ወንጌል ለዓለም🔈🌎
''And he said to them, Go into all the world, and preach the gospel to every creature. Mark 16:-15 እንዲህም አላቸው ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ማርቆስ 16:-15 የተመሠረተበት ቀን (ግንቦት 08/09/2012) ለአስተያየት @Geruuu ላይ inbox.
إظهار المزيد5 435
المشتركون
-324 ساعات
-137 أيام
-4530 أيام
أرشيف المشاركات
ተቀሰቀሰ _በረከት ተስፋዬ
እኔ ህያው ነኝ
እኔ ህያው ነኝ
ቀድሞ ሙት ነበርኩኝ
ዛሬ ህያው ነኝ
ሞት አሸንፈው የሄዱት እላይ
እንደ ጌታቸው ሌላ አለ ወይ
መውጊያውን ሰብሮ ሞትን ድል ነሳ
በሶስተኛው ቀን ጌታ ተነሳ
ቀድሞ በሞተልኝ
ዛሬ ህያው ነኝ
ቀድሞ በተነሳልኝ
ህይወት አገኘሁኝ
ቦታው የእኔ ነው የሞተበት
አሁን ያኖረኝ የሱ ህይወት
በምህረት አይቶኝ ልቡ ቢሳሳ
ሞቴን ሞተና ይዞኝ ተነሳ
ፍፁም ሳይሳሳ ለክቡር ነፍሱ
ትንሳኤ ለኔ ሞቴን ሞተ እሱ
ከሙታን ሰፈር እኔን ሊያወጣ
የሞቴን ፅዋ ብቻውን ጠጣ
ቀድሞ በሞተልኝ
ዛሬ ህያው ነኝ
ቀድሞ በተነሳልኝ
ህይወት አገኘሁኝ
ሙቱ መንፈሴ ሆነ ህያው
እኔም ተነሳሁ በትንሳኤው
ሞቴ ህይወቱን ስለለበሰ
በድን ህይወቴ ተቀሰቀሰ
በድን ህይወቴ ተቀሰቀሰ
ትንሳኤው የእኔ ነው
ቦታው የእኔ ነው የሞተበት
አሁን ያኖረኝ የሱ ህይወት
በምህረት አይቶኝ ልቡ ቢሳሳ
ሞቴን ሞተና ይዞኝ ተነሳ
ፍፁም ሳይሳሳ ለክቡር ነፍሱ
ትንሳኤ ለኔ ሞቴን ሞተ እሱ
ከሙታን ሰፈር እኔን ሊያወጣ
የሞቴን ፅዋ ብቻውን ጠጣ
ቀድሞ በሞተልኝ
ዛሬ ህያው ነኝ
ቀድሞ በተነሳልኝ
ህይወት አገኘሁኝ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
https://t.me/joinchat/AAAAAEc7LsLkjQ-Xk3eBOA
ለኔ ነው
ለምለም ማታ - New Clip
ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር አድርጉ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
https://t.me/joinchat/AAAAAEc7LsLkjQ-Xk3eBOA
Repost from ቴዎ ፍሎስ theophilus
የበርጤሜዎስ ጩኸት ክፍል 4
#ይጠራሃል #ብለዉ #ጠሩት
#መጠራታችሁን #ተመልከቱ #ማን #እንደነበራችሁ
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 22/01/2016
Repost from ቴዎ ፍሎስ theophilus
#የበርጤሜዎስ #ጩኸት #ክፍል 2
#ለአንተ #ይቻልሃልና
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 15 01 2016
Repost from ቴዎ ፍሎስ theophilus
የበርጤሜዎስ ጩኸት ክፍል 1
#ኢየሱስ እንደሆነ #በሰማ ጊዜ ልመናዉን ቀየረ
#ከፀደቀ #መንፈሰ
"Rebuni"
bereket megrsa
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
https://t.me/joinchat/AAAAAEc7LsLkjQ-Xk3eBOA
"ደሙን ለኔ አፍስሶ"
ኮብልላ ነበረች ነፍሴ ከእግዚአብሔር መንገድ
