ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞ @orthodox1 ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye ማናገር ይችላሉ 🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹 Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝ @orthodox1
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ~~~~~~~~~~~~~~~ ምነው እሱን በሆንኩ ያን የቀኝ ወንበዴ ብመስለው ላ’ንድቀን : ባየው መንገዴ ለመስረቅ አይደለም ንብረት ለመቀማት አልያም ለመዝረፍ ሕይወትን ለማጥፋት በዚያ መንገድማ ከሱስ ብበልጥ እንጂ መች ከእርሱ አንስና እኔን ታውቀኝ የለ … የወንበዴ አለቃ ያ’ጢኣተኞች ዋና ያ … ጸጸት ያዘለ በዚያች የጭንቅ ሠዓት «አስበኝ» እያለ ከመስቀልህ ጥላ ከሥር ስለዋለ ካ’ዳም ቀድሞ ገባ ምሕረት ተቀበለ እኔም እንደ ጥጦስ : ማታዬ እንዲያምር ብትለኝ ምን አለ? … «ከገነት ተጠለል: ዛሬን ከእኔ እደር» 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ : ዛሬን ከእኔ እደር» ደ’ሞ ይህን ተመኘሁ ለንጊኖስን በሆንኩ ያቺን ዕለተ ዓርብ : ቀራንዮ በዋልኩ ለአመጽ አይደለም : ከከአይሁድ ለማበር አልያም ለመውጋት : ያንተን ጎን በጦር በዚያ መንገድማ አንተን ለማሳመም: ማን እኔን መሰለ ስንቴ እንዳቆሰልኩህ … ስንቴ እንደወጋሁህ : እኔን ታወቀኝ የለ! ያ …የጲላጦስ ጭፍራ በመስቀል ላይ ሳለህ በሞት በመከራ በጦሩ ቢወጋህ ሳያዝን ሳይራራ ከቀኝ ጎን አፍስሰህ ውኃው ከደም ጋራ በፍቅርህ ስታስረው ዐይኑን ስታበራ ትዕግስትህን ጎትቶት ባንተ እንደ ተጠራ ምናለ እንደው ’ኔንም … ላንተ ብቻ እንዲያድር : ልቤን ብታበራ 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ሰው ባ’ረገኝ ፣ ያቺንም ምነው በመሰልኳት የቺን አመንዝራ እንደርሷ ላንድ ቀን : ከፊትህ ብጠራ ለዝሙት አይደለም ነፍሴን ለማሳደፍ አልያም ለመርከስ መቅደስክን ለማጉደፍ በዚያ መንገድማ ነውርን በመሸከም : መች ከእርሷ አንሳለሁ ሕግህን በማፍረስ … እኔን ታውቀኝ የለ : ምን እነግርሃለው ያቺን … ድኩም ዘማ በኃጢአቷ ቆስላ በበደሏ ታ’ማ ዓለም ተሰብስቦ ሕይወቷን ሊቀማ እንዲወግሯት ሳትፈርድ ቸርነትህ ቀድማ መሬቱን ስትጭር ድምጽህ ሳይሰማ ነውሯን እንደቀበርክ በከሳሽ ፊት ቆማ ዳግም አትበድዪ : በፍቅር ሂጂ እንዳልካት እንደው የኔንም ነፍስ … ምናለ መልሰህ: እንዲያ በማረካት 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ባ’ረገኝ ፣ ያቺንም ሴት ✍️๏ በአግናጥዮስ 🖊 ሕዳር ካህናተ ሰማይ ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፃፈ ☞ ከምድር ጌጥ ታላቋ ደብረ ሊባኖስ
#like #share #subscribe መድኃኒታችን የምኞታችን ማረፊያ፣ መድኃኔዓለም መድኃኒት ምግብ ልብስና ቤታችን፣ የኑሯችንም መሠረት ትጉህ ኖላዊ ነው ፤ ነቅቶ የሚጠብቅ ከተራራው ወርዶ፣ ከበለስ ለበላች – ላንዷ የሚጨነቅ ከአውሬ እየታደገ ፤ እንዳንመስል ዓለሙን በመስቀል መንበር ላይ፣ አዘጋችቶ ሰጠን – ሥጋውና ደሙን መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያልቀው ምግብ ለተራበው ዓለም ጸጋችን ተገ’ፎ ፣ ተራቁተን ብንርቅ በቁም ሞትን ለብሰን ፣ በለስ አገልድመን –በኃጢዓት ብንደርቅ በልጅነት ሥልጣን ከክብር ሊመልሰን ከሸማኔ ጎድጓድ ፣ ከድንግል ተገኝቶ – ራሱን አለበሰን መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማያረጀው ልብስ ለታረዘው ዓለም ከንቱ ቃል በመስማት ፣ ማረፊያ ስናጣ ከገነት ተሰ’ደን ፣ ከሰማዩ መንግሥት–ወደ ምድር ብንመጣ ተድላና ርስት ሆኖ የምንወርሰው ሀገር መንግስተ ሰማያት፣ ወንጌልና ተስፋ –እርሱ ነው እግዚአብሔር። መድኃኒታችን መድኃኔዓለም የማይፈርስ ጽኑ ቤት ለፈላሲው ዓለም ግጥም መጋቤ ሐዲስ ቴዎድሮስ በለጠ (ዶ/ር) ዜማ ዘ. ዘውዱ ጌታቸው ክራር ዘ. ዘውዱ ጌታቸው መሰንቆ እንዳልካቸው አዱኛ ዋሽንት ኤልያስ ፈቃዱ ድምጽ አጃቢ ዘማሪት መቅደስ ማርዬ ድምጽ ቅጂ ሚክሲንግና ማስተሪንግ ዘጎላ ሬከርድስ
✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_BHX6I-EjDdHv2Mbfsdw/videosእግዚአብሔር ያክብርልን
#like #share #subscribe ሕግጋተ ወንጌል ከፍቅረ ቢጽ ጋራ ፍቅረ እግዚአብሔር አጽና ኦሪትና ወንጌል በሁለቱ ትዕዛዛት ተሰቅለዋልና በባልንጀራህ ላይ በከንቱ አትቆጣ የእግዚአብሔር ሰላም ከቤትህ እንዳይወጣ አድመኝነት ቁጣ ጠብና ክርክር ፀሐይዋ ሳትገባ ትተህ በፍቅር ኑር ወደሴቲቱ አይቶ ልቡ ‘ሚያመነዝር ምኞቱ ኃጢዓት ወልዳ ከሞት ጋር የሚኖር ያለዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ከሰማዩ መንግሥት የለው እድል ፈንታ እውነት ከሆነ አዎን ፡ ካልሆነ አይደለም በል በሰማይም በምድር ፡ ፈጽሞ አትማል ክፉውን በክፉ ፡ ተቃውመህ አትመልስ መልካም የሆነውን በሰው ሁሉ ፊት ያዝ እግዚአብሔርን መምሰል ራስህን አስለምድ ላሳዳጆች ጸልይ ጠላትህን ውደድ የሚረግሙህንም መርቅ እንጂ አትርገም ይህ ነው ሕገ ወንጌል ፡ ልዝብ ቀሊል ሸክም ግጥም መጋቤ ሐዲስ ቴዎድሮስ በለጠ (ዶ/ር) ዜማ ዘ. ዘውዱ ጌታቸው ክራር ዘ. ዘውዱ ጌታቸው መሰንቆ እንዳልካቸው አዱኛ ዋሽንት ኤልያስ ፈቃዱ ድምጽ ቅጂ ሚክሲንግና ማስተሪንግ ዘጎላ ሬከርድስ
We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!