cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ትንሳኤ ዘኢትኤል መማሪያ

የአባቶቻችን እና የሀገራችን ታሪክና ጥበብ ግዕዝን, ስለጥንት ነገስታት ታሪክ፣ ስለዕፆች፣ መድሀኒቶች፣ መሰውሮች፣ የደመና ጥበብ ፣ቅርሶች፣ጥንታዊ የብራና መፅሐፍት፣ስነ ፈለክ ፣አክሲማሮስ፣ራዕየ ሳቤላ፣መፅሐፈ ጅማትርያ ፣መፅሐፈ ፓዝዮን፣መፅሐፈ ፀሐይ፣መፅሐፈ ልሳን፣መፅሐፈ ጥበብ፣የመላእክት ቋንቋ ወዘተ ... ለጓደኛ ያስተላልፉ ኢትኤልን ስለመረጣቹ አመሰግናለሁ ይቆየን.. 👳‍♂

Show more
Advertising posts
6 728Subscribers
+224 hours
-247 days
-7330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ቤታችን ጨልሟል ነገር ግን መዛግብቶቻችን ላይ የብርሀናት ጭላንጭል ይታያል ቤታችንን እንፈትሽ ወደ ቀደመዉ ተፈጥሯዊዉ እረፍት እንመለስ! አ40 ዳ100 ም4=144 ኢ40 የ90 ሱ7 ስ7=144 #####የፊደል አዋጅ ኁልቁ ፊደላት ሀገራችን ኢትዮጵያ ጥንታዊና ባለ ብዙ ሀብት ባለቤት ካደረጓት ዉስጥ የራሷ የሆነ ፊደል የራሷ የሆነ ቁጥር የራሷ የሆነ ስርዓት እምነትና ባሕሎቿ ናቸዉ። የአንድን ሀገር ቀደምትነት የሚለካዉ በቤቷ ዉስጥ ባሉት ሀብቶች ሲሆን ሀገራችንም ኢትዮጵያ እነዚህንና ሌሎች ጥልቅ የሆነ ሀብት ያላት ሀገር መሆኗን ሁሉም ያዉቃል ነገር ግን እኛ ኢትዮጵያዉያኖች በቤታችን ዉስጥ ያለዉን ሀብታችንን ሳናዉቅ ከቤታችን ዉጪ ባለ የባዕዳንን አስተምህሮት ፍለጋ ቤታችን ዉስጥ ያለዉን ዘንግተነዋል። በቅርብ ያለ ጸበል ልጥ መንከሪያ ይሆናል እንደተባለሁ ሁሉ ቤታችን ዉስጥ ያለዉን  ዕዉቀት ንቀነዉ ከረሳነዉ ብዙ አመታት ተቆጥረዋል። የረሳናቸዉንና አገልግሎታቸዉን ያላወቅናቸዉ እዉቀቶችን ጥናት ከማድረግ ይልቅ የዉጪ ሀገር ሰዉ መጥቶ አጥንቶ ባቀረበልን ሀሳብ ላይ  ብቻ አምነን  ተቀምጠናል።ለምን? ቀደምት ኢትዮጵያዉያን ትልቅ የሆነ የማይነቃነቅ መሠረት በዓለት ላይ ጥለዉልን አልፈዉ እኛ ግን እነሱ ባስቀመጡልን የዓለት መሰረት ላይ ቤታችንን መገንባት ሲገባን ሌላ አዲስ መሠረቱም በአሸዋ ላይ የሆነ መሠረት ካልቆፈርን በማለት አይምሮዋችንን ካደከምነዉ ቆይተናል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በቤቱ ያሉትን ዕዉቀቶች መመልከት መጠቀምና በራሱ ሀሳብ ላይ መቆም ይገባዋል። ንቃተ ልቦናችንን ልናበረታዉና ያላስተዋልነዉን ልናስተዉለዉ ይገባል።።።።።።።!!! ##ኁልቁ ፊደላት የፊደል አዋጅ አቆጣጠርና ህግ ነዉ።ይህም የፊደል አቆጣጠርና ህግ ፳፮ቱ የግዕዝ ፊደላትን የሚመለከት ሲሆን ፊደላቶቹም የራሳቸዉ የሆነ ቁጥር ዉክልና አላቸዉ ፊደል ቁጥር አለዉ ቁጥርም ፊደል አለዉ።ይህንን የፊደል ህግ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለኛ ለልጆቻቸዉ ያስቀመጡበት ምክንያት ጥበብን እንድንረዳ እንዲሁም ጥንታዊ የሆኑ መዛግብቶችን ስንመረምር ምዕራፍና ቁጥሮቻቸዉ በዚሁ የፊደር አቆጣጠርና ህግ የተጻፉ በመሆኑ የመዛግብቶቹን አዘጋጆች ከማን ዘንድ እንደሆኑና ሀሳባቸዉን እንድንረዳና መሰረታቸዉን አዉቀን በጥበብ እንድንኖር ይረዳናል ከዚህም በተጨማሪ ስለ ከዋክብት ስለ ሰዉ ልጅ ባህሪና ስለ ዓዉዶች ፊደላትና ቁጥሮች ከሰዉልጆች ጋር ስላላቸዉ ቁርኝት በደምብ እንድንረዳና ጠልቀን እንድናዉቅ ይረዳናል። ###የፊደል አዋጅ አቆጣጠርና ህግ አገልግሎትና ጥቅማቸዉም ቀደምት ጠቢባን ስሞችን ከተፈጥሮ እንዲሁም ከሰማያዊ ስርዓቶች ጋር ያላቸዉን ዉክልናና ተምሳሌት እንድንረዳና እንድንገለገልባቸዉ እንድንጠቀምባቸዉ ከትበዉ አስቀምጠዉልናል። ይህንንም አቆጣጠርና ህግ ለመረዳት በቅድሚያ የራሳችን የሆነዉ ቁጥር ማወቅና መረዳት ይጠበቅብናል ይህም ማለት የምንኖርበትን ቤት የቤተሰባችንን ቋንቋ ማወቅ ሲሆን ይህንንም የገዛ ቤታችንን ቋንቋ ካላወቅንና ካልተረዳን በገዛ ቤታችን ባዳ እንደመሆን ይቆጠራል ስለዚህ ግዕዝን ማወቅ ቁጥሮቹን መረዳትና መለየት አስፈላጊና መሠረታዊ ነዉ ።የፊደል አዋጅ አቆጣጠርና ህግን በሀያ ስድስቱ የግእዝ ፊደላት ላይ የተወከሉትን በዝርዝር እናስቀምጣለን። ሀ፩ ለ፪ ሐ፫ መ፬ ሠ፭ ረ፮ ሰ፯ ቀ፰ በ፱ ተ፲ ኀ፳ ነ፴ አ፵ ከ፶ ወ፷ ዐ፸ ዘ፹ የ፺ ደ፻ ገ፪፻ ጠ፫፻ ጰ፬፻ ጸ፭፻ ፀ፮፻ ፈ፯፻ ፐ፰፻ ###የአቆጣጠር ህግ ከ ሀ እስከ ሆ የሚገኙትን ፊደሎች በሚጀምርባቸዉ ፊደር ጠቅልሎ ይቆጥረዋል ይህ  ማለትም ለምሳሌ  ሄዋን የሚለዉን ስም (ሄ) በ(ሀሌታዉ ሀ፩) ዉስጥ አስገብቶ ነዉ የሚቆጥረዉ። ሄ(ሀ፩) ዋ(ወ፷) ን(ነ፴) ሲሆን ድምራቸዉም ፺፩ የሚመጣ ሲሆን የቁጥሩና የሄዋን ተምሳሌቱም ሴቶችን ሲወክል እነሱም ልጅን በመዉለድ ተፈጥሮን የሚያስቀጥሉ ሲሆን የምኖርበትም ምድር በየ ፺፩ ቀናት ዉስጥ እየተዋለዱ ወቅቱን የሚመግቡ መጋቢያን ከዋክብት በየዘጠና አንድ ቀናት ምግብናቸዉን ጨርሰዉ አዲስ መጋቢ የሚመጣበትና የሚቀያየርበት የቁጥር ልኬት ነዉ። እንዲሁም ከሰዉ ወገን የሆኑትን ሁሉ ቁጥራቸዉን ያመሳስለዋል ለምሳሌ አዳም እና ኢየሱስ እንዲሁም በራዕይ ዮሐንስ የተጠቀሱትን መቶ አርባራት ሺ ህጻናትን በቁጥር ልኬት አንድ አድርጎ የሰዉ ልጆች ወገንነት ያመላክተናል። ዉድ የጠልሰም ሀሳብ ተከታታዮች ከኁልቁ ፊደላ ጋር ያላችሁን ሀሳብ የምታዉቁትንና የሚሰማችሁን አካፍሉን። በቀጣይ #ኁልቁ ፊደላትና የሰዉ ልጆች ባህሪ አወጣጥ #አራቱ ባህሪያትና አራቱ ወቅቶች ምግብናቸዉ #አራቱ አዉዶች አንዷ ቀን #አስራ ሁለቱ ከዋክብት
Show all...