በጣም የበደልኩኝ ኀጢአተኛም ነበርኩ
ግን አዳኜ ከላይ ፍቅሩን ሰጠኝ ሰላም
ልጁን ለእኔ ልኮ አወጣኝ
አዝ፦ ደሙን ለእኔ አፍሶ አዳነኝ (፪x)
የማልረባም ብሆን አምላኬን የማላውቅ
ልጁ ለእኔ ወርዶ አወጣኝ
ተስፋ ቢስ ነበርኩኝ ሊያወጣኝ ሲመጣ
ግን እርሱ ነገረኝ ነጻ እንደምወጣ
ከዚያማ አነሳና ክብሩን አቀናጀኝ
ልጁን ለእኔ ልኮ አወጣኝ
አዝ፦ ደሙን ለእኔ አፍሶ አዳነኝ (፪x)
የማልረባም ብሆን አምላኬን የማላውቅ
ልጁ ለእኔ ወርዶ አወጣኝ
ልቤን ደስ ይለዋል ከመረጥኩት ወዲህ
ከማዕበሉ አሁን ወዴርሱ ሸሻለሁ
ክንዱን ከተደገፍኩ አልፈራም መከራን
ልጁን ለእኔ ልኮ አወጣኝ
አዝ፦ ደሙን ለእኔ አፍሶ አዳነኝ (፪x)
የማልረባም ብሆን አምላኬን የማላውቅ
ልጁ ለእኔ ወርዶ አወጣኝ
ሰማያዊ ደስታን ሰላምን ከሰጠኝ
ጌታ ሆይ ሕይወቴን ለአንተ ሰጣለሁኝ
እንግዲህ እጄን እየያዝክ ከአንተም ጋር አቁመኝ
ልጁን ለእኔ ልኮ አወጣኝ
አዝ፦ ደሙን ለእኔ አፍሶ አዳነኝ (፪x)
የማልረባም ብሆን አምላኬን የማላውቅ
ልጁ ለእኔ ወርዶ አወጣኝ
አዲሱ ወርቁ-||-Easter Song
🕐5:07Min-||-💾-3:4MB
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
https://t.me/joinchat/AAAAAEc7LsLkjQ-Xk3eBOA
አራት መነኩሴዎች ከሚኖሩበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ ጉዞን ይጀምራሉ፣ አርፍደዉ ስለተነሱ የፈለጉበት ቦታ በጊዜ ስላልደረሱ፣ እዛዉ በደረሱበት ቦታ አረፍ ብለዉ ለመሄድ ይወስናሉ፡ ሰዓቱም ስለመሸ ምሽቱንም ባሉበት ቦታ ድንኳን ይዘዉ ስለነበር ድንኳናቸዉ ዘረጉ። ከመተኛታቸዉ በፊት ለመፀለይ ይስማማሉ ከመፀለያችን በፊት አንድ ህግ እናዉጣ አለ አንደኛው መነኩሴ ይህም ህግ ሁላችንም የምንፀልየዉ በዉስጣችን ነዉ ምን አይነት ነገር ቢፈጠር ማዉራት አይፈቀድም አለ፣ የቀሩት ሁሉም በወጣዉ ህግ ተስማምተዉ በዉስጣቸዉ ድምፅ ሳያሰሙ መፀለይ ይጀምራሉ። በጣም ስለጨለመ በድንኳናቸዉ ዉስጥ ሻማ ለኩሰዉ ነበር የሚፀልዮት። ትንሽ እንደቆዮም ከዉጪ በመጣ ንፍስ እየበራ የነበረዉ ሻማ ያጠፍዋዉ።
አንደኛዉ መነኩሴ ከመካከላቸዉ ወይኔ ሻማዉ እኮ ጠፍ አለ፣ ሁለኛዉ መነኩሴ ቀበል አድርጎ በፀጥታ ነዉ መፀለይ ያለብን አለ፣ሶስተኛዉ ደግሞ እባካችሁ ዝም እንበል ያወጣነዉን ህግ እየጣሳችሁ እኮ ነዉ አለ፣ አራተኛዉ መነኩሴ በመጀመሪያ ፈገግ ብሎ እኔ ብቻ ነኝ ያላወራሁት አለ።
ይህንን ታሪክ ያነሳሁት አንድ መልእክት ለማስተላለፍ ነዉ።
በዚህን ጊዜ የአገልጋዮችን ስህተት ወደ social media ይዞ መጥቶ መተቸት የተለመደ ነዉ፣ በአስተምህሮ ወይም በልምምድ ስህተት ዉስጥ ያለን ሰዉ እንድንቃመዉ መፅሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ያስተምረናል 👉ፊል 3:2 ማቴ 16፡12 ገላ 5:5_11_12 1ዮሐ 2:22...... መፅሐፍ ቅዱስ ስህተትን እንድንቃወም ብቻ ሳይሆን የሚያስተምረን ስህተትን ስንቃወም አስቀድመን ማወቅ ስላለብን ነገር እንደ መመሪያ ያስተምረናል። ነገሩ ስህተት መሆኑን ብቻ ማወቅ ሳይሆን ያንን ስህተት የምናቀናበትን መንገድ አስቀድመን ማወቅ መቻል አለብን። ምክንያቱም በአሁን ሰዓት ስህተት የሆነን ነገር ለመቃወም በተሳሳተ መንገድ እየተቃወሙ ያሉ እየበዙ ስለመጡ። በቤተክርስቲያን ዉስጥ በአስተምህሮም ሆነ በልምምድ በስህተት መንገድ ያሉ አገልጋዮች ከመፅሐፍ ቅዱስ መምሪያ ዉጪ ስለሆኑ ነዉ። ከመመሪያው ዉጪ ሆነዉ የተሳሳቱትን የምንመልሳቸዉ በመመሪያዉ ነዉ። ስለዚህ የሳቱትን ለመመለስ የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያን ልንከተል ይገባል። ለእኛ ሲባል የሚሻር የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያም ሆነ ህግ የለም። ለምሳሌ መፅሐፍ ቅዱስ " ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" ይላል(1ኛ ጴጥ4:11) ይህ ለሁሉም ሰዉ የሚሰራ መመሪያ ነዉ። የተሳሳተን ሰዉ በመሳደብ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል በመናገር ነዉ ልናቀናዉ የምንችለዉ። እኛ ስንሳደብ የእኛ ስድብ ልክ ስለማይሆን።" ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።" ይላል መፅሐፍ ቅዱስ።እግዚአብሔር የአንደበታችንን ቃል ብቻ ሳይሆን የልባችንን motive (ምክንያት) የሚያይ አምላክ ነዉ የተሳሳተን ሰዉ ስንቃወም እርሱን ለመመለስና ገንዘብ ለማድረግ እንዲሁም በእዛ ስህተት መንገድ የሚሄዱትን ምዕመናንን ለማቅናት እንጂ የተሳሳቱትን ፈፅሞ ለመስበርና ለማጥፍት መሆን የለበትም " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የወደቁ አይነሡምን? የሳተስ አይመለስምን? "( ኤር 8:4) ይላል የሳቱት ቢመለሱ እኛ ለእነርሱ የሚመለስ ልብ እንዳለን እናረጋግጥ። ተሳስታችኋል የተባሉ ከስህተታቸዉ የተመለሱ እዉነተኛዉን አስተምህሮ የሚያስተምራቸዉ አጥተዉ ግራ በመጋባት ዉስጥ ያሉ በርካታ ሰዎች አሉ።😔 ስህተትን መናገር ብቻ ሳይሆን ከስህተቱ ለተመለሰ ሰዉ በፍቅር የሚያቅፍ እጅ ሊኖረን ይገባል።ለዚህ ደግሞ እዉነትን በፍቅር ልንይዘዉ ይገባል " ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን"(ኤፌ4:15) ስህተቱን ለመናገር እንደረበታነዉ ሁሉ እዉነተኛዉን አስተምህሮ ለማስተማር መትጋት አለብን። " እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። "(ዮሐ8:32) በስህተት የተያዘን ሰዉ ነፃ የምናወጣዉ በእዉነት ነዉ። 1+1 ሶስት አይደለም ፥4ትም አይደለም፥10ም አይደለም እያልክ ያልሆነዉን ከምትነግረኝ የሆነዉን 2 ብትነግረኝ ያልሆነዉን እኔ በቀላሉ እለያለሁ። አማኞች ስህተት የሆነዉ ነገር እንዲለዩ እዉነተኛዉን የእግዚአብሔርን ቃል እናስተምራቸዉ።
ይህ ከላይ የገለፅኩላችሁ ስህተትን ስንቃወም መፅሐፍ ቅዱስ ከሚሰጠን መመሪያዎች በጥቂቱ ናቸዉ።
መጀመሪያ ወዳነሳሁላችሁ ታሪክ ልመላሳችሁ፣ አራቱም መነኩሴዎች ያወጡትን ህግ ሽረዋል። አራቱም የሻሩት ልክ በሚመስል ምክንያት ነዉ፣ አንደኛዉ የሻማ መጥፍቱን እንዲያዉቁ ተናገረ ፥ሁለተኛው ደግሞ የወጣዉን ህግ ለተናገረዉ ሰዉ ለማስታወስ ተናገረ፥ሶስተኛዉ ደግሞ ሁለቱም ፀጥ እንዲሉ እንዳይናገሩ ተናገራቸዉ፥አራተኛዉ በስተመጨረሻ እኔ ብቻ አልተናገርኩም ብሎ አለመናገሩን ተናገረና ህጉን አፈረሰ።
