ወርቃማ ንግግሮች
ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና። አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg
Show more16 144Subscribers
+2224 hours
+3607 days
+1 11430 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ከፍርስራሽ ስር የወደቁ በድሮን ተመተው ከህንፃው ስር የተጋደሙ ፍልስጤማዊያንን በመፈለግ ላይ የተሰማሩት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከአንድ ጥግ የ16 አመትን ወጣት አገኙ። ሰውነቱ በደም ተጨማልቆ እስትንፋሱ ተቋርጧል። ከፍነው ለመቅበር እንዲያመቻቸው ወደ ሆስፒታል ሊወስዱት አንከፍክፈው አነሱት። አንድ ሁለት እንደተራመዱ አነስተኛ ደብተር ከኪሱ በኩል ወደቀች። አነሷት። የእለት ተግባሩን የሚመዘገበበት ማስታወሻ ነበረች። ገልጠው ተመለከቱት በእርግጥም ዓይናቸው ያየውን ማመን አቃተው። ለአንድ ሳምንት የፈፀመውን ኃጢያት በደብተሩ ላይ አስፍሯል።
ቅዳሜ:- ዉዱእ ሳላደርግ ተኝቻለሁ ይላል።
ዝቅ አሉ
እሁድ:- በሰዎች ፊት ጮክ ብዬ ስቄያለሁ
ሰኞ:- ወደ ወራሪዋ ጦር የተኮስኩት ኢላማውን ጠብቆ ሲያርፍ በራሴ በመገረም ኩራት ተሰማኝ
ማክሰኞ:- የሌሊት ሰላቴን ስሰግድ ሱጁድና ከሩኩኤን ማስረዘም ሲገባኝ በፍጥነት ነበር የተነሳሁት።
ረቡዕ፡- የጦር አዛዣችን በሰላምታ ቀደመኝ። በአጅር በለጠኝ።
ሐሙስ:- የቀን ዚክሬንና ቂርአቴን ረሳሁ
ጁሙዐ:- በረሱል ላይ 1,000 ሰለዋት መጨረስ ተስኖኝ 700 ላይ ተገታሁ" ይላል በደብተሩ አጂብ ተሰኙ። በእርግጥም በዘመናችን ይህን መሰል ማየታችን ያስገርማል።
ይህ ወጣት ያሳካው ላይ ለመድረስ እኛስ ምን ያህል ዕድሜ ያስፈልገናል? ከዛሬ ለመጀመር አታቅዱምን?! እርሱ 16 አመቱ ነበር። ረህመቱላሂ አለይሂ።
Mahi Mahisho
https://t.me/yesheh_kalidrashid_daewawoch
እውነት /ሀሰት
🖋ትክክለኛው መልስ
ስታገኙ እጅግ ጠቃሚ ስጦታዎች ይሰጣችኋል
👇👇👇👇
1// የሀቅ መመዘኛ የሸሪአ ትምህርትን ነው በእኛ ላይ ደግሞ መማር ግዴታ ነው ?
👍 7
እውነት
ሀሰት
Show all...
ስጦታ 🌱
You’ve been invited to add the folder “ስጦታ 🌱”, which includes 59 chats.