          🌿የፊንጢጣ ኪንታሮት መንስኤ እና መፍትሔ🌿 👉የኪንታሮት ህመም ምልክቶች እንደኪንታሮቱ ቦታ የሚወሰን ሲሆን የዉስጠኛዉ የኪንታሮት አይነት ብዙዉን ጊዜ በአይን የማይታይ ቢሆንም በሚፀዳዱበት ወቅት ማማጥ ካለዎ የደም ስሮቹ ሊቆጡና በቀላለ ሊደሙ ይችላሉ፡፡ አንዳንዴ በሚያምጡበት ወቅት የዉስጠኛዉ ኪንታሮት አይነት ወደታች በመምጣትና በፊንጢጣ ዉስጥ በማለፍ ህመምና የመቆጥቆጥ ስሜት ሊኖረዉ ይችላል፡፡ 👉 የዉጪኛዉ የኪንታሮት አይነት በፊንጥጣ ዙሪያ ባለዉ ቆዳ ስር የሚገኝ ሲሆን የደም ስሮቹ በሚቆጡበት ወቅት ሊያሳክኩ ወይም ሊደሙ ይችላሉ፡፡ አንዳንዴ ደም በዉጭኛዉ ኪንታሮት ዉስጥ በመጠራቀምና በመርጋት ከፍተኛ ህመም፣ እብጠትንና መቆጣትን/መለብለብን ሊያመጣ ይችላል፡፡ 👉በሚፀዳዱበት ወቅት/ሰገራ በሚወጡበት ወቅት ከፊንጢጣ የሚወጣ ህመም የሌለዉ ደም/መድማት፡- ይህን ክስተት በመፀደጃ ሳህን ላይ ወይም በሶፍት ላይ ሊያዩ ይችላሉ፡፡ 🌿በፊንጥጣ አካባቢ የማሳከክ ወይም የማቃጠል ስሜት ካለዎ! 🌿በፊንጥጣ አካባቢ ህመም ወይም ምቾተ ያለመሰማት ካለዎ! 🌿በፊንጥጣ ዙሪያ እብጠት ካለዎ! 🌿የሰገራ ማምለጥ ካለዎ! ❤️ወደ ህክምና ባለሙያ በመሔድ መፍትሔ ይውሰዱበት❤️ 👉ምንም እንኳ ለኪንታሮት ዋነኛ ምልክቱ በሚፀዳዱበት ወቅት የደም መፍሰስ ቢሆንም በፊንጢጣ ደም መምጣት ሁሌ ከኪንታሮት ጋር ብቻ የተያዘ ሳይሆን እንደ የትልቁ አንጀት ካንሰር ወይም የፊንጥጣ ካንሰር ምልክትም ሊሆን ስለሚችል የህክምና ባለሙያዎን ማማከር ያስፈልጋል፡፡ 🌿ኪንታሮት ህመም ካለዉ፣ በተደጋጋሚ ወይም በጣም የሚደማ ከሆነ፣ወይም በኪንታሮት ማስታገሻ ህመሙ የማይሻሻል ከሆነ! 🌿ከኪንታሮት የህመም ምልክቶች ጋር አስፋልት/ሬንጅ የመሰለ ሰገራ ካለዎ፣የረጋ ደም ካለዎ፣ከሰገራዎ ጋር ደም ካዩ! 