ተወዳጆች የእግዚአብሔር ቃል የሁላችንም መመሪያ ነዉ። አንድ አገልጋይ ከተሳሳተ ልንመልሰዉ የሚገባ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ አሳማኝ በሚመስል ምክንያት ግን ስህተት በሆነ መንገድ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ህግ በመሻር መሆን የለበትም።
ጌታ ኢየሱስ ታልፎ በሚሰጥበት ምሽት
ይሁዳ ጭፍሮችንና ከካህናት አለቆች ከፈሪሳውያንም ከሎሌዎችን ጋር በችቦና በፋና በጋሻ ጦር ሆኖ ወደ ኢየሱስ መጣ
ኢየሱስም የሚመጣበትን ሁሉ አውቆ ወጣና ማንን ትፈልጋላችሁ አላቸው። የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ። እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር።እንግዲህ። እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ወደቁ።ደግሞም። ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም። የናዝሬቱን ኢየሱስን አሉት።
ኢየሱስ መልሶ። እኔ ነኝ አልኋችሁ፤ እንግዲህ እኔን ትፈልጉ እንደ ሆናችሁ እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው አለ፤ይህም። ከእነዚህ ከሰጠኸኝ አንዱን ስንኳ አላጠፋሁም ያለው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ስምዖን ጴጥሮስም ሰይፍ ስለ ነበረው መዘዘው፥ የሊቀ ካህናቱንም ባርያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠ፤ የባርያውም ስም ማልኮስ ነበረ።ኢየሱስም ጴጥሮስን። ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው፤ አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣትምን? አለው።
(ዮሐ 18_1_11) ጴጥሮስ የማልኮስን ጆሮ ለመቁረጥ በቂ ምክንያት ነዉ ያለዉ። ግን ልክ አልለበረም። ኢየሱስ ጎበዝ ብሎ አላበረታታዉም ወዲያዉኑ ሰይፍህን ወደ ሰገባዉ ክተት ነዉ ያለዉ። ተወዳጆች ከእኛ ልክ ካልሆነ አሳማኝ ከሚመስል ምክንያት ይልቅ የእግዚአብሔር ቃል መመሪያ ሁሌም ልክ ነዉ።
ክፍል 2 ይቀጥላል ..
#ከፀደቀ #መንፈሰ
አንድ ሰዉ ስለ እግዚአብሔር ፀጋና፣ፅድቅ ተምሮ ታዲያ ሀጢአትን ብሰራ ምን ችግር አለዉ? ብሎ ካሰበ ትምህርቱ በፍፁም አልገባዉም። በክርስቶስ መፅደቃችን በገባን ልክ ራሳችንን ለፅድቅ ተገዢዎች አድርገን ለማቅረብ እንተጋለን።
#ከፀደቀ #መንፈሰ
Photo unavailableShow in Telegram
ዶ/ር መለሰ ወጉ
ከ50 በላይ ቤተ ክርስቲያናትን ተክሏል!
ከ60 ዓመት በላይ ወንጌልን አገልግሏል!
ከ30 በላይ መጻሕፍት ጽፎአል!
ከ30 በላይ መለስተኛ መጻሕፍት ዐሳትሞአል!
ከ200 በላይ "የሕይወት መስታውት"
መጽሔት ጽሑፎች!(በመጽሔቶቹ የታተሙት ጽሑፎች ሁሉ የእርሱ ናቸው)::
ከ400 በላይ በካሴትና በሲዲ የተዘጋጁ ትምህርቶች አስተላልፎአል!