~ አእምሮህን ዘግተህ አትቀበል
{ የሚነገረንን እውነት ትኩረት ሰጥተን) የምንሰማና
በአእምሯችን የምንጠቀም (የምናስብ) ቢሆን ኖሮ ከእሳት ሰዎች ባልሆንን ነበር።} (አል ሙልክ )
‹‹አል-ዐታቢ የተባለው የሻም አገር ገጣሚና ባለቅኔ አንድ ዕለት ወደ ከተማዋ በሚያስገባው ዋና በር ላይ ሆኖ በሰዎች መካከል ይመገባል። ጓደኛው ‹ወይ ጉድህ!! ትንሽ እንኳ እፍረት አይሰማህምን!?› አለው። እርሱም ስማ አንተ በቤትህ ውስጥ ከብቶች እያዩህ ብትበላ ታፍራለህን?› ሲል ጥያቄውን በጥያቄ መለሰለት። ጓደኛውም በከብቶች መካከልማ ከሆንኩ መመገብ አላፍርም አለ። ‹መልካም! እንግዲያውስ እነዚህም ሰዎች ከብቶች እንዴት እንደሆኑ አሳይሃለሁ፥ ትንሽ ጊዜ ብቻ ታገሰኝ አለው፡፡
ከዚያም ብድግ ብሎ ለሰዎቹ ትምህርት መስጠት፣ ምክር መምከር ፣ ታሪክ መተረክና ዱዓ ማድረግ ጀመረ። ሰዎቹም እርሱን ለማዳመጥ ከዚያም ከዚህም ተመሙ። ቦታው ጠቦመጋፋት እስከሚጀምሩም ድረስ በዙ። በዚህ ጊዜ በንግግሩ መካከል እንዲህ አላቸው ከአንድ በላይ በሆነ ሰነድ የደረሰን ዘገባ እንደሚያመለክተው (የነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ሐዲስ ማለቱ ነው።) “በምላሱ ጫፍ የአፍንጫውን ጫፍ መንካት የቻለ ሰው ሁሉ ጀሀነም አይገባም” ተብሏል አላቸው። የዚህ ጊዜ አብዛኛዎቹ ሰዎች ምላሳቸውን እያወጡ መንካት እንደሚችሉና እንደማይችሉ ለማረጋገጥ መሞከር ጀመሩ፡፡ ከዚያም ዘወር አለና ለጓደኛው ‹‹አየህ? እነዚህ ሰዎች አእምሮአቸውን የማይጠቀሙ ከብቶች ናቸው ብዬ አልነገርኩህምን? አለው።››
(ሙሓደራቱ አል-ኡደባእ ገ/31)
ብዙዎቻችን በብዙ ነገሮች ላይ አገናዝበን ፣ አብላልተን ፣ በራሳችን የደረስንበትን ድምዳሜ የመያዝ ልምዱ አለን ለማለት አንችልም። ከዚህ ይልቅ ብዙ የተጮኸለትንና የመናገር ወይም የመጻፍ ዕድል ያገኘውን ነገር በደፈናው የመሸመት ነገር ይቀለናል። ከዚህም የተነሳ በብዙ የሕይወት ጉዳዮቻችን ላይ የምንከተላቸው ሃሳቦች የኛ ሳይሆኑ የሌሎች ናቸው። ይህን የሚያሳየው ስሜቶቻችንን የሚያነሳሳው የሌሎች ሰዎች አባባል መሆኑ ነው። እንዲሁም በዙሪያችን ያለው ማኅበረሰብ የሚወደውና የሚጠላው ነገርም በቀላሉ ይዘውረናል። እንዲያውም በድፍረት እንናገር ከተባለ የአንዳንዶቻችን አእምሮ በርካታ የስሜት ባርነቶችንም ያቀፈ ነው።
ይህን የሚያስረዳን ደግሞ በውስጣችን ያሉት ብዙ ነገሮች ለመጀመሪያ ጊዜ በአጋጣሚ የሰማናቸው፣ ያየናቸው፣ የወረስናቸውና እንድንሆናቸው በሌሎች የተነገሩን፥ ሆነው መገኘታቸው ነው። ሆኖም ግን እነዚህ ነገሮች አብረውን በቆዩ ቁጥር ከስሜቶቻችን ጋር ስለሚዋሃዱ ነገሩን ትክክል ለማድረግ ምክንያቶችን እንፈልግላቸዋለን። ከዚያም የእኛው እናደርጋቸዋለን። ምክንያት የማናገኝለትን ደግሞ በሌላ ከመጠየቅም ሆነ ሌላን ሰው ከመጠየቅ እንሸሻለን። በዚህ መንገድ እኛው ጋር እድሜያቸውን ያስረዘሙና ሽግግራቸውን ያስቀጠሉ የመፈተሸ እድል ያላገኙ በርካታ ማንነቶች እንዳሉን እሙን ነው።
