን ያህል ወይም ምን ዓይነት የጤና መታወክ ይፈጥራል? የሚለውን ማብራራት ሳይሆን ምን ያህል? መንፈሳዊ ጉዳት ያስከትላል ለሚለው ጥያቄ በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው::    ምንም እንኳን ከዚህ በላይ ምንም ዓይነት የጤና ጉዳት እያስከትልም፡ ጉዳት የሚያስከትለው ድርጊቱን የሚፈጽመው ሰው የበደለኘነት ስሜት የሚሰማው ከሆነ ብቻ ነው::›› በሚል በባለሙያዎች የተሰነዘረው ሐሳብ አስተማማኝነት እንደሌለው ቢገለጽም በዚህ ክፉ ልማድ የተመረዙትንና እየተሳቡ ያሉትን ሰዎች ከድርጊታቸው እንዳይላቀቁ የሚጫወተው ሚና ግን እጅግ የከፋ ነው:: ምክንያቱም ይህ ሥራዬ የጤና መታወክ የሚፈጥርብኝ ስጸጸት ብቻ ከሆነ ጉዳት እንዳያስከትልብኝ ራሴን እንደ ጥፋተኛ እየቆጠርኩ መቆርቆር የለብኝም እያሉ እንዲጽናኑ ስለሚያደርጋቸው ነው::   በዚህ መልኩ በክፉ ሥራቸው እንዳይጸጸቱና እግዚአብሔር የሚያመጣባቸውን የቅጣት ፍርድ እያሰቡ እንዳይፈሩ በጤና ባለሙያዎችና በሥነ አእምሮ ጠበብቶች የተሰጣቸው ምክር ምንም ዓይነት ፍርሃተ እግዚአብሔር በልቡናቸው እንዳይኖር ያደርጋል፡፡ ይህ ደግሞ <<የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነውና›› በእግዚአብሔር ዘንድ የተጣሉና ረድኤት የሌላቸው እንዲሆኑ ከማድረጉም በላይ ከክፉ ሥራቸው እንዳይመለሱ ያደርጋል:: ምክንያቱም ሰው ከክፉ ሥራው የሚመለሰው በዋናነት ክፉ ሥራው የሚያስከትልበትን ፍርድ አስቦ ነውና፡፡ ምንም ክፉ ነገር አያገኝኽም እየተባለ በባለ ሙያ
Show all...
የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot

6👍 3
"ገብር ኄር" ቸር አገልጋይ ማነው ለንጉሥ የታመነ መክሊቱን ያልቀበረ አትርፎ የከበረ (፪) ባለ አምስቱ መክሊት መልካም ያደረገው በመውጣት በመውረድ አትርፎ መጥቶ ነው በጥቂቱ ታምኖ በብዙ የተሾመው ባለ አምስቱ መክሊት ሊቀ ጳጳሱ ነው። ሳይሰለች የተጋ ባለሁለት መክሊት የታመነ እረኛ በፍቅርና በእምነት ግባ የተባለው ወደ ጌታው ደስታ አጥምቆ ያቆርባል ካህኑ የጌታ። ለሚበልጠው ጸጋ ተጠርቶ የነበረ መክሊቱን ደብቆ ቆፍሮ የቀበረ ሰነፍ ባርያ ተብሎ ወደ ፍርድ ተጣለ ማኔ ቴቄል ፋሬስ በአምላክ ፊት ቀለለ። ፈቃድህን ማድረግ ነፍሱ ለምትወደው ወንጌልህን መግለፅ የየዕለት ግብሩ ነው ህግህ ለዘለላም ተጽፎ ይኖራል በታላቅ ጉባኤ ጽድቅህ ይነገራል።         በዘማሪ ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
22👍 4
ተብለን ወደ ውርደት አዘቅት እንዳንላክ መጠንቀቁ አይከፋም፡፡ የመሾም የመሻር የማሳደግና የማውረድ ሥልጣን የእግዚአብሔር ነውና፡፡ “ከእናንተ መካከል አንዱን እንኳ እንዳናስቸግር ቀንም ሌሊትም እንሠራ ነበር” (፩ኛ ተሰ. ፪፥፱) በጎና ታማኝ አገልጋዮች ሆነን እንድንገኝ ጠንክረን ልንሠራ ይገባናል፡፡  በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ጥቅሶች፦ -፪ኛ ጢሞ ፪፥፩-፲፮ -፩ኛ ጴጥ ፭፥፩-፲፪ -የሐዋ ሥራ ፩፥፮-፱ ምስባኩም፦ መዝ ፴፱፥፰ "ከመ እግበር ፈቃድከ መከርኩ አምላኪየ ወሕግከኒ በማዕከለ ከርሥየ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ" "አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድኩ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው በታላቅ ጉባዔ ጽድቅህን አወራሁ" ወንጌሉም፦ ማቴ ፳፭፥፲፬-፴፩ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Show all...
4👍 2