" በመልካም የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች፥ ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 5:17)
#አሳዛኝ_ዜና😭😭
በተለያዩ ዝማሬዎቹ የተባረክንበት ዘማሪ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ አለም በሞት ተለይቶ ወደሚወደው ጌታ ሄዷል። የሄደው ወደጌታ ቢሆንም የሚወዱት ሲለይ ያሳዝናልና ለወዳጅ ዘመዶቹ ፣ ለቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን....
" እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤"
(ወደ ቲቶ 3: 5)
Photo unavailableShow in Telegram
ፓስተር ቴዲ ሆኗልበብዙ ዝማሬዎቹ የምናውቀው እንዲሁም በቤተክርስቲያን ውስጥ በዝማሬዎቹ አማኞችን የሚባርከው ዘማሪ ቴዲ ታደሰ መጋቢ ወይም ፓስተር ቴድሮስ ታደስ ተብሎ ተሹሞል። እግዚአብሔር በፊቱ የተሳካ የአገልግሎት ዘመን እንዲሰጠው እንመኛለ። መጋቢ ቴዲ እንኳን ደስ አለህ
Repost from The power of Holy Spirt
#ያላመኑ_ሰዎች_መንፈስ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው ሕብረት አንጻር ሙት እንጂ ፍጽሞ ሙት አይደሉም
በማያመን ሰው ውስጥ ያለው የሰው መንፈስ በክርስቶስ ሲያምን ሕያው የሚሆን ሙት አይደለም ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የማያምኑ ሰዎች ሕያው የሆነ ሆኖም ዓመጸኛ መንፈስ እንዳላቸው መናገሩ ግልጽ ነው፡።
ለምሳሌ የሐሴቦንን ንጉሥ የሴዋንን መንፈስ "እግዚአብሔር አደንድኖት " ነበር (ዘዳ 2:30) ወይም ናቡከደነፆር መንፈሱ ደንድኖ ልቡ በእብሪት ተሞልቶ ነበር(ዳነ 5:20) ወይም ታማኝ ያልሆኑት የእስራኤል ሕዝብ እልከኞችና ዓመጸኞች ከመሆናቸው የተነሳ "መንፈሳቸው በእግዚአብሔር የማይታመን ነበር " መዝሙር 78:8) ሐዋርያው ጳውሎስ "መንፈሳችሁ ከጽድቅ የተነሳ ሕያው ነው "(ሮሜ 8:10) ስል "ለእግዚአብሔር ሕያው " መሆንን ለመግለጽ ነው እንጂ መንፈሳችን በፊት ፈጽመ "ሙት" ነበር ለማለት አይደለም በእርግጥ መንፈሳችን ከእግዚአብሔር ጋር ምንም ዓይነት ኀብረት ስለሌለው በዚያ አንጻር ሙት ነበር። በተመሳሳይ ሁኔታ ሁላችንም በሁለንተናዊው ሰውነታችን በበደላችን በኃጢአታችን ምክንያት ሙታን ነበርን (ኤፌ 2:1) ነገር ግን በክርስቶስ ኢየሱስ ለእግዚአብሔር ሕያዋን ሆነናል ስለዚህ ለኀጢአት ሞተን ለእግዚአብሔር ሕያዋን እንደሆንን ራሳችንን እንቆጥራለን ሮሜ 6:11 :;
አንዱ የሰውነታችን ክፍል (መንፈስ )ተብሎ የሚጠራው) ብቻ አይደለም ሕያው የሆነው እኛ በሁለንተናችን በክርስቶስ "ዐዲስ ፍጥረት "ነን 2ቆሮ 5:17።
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ፃዲቅ ክፍል 5
#ፅድቁ #ተቆጥሮልኝ #ፃድቅ #ሆንኩኝ
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 20:07:2016
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 4
#ፅድቅን #የተከተሉ #እስራኤላዉያን
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 17_07_2016
