cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
34 906
المشتركون
-224 ساعات
+1697 أيام
+99230 أيام
أرشيف المشاركات
በጉራጊኛ ደርሥ ተለቋል። ጉራጊኛ ተናጋሪዎች ገብታችሁ ኮምኩሙ፦ https://t.me/wahidcomguragiga/36
إظهار الكل...
፨ "ኸሚሥ" خَمِيس ማለት "አምስት" ማለት ሲሆን "ሐሙስ" ማለት ነው፥ "ሐሙስ" ማለት "አምሽት" "አምስት" ማለት ነው። ፨ "ጁሙዓህ" جُمُعَة ማለት "ስብስብ" ማለት ሲሆን "ዓርብ" ማለት ነው፥ "ዓርብ" የሚለው "ረበዐ" ማለትም "ሰበሰበ" ማለት ሲሆን "መሰብሰቢያ" "ስድስተኛ" ማለት ነው። አሏህ ለመላእክት፦ "እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ፥ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ" ብሎ በነገራቸው መሠረት ሰውን በስድስተኛው ቀን ፈጠረ፦ 38፥71 ጌታህ ለመላእክት «እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ 2፥30 ጌታህ ለመላእክት፡- «እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ! وَإِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي جَاعِلٌ فِي الْأَرْضِ خَلِيفَةً ተፍሢር ኢብኑ ከሲር 7፥54 "እነዚህ ስድስት ቀናት አሐድ፣ ኢስነይን፣ ሱላሳእ፣ አርቢዓእ፣ ኸሚሥ፣ ጁሙዓህ ናቸው። ፍጥረት ሁሉ በጁሙዓህ ቀን ተሰብስቦ ነበር፥ በዚያ ቀን አደም ተፈጠረ። والستة الأيام هي : الأحد ، والاثنين ، والثلاثاء ، والأربعاء ، والخميس ، والجمعة - وفيه اجتمع الخلق كله ، وفيه خلق آدم. ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 4, ሐዲስ 1 አቡ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "መልካም ቀን ፀሐይ ከወጣችበት የጁሙዓህ ቀን ነው፥ በዚያ ቀን አደም ተፈጠረ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ خَيْرُ يَوْمٍ طَلَعَتْ فِيهِ الشَّمْسُ يَوْمُ الْجُمُعَةِ فِيهِ خُلِقَ آدَمُ ለመሆኑ ባይብል ላይ ፈጣሪ ሰማይን እና ምድርን የፈጠረው በየትኛው ቀን ነው ይላል? ዘፍጥረት በመጀመርያው ቀን ይለናል፦