እንደሚታወቀው አንድን ሰው ትልቅ የሚያደርገው በቃል የሸመደደው እውቀት ብዛትና የመረጃ ማከማቻ መሆኑ አይደለም። ያ መልካም ቢሆንም ብቻውን ግን በቂ አይደለም። ይልቁንም ትልቅነት እውነትን ፈላጊ፣ ፈታሽና ነገሮችን በጥልቀት የማየት ልምምድ ነው። ይሁንና ብዙዎቻችን ያደግንበት ማኅበረሰብ በብዙ ነገሮች ላይ “ይህን ተዉት፥ ያንን ያዙት ማለት የሚያበዛ በመሆኑ የሰጠው ጥቅም ሊኖር ቢችልም፥ ንቃተ ሕሊናችን ከፍታውን እንዳያገኝ እንቅፋት ሆኖታል።
ከዚህም የተነሳ አንድን ነገር ከመገንዘባችን በፊት የሌሎችን ሃሳብ በደፈናው መቅዳትን እንመርጣለን። ይህ ደግሞ በሕይወት እውነታዎች ላይ ግልብ ዕይታ እንዲኖረን ወይም በሌሎች ብቻ እንድንመራ፥ እልፍም ሲል የመሃይም ማጎብደድ እንድናጎበድድ ያደርገናል።
የዚህ ዋና ምክንያቱ ባሕላችን ነው። ገና ልጆች ሳለን ወላጆቻችን የአንድ አመለካከት እስረኛ አድርገው የመቅረጽ ሚናን እንዲድጫወቱ ስለሚያበረታታ ነው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የበላይነት እንዳላቸው የሚታሰቡት ማኅበረሰቦች ወይም ግለሰቦች የሚደግፉትንና የሚጮሁለትን ነገር በጭፍኑ የመከተል አባዜያችን ነው።
እርግጥ በወላጆች መቀረጽም ሆነ የሌሎችን ዕይታ መውሰዱ በራሱ ችግር የለውም። ምክንያቱም የነገሩ ትክክለኝነት እንጅ እውነት የትላንት ወይም የዛሬ የሚባል ነገር የለውም። ነገር ግን ችግር የሚሆነው እነርሱ ያመኑበት እንጅ በራሱ ትክክል ያልሆነ በሚሆንበት ጊዜ ነው።
አእምሮን በሚገባ አለመጠቀም የመጀመሪያ ምልክቱ የሌሎችን ዕይታ ለመስማት ፍቃደኛ የማይሆኑ ጠባብ ሰዎችን መፍጠሩ ነው። በታሪክ ውስጥ በአስተሳሰብ መስመር (በመዝሀቦች) መካከል ያለውን ልዩነት በማጉላት በታላቁ በኒ ኡመያ መስጊድ ውስጥ አንድ ወቅት ሶላትን አራት ጊዜ የተለያየ የአስተሳሰብ መስመር ባላቸው ኢማሞች ተሰግዶ እንደነበር ታሪክ ያስታውሳል ። እውነቱን ለመናገር የትኛውም ዓይነት ጭፍንነት የሚገነውና ጽንፍ የሚይዘው አእምሮን ካለመጠቀምና ከማመዛዘን እጥረት ነው።
~ ሰው ምክንያታዊነቱን ሲዘጋ የለመደውን ወይም የወረሰውን ነገር በመደጋገም ግትር ይሆናል። የኔ ሃሳብ ብቻ ትክክል ነው ብሎ መከራከር የተከላካይነት ጠባይን ያመጣል። ቡድንተኝነቱን በሚያጠናክሩ ነገሮች ላይ ብቻ ያተኩራል። የሚያምንበትን ነገር በኃይል ለማሳካትም ይሞከራል። ከዚህም የተነሳ ለበርካታ ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ጉዳቶች ተጋላጭ ይሆናል። የሆነ ሆኖ ግን ታላቁ ቁርኣን የትኛውንም ነገር ለመገንዘብ አእምሮን መጠቀም እንደሚገባና ሌሎችንም በጭፍኑ መከተል ከመስመር እንደሚያወጣ በብዙ አንቀጾቹ ላይ በግልጽ አስፍሯል። ለአብነትም የሚከተሉትን እንመልከት…
وَقَالُوا لَوْ كُنَّا نَسْمَعُ أَوْ نَعْقِلُ مَا كُنَّا فِي أَصْبِ السَّعِيرِ
"የምንሰማ፥ ወይም የምናስብ፥ በነበርንም ኖሮ በነዳጅ እሳት ጓዶች ውስጥ ባልኾን ነበር ይላሉ።"
(አል-ሙልክ፡ 10)
👍 12❤ 4🥰 2🤔 2
ይህ ግሩፕ የሸኻችንን ሸኽ ያሲን ሙሳን
ለማሳከም የተከፈተ ነው