🌿 በጣም ከፍ ያለ የደም መፍሰስ ካለዎ፣ የመደበር ወይም የማዞር ስሜት ካለዎ! 🌿የኪንታሮት በሽታ መንስኤዎች በጥቂቱ። 🌿ኪንታሮት በፊንጥጣ ዙሪያ ባሉ የደም መልስ ላይ ጫና በሚበዛበት ወይም በሚፈጠርበት ወቅት የደም ስሮቹ ስለሚያብጡና ስለሚወጠሩ የህመሙ ምልክቶች ይታያሉ፡፡ በደም ስሮቹ ላይ ጫና እንዲጨምር ከሚያደርጉ ነገሮች ዉስጥ የሚከተሉት ይጠቀሳሉ። 👉 በሚፀዳዱበት ወቅት ማማጥ ካለ! 👉 መፀዳጃ ላይ ለረጅም ጊዜ መቀመጥ 👉 ተቅማጥ ወይም የሆድ ድርቀት ረዘም ላለ ጊዜ ከነበረዎ 👉ውፍረት መኖር 👉 እርግዝና 👉የፋይበር መጠናቸዉ አነስተኛ ወይም ፋይበር የሌላለቸዉን ምግቦች ማዘዉተር ናቸዉ፡፡ ❤️የኪንታሮት ህመም ጉዳቶች • የደም ማነስ እንዲከሰት ያደርጋል። • የኪንታሮት መታነቅ/ Strangulated hemorrhoid ❤️የሊቃውንቶች የዕጽዋት መፍትሔ❤️ 👉የዕሬት ፍሬ እና የክንፉ ግንድ 👉የምድር እንቧይ ፍሬ ❤️እነዚህን ዕጽዋት ፍሬያቸውን አድርቆ በብረት ምጣድ በጣም ሳያሳርሩ ቆልተው በደንብ አድርጎ ሰልቆ በርከት አድርጎ በማዘጋጀት! ግማሽ የሻይ ማንኪያ የተቆላ ግማሽ የሻይ ማንኪያ ያልተቆላው ዕጽዋቱ በመለካት በንፁህ ቅቤ አልያም በንፁህ ማር በመለወስ ማታ ማታ ኪንታሮቱ ያለበት ቦታ ቀብተው መተኛት ጧት ሲነሱ ትንሽ ውኃ ለብ አድርገው ይታጠቡት። 👉ይህ ድርጊት ከ ሁለት ሳምንት እስከ አንድ ወር ድረስ መጠቀም ይኖርቦታል።ሳያቆስል በሽታውን የሚያመክን ፍቱን መፍትሔ ነውና በአግባቡ ይጠቀሙ። የጥንት አባቶች እውቀት እና ጥበብ ሳይበረዝ እንደወረደ ይቀርባል። የአያቶቻችን የእጽዋት ጥበብ፣ በህይወትዎ ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው፣ ክፉ መናፍስትን እንዴት ማራቅ እንደምንችል፣ የብራና መጽሐፍት እና ጥቅማቸው በዚ ይዳሰሳሉ።
Show all...