❤🤔🤔🤔ወዮልኝ ❤🤔🤔
እኔ
ወንጌልን ላረሳ ኪዳን የገባሁት
ሞትና ትንሳው አውጃለሁ ያልኩት
ከደሙ ጠጥቼ ስጋው የቆረስኩት
እኛ
ከበላን እንጀራህ ከጠጣን ፅዋህን
ልናወራው ሞትህ የመስቀል ፍቅርህን
ነበረ ኪዳኑ ልናውጅ ድምፅህን
በጫት በሲጋራ በሀሺሽ ተይዞ
ወንድሙን በመጥላት በቂም ተመርዞ
ኑሮ ለመረረው ግራ ገብቶት ላለው
ችላ አትበለው ለርሱም ጥሪ አለው
በልባችን አምነን በአፋችን መስክረን
በሞት ለሚነዱት የህይወት ሽታ ሆነን
እንድንኖርለት ነው ጌታ የነገረን
ታያ ምን ሆነንነው ኧረ ምን ነክቶን ነው
ከመመስከር ይልቅ ዝምታ የመረጥነው
ከወንጌሉ በላይ ክብር ያስቀደምነው
የምስራች ትተን ለስጋ ከኖርን
ከመመስከር ይልቅ ካስቀደምን ክብር
ወዮ እንበል ያኔ ወገን ከምድር
የወንድሜ መሞት በእሳት መግባቱ
እኔው ካልነገርኩት ሳይመጣ ንዳዱ
በፍፁም አይቀርም በሲዖል መንደዱ
በስጋ የወለደኝ ያ ውዱ አባቴ
አምጣ የወለደች ያቺ ውብ እናቴ
የተሸከመችኝ የኔዋ እህቴ
ከልቡ የመከረኝ መካሪው ወንድሜ
ለሲዖል ሲጣሉ ኧረ እንዴት ያስችለኝ
ማረፍያ የሆነ መድሀኒት እያለኝ
አዋጅ ብዬ ልውጣ እነሱም ያምልጡ
ለጥልቁ ያ ገዢ ታልፈው ሳይሰጡ
ወደ እቅፉ ይግቡ ከደሙ ይጠጡ
በወንጌል አላፍርም ብለህ የገባኸው
ልትሰብከው በአፈህ ኪዳን ያደረከው
ወዮ ያኔ ጉድህ እሱን ችላ ካልከው
ተነስ ተነሽ ተነስ ተነሽ
አብረን እንነሳ
የቲጂ አቤኒ
የእናቱ ብሩክ
ቆየት ያሉ እና አዳዲስ የአምልኮ መዝሙሮች ይፈልጋሉ? እንግዲያስ አድሱን የአምልኮ መዝሙሮች የምገኙበትን ቻናላችንን ይቀላቀሉን👇👇
https://t.me/+Kr8zEBYUAR4yNjA8
አሁኑኑ ይቀላቀሉን ከኛ ጋር ጌታን ያምልኩ
🎶 የአምልኮ መዝሙሮችን ለማግኘት🎶
መንፈሳዊ ግጥም ለማግኘት✅
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 3
#ፅድቃችን #በእግዚአብሔር #ፊት
እግዚአብሔር #ጻዲቅ ነዉ
ማነዉ በፊቱ #የሚቆመዉ?
ቀን 2_07_2016
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 2
የእኛ ፅድቅ በእግዚአብሔር ፊት
#ለመፅደቅ #ፅድቅን #ያዋጣ #የለም
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 28_06_2016
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 1
የእግዚአብሔር ፅድቅ ክርስቶስ አጸደቀን
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 24_06_2016
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 1
የእግዚአብሔር ፅድቅ ክርስቶስ አጸደቀን
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 24_06_2016
Photo unavailableShow in Telegram
የብዙሀኑን መልእክት እና ኮሜንት አይተናል። በቅንነት የመለሳችሁ እግዚአብሔር ይባርካቹ እያልን የተሳለቃችሁ ደግሞ 1ሳሙ 2:12-17 ጋብዘናቹሀል። መዝሞሩ መፅሀፍ ቅዱሳዊ ሲሆን ሀሳብም ከታች ባለው የቃል ክፍል ጋር የተያያዘ ነው።
“ደግሞም ስቡን ሳያቃጥሉ የካህኑ ሎሌ መጥቶ የሚሠዋውን ሰው፦ ጥሬውን እንጂ የተቀቀለውን ሥጋ ከአንተ አይወስድምና እጠብስለት ዘንድ ለካህኑ ሥጋ ስጠኝ ይለው ነበር።”
— 1ኛ ሳሙኤል 2፥15