በዚህ በተከበር ወር ከኸይር ስራ ልንሰላች
አይገባም ይህ እንደ ተራ ነገር ቆጥረነው
scroll አድርገን ልናልፈው ፈፅሞ ተገቢ አይደለም
ተቀላቀሉ 👇👇👇
t.me/+FCoJ8Aqxga1mZmI0
t.me/+FCoJ8Aqxga1mZmI0
ሸይኽ ያሲን ሙሳን እናሳክማቸው
ይህ ግሩፕ የሸኻችንን ሸኽ ያሲን ሙሳን ለማሳከም የተከፈተ ነው ሸር አድ በማድረግ የቻልነውን እየነያን እናሳክማቸው
https://t.me/+FCoJ8Aqxga1mZmI0Seid mohammed nur and redwan kamil CBE - 1000613590769 Awash bank 014251311288500
Repost from ትዳር እና ኢስላም 🌷🌹🥀
بسم الله الرحمن الرحيم
{ وَٱلۡعَصۡرِ }
{ إِنَّ ٱلۡإِنسَـٰنَ لَفِی خُسۡرٍ }
{ إِلَّا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّـٰلِحَـٰتِ وَتَوَاصَوۡا۟ بِٱلۡحَقِّ وَتَوَاصَوۡا۟ بِٱلصَّبۡرِ }
[Surah Al-asr ]
ሰለፎች ተገናኝተው ሲለያዩ ከላይ ያለው ማለትም
Surah Al-asr አንደኛው ላንደኛው በየተራ ይቀሩት ነበር ።
ግን ዛሬ ላይ ይህን የሰለፍች መንገድየተረሳ
የተዘነጋ ይመስላል
ከኛ ውስጥ አንዳችን ለጓደኛችን ይህን ሱራ
አስቁመን ብንቀራለት ስቆብን ሁላ ሊያልፍ ይችላል
አልያም ድምፅ ያምራል ብሎ ያሾፍብናል
ለዚህ ሁሉ ምክንያት ግን👇
1/ ዲናዊ የሆኑ እውቀቶችን ካለመገንዘብ
2/ ለቁርአን ያለን ክብር የወረደ ስለመሆኑ
3/ የቀልባችን መድረቅ
4/ጓደኝነታችን ለአላህ ብሎ የተዋደዱ ከሚባሉት
ውስጥ የማይመደብ እና ለጥቅም የተገናኘን ስለመሆኑ እንዲሁ ለዱኒያዊ አላማ የተገናኝን
በመሆኑ ነው
ሼር ሼር
ቻናል t.me/tdar_ina_islam ተቀላቀሉ
👍 1
በተፈጥሮ እንግዳ ቸኮላ ነው በር በር ነው የሚያየው ከመቀመጣቸው ይልቅ ለመሄድ ለመሰናበት ይቸኩላሉ።
ረመዷናችን እንግዲህ እንዲሁ ነው። እንግዶቻችን እንደቸኮሉ ነው ነፍሶቻችን አንድሱ ፣ ቁርዓን አንብቡ ፣ ጉድለቶቻችሁን ሙሉ ፣ ስግደታችሁን አስረዝሙ ፣ የሱና ሰላትን ስገዱ ፣ ዱዓአችሁንም በማብዛት ፣ ነፍሶቻችሁን በማጣት የረመዳንን ህይወት ለልባችሁ አድርጉ።
ዛሬ ረመዷን ⑦ ነው።
👍 16
「𑁍📲አዲስ አፕ | ተለቀቀ 𑁍」
╭┈⟢🎁የረመዷን ስጦታ
│
│❏መጃሊሱ ሸህሪ ረመዷን
│
│ሊሸይኺል ዑሰይሚን
╰─────────────────╯
╭🎙የደርሱ አቅራቢ:-
├─┈┈┈
│✑አቡ ዐብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
╰──────────────
╭⧿⧿⛉
├⎙አሁኑኑ ዳውንሎድ በማድረግ │ይጠቀሙ!
│
┝ለሌሎችም ሼር በማድረግ የአጅሩ │ተቋዳሽ ይሁኑ!
╰───────────
╭╼╺╼╺╼╺╼╺╼ ╺╼╺╼
┢⎘ ለመሰል ስራዎች ይቀላቀላሉን
┃
┡🖇http://t.me/Yusuf_App1
╰─╼╺╼╺╼╺╼╺╼╺╼╺╼
👍 2
Sign in and get access to detailed information
We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!