"ሂድና ውደዳት!" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) በአንድ ወቅት አንድ ሰው ሚስቱ እንድትወደው ብዙ ነገር አድርጎ ስላልተሳካለት ሚስቱም ስላልወደደችው ተበሳጭቶ ወደሰባኪው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይሄዳል፡፡ "ሚስቴ እንድትወደኝ ብዙ ለፋሁ ፤ ያላደረኩት ነገር የለም ፤ምንም ልትወደኝ አልቻለችም፡፡ እንድትወደኝ ማድረግ የምችለው በምን መንገድ ነው?" ሲል በሀዘን ተሰብሮ ይጠይቀውና የሚነገረውን ጥበባዊ መንገድ በጥንቃቄ ለመረዳት እዝነልቦናውን አዘጋጅቶ የአባቱን ዓይን ዓይኑን እየተመለከተ የአንደበቱን ጥኡም ቃል ይጠባበቃል፡፡ ቅ/ዮሐንስ ግን የነገሩት በአጭሩ በሁለት ቃል ብቻ የተዋቀረ ነበር፡፡ "ሂድና ውደዳት!" ሰውየው 'ያልኩትን አልተረዳኝ ይሆን እንዴ?'  እያለ እያሰበ ጥያቄውን ደግሞ አቀረበ።  "ሚስቴ አልወደኝ አለች ምንም ባደርግ ልትወደኝ አልቻለችም ነው ያልኩት" አለ በድጋሜ፡፡ "ሂድና ውደዳት" አለው ሰባኪው በድጋሜ፡፡ አሁንም ለሶስተኛጊዜ ሰውየው "ልትወደኝ የሚገባት ሚስቴ አልወደደችኝም ነው ያልኩዎትኮ!" አለ፡፡ ሰባኪውም መልሶ "ሂድና ውደዳት!" አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ሰውየው እርሱ እንደሚወዳት ለመናገር 'እኔማ...' ብሎ ጀምሮ ራሱን መፈተሽ ጀመረ፡፡ እሱ ውስጥ ያለው፣ እርሱ የሚወደው፣ የእርሱ ፍላጎት የእርሱን የራሱን በእርሷ መወደድ እንጅ እርሷን መውደድ አልነበረም፡፡ ጊዜውን ለመወደድ በመጣር ብቻ አሳልፎታል፤ ጥረቱ ሁሉ እንድትወደው እንጅ እንዲወዳት አልነበረም፡፡  አዘነ፡፡ እርሷን መውደድ ሲገባው ራሱን በርሷ ለማስወደድ ሲጥር ኖሯል፤ አልተሳካለትም፡፡ ፍቅር የሚመጣው በራሱ በፍቅር እንጅ በሌላው ሁሉ ጥረት አይደለም፡፡ በሌላ ጥረት የሚመጣ ሰው ሰራሽ "ፍቅር" ካለ ግን ፍቅሩ ሀሰተኛ ነው፡፡ ራስን ከመውደድ አልፈን ራስን ወደማስወደድ ከመሄድ ይልቅ ሌላውን በመውደድ መወደድን አናጣውም፤ ፍቅር ሌላውን የሚወድ ከሆነ ፍቅርንማ እንደምን አይወድ! እርሷን ስትወዳት ፍቅሯን ታገኛለህ እንጅ ፍቅሯን ያለፍቅርህ አትሞክረው! አንዳንዶቻችን እኔ ላደረኩት ነገር ለምን አልተደነቅሁም ለምንስ አልተወደድኩም እንላለን። እንደዚህ ካልን ያደረግነውን ላደረግንለት ሳይሆን ለራሳችን ነው ማለት ነው ያደረግነው፤ ይህ ደግሞ የፍቅር ባህሪ አይደለም፡፡  እኛ ለሌሎች የሌለንን ፍቅርም ሌሎች ጋ ወደኛ መጠበቅ የለብንም፡፡ ለባለቤቴ ባደረኩላት ነገር ከእርሷ ምስጋናን የምሻ ከሆነና ካልተመሰገንኩ ከከፋኝ እኔ ከፍቅር የነፃሁ ምስኪን ነኝ፡፡  በርግጥ ሚስቴ ደስ ስትሰኝ ማየት ሊያስደስተኝ ይገባል፤ ይህ ማለት ግን እንደዋጋ አድርጌ ልወስደው ሳይሆን መደሰቷን ስለምመርጥላት ስለእርሷ ደስታ ስል ነው፡፡ ስለእኔ በደስታዋ መደሰት ያይደለ፡፡ "ሂድና ውደዳት!"   የሁልጊዜም መርሃችን ልትሆን ይገባል፡፡ እንድትወደን ሳይሆን እንድንወዳት ስንወዳት የምር ትወደናለች፡፡ ስንወድ ከተወዳጁ በምንጠብቀው ነገር መመስረት የለብንም የፍቅራችን መሰረት መመስረት ያለበት ፍቅራችን ላይ እንጅ በሚጠበቅ በሌላ ፍቅርም ሆነ ሌላመሰረት ላይ መሆን የለበትም፡፡ አምላክ እኛን ስለወደድነው አይደለም የወደደን፤ በራሱ ፍቅር ተመስርቶ ወደደን እንጅ፡፡ እኛም በራሳችን ፍቅር ተመስርተን ልንወደው ወይም ስለማይናድ በራሱ ፍቅር ተመስርተን ልንወደው ይገባል፡፡ ሰው ላይ ግን መመስረቻው የሰው ፍቅር አይደለም፤ አያስተማምንም፡፡ በራስ ፍቅር መሠረት ላይ የተተከለች ፍቅር በራስ ይዞታ ላይ እንደተሰራች ቤት ናት፡፡ ማንም መጥቶ አያፈርሳትም፡፡ ወዳኝ ከምንዋደድ  ወድጃት ብንዋደድ ይሻለኛል፡፡ መሰረቱን ራሴ ላይ ራሴ ብይዘው!
Show all...
አቃቢ ርዕስ ሙኤዝ አራጀር ዳፌስሻ ቅሩኤል ኮፋኤል ጅመዝጅ ቁመጅ አአር ቅቅፍት ረንኤል ቃመድ አቅመጅጅ ኦ እግዚእነ ዕቀበኒ እምኩሉ ነገር ሊተ ለገብርከ እገሌ  ........ ገቢር 49 ጊዜ በብር ቀለበት ደግመህ ያዝ
Show all...
ሰላም ለሁላችሁም ዛሬ ትንሽ ስለ ብርሀና አፃፃፍ ላውጋችሁ። በጥንቱ ጊዜ ብርሀና በግዕዝ ሲፃፍ ከላይ ወደታች ይፃፍ ነበር ።ይህም 22 ፊደላት 4ዲቃላ ብቻ የነበሩት ሆኖ ይፃፍ ነበረ ።ከዚያም አባ ፍሬ ምናጦስ ከሳቴ ብርሀን ስድስት ዘር ፊደላት ተጨምሮላቸው 154 በመሆን አ ኡ ኢ ኣ ኤ እ ኦ ፣በ ቡ ቢ ባ......፣ገ ጉ ጊ ጋ....፣ደ ዱ ዲ ዳ፣...በመባል በዝርዝር መፃፍ ተጀመሩ በተጨማሪ ከሀ-ፐ አቀማመጣቸው ተስተካክሎ መፃፍ በተጀመረበት ወቅት እስከ ቅርብ ጊዜ የግዕዝ ፊደላት ከቀን ወደ ግራ ነበረ የሚፃፍ ነበረ ።በተጨማሪ የጥበብ መፅሐፍት ጨምሮ ይህንን አፃፃፍ ተከትለው ይገኛሉ በተጨማሪ በምፃረ ቃልም ይፃፋሉ ለዚህ ብዙ ጊዜ የብርሀና መፅሐፍት ለንባብ ለመረዳት ለማወቅ አስቸጋሪ የሚሆኑት ለዚህም ነው ብዙ ጊዜ ከብርሀና ወደ pdf በመቀየር ስልካላችሁ የነበረው ። @truth00011 ጥያቄ አስተያየት መፅሐፍትም ጥበብም ስፈልጉ በዚህ ታገኙኛላችሁ
Show all...
የእውቀት የጥበብ ፍቱን የሚሰራ ነው ..............ዑራኤሉ ሦስተኛውን አይን ለመክፈት ገቢሩ የድመት የውሻ የድንቢጥ የጉጉት አይናቸውን በአንድነት ደቁሶ በሌት ወፍ ደም ለውሶ ድርሳኑን ደግሞ አይንን መኳል ነው ፍቱን ነው
Show all...
3 አይና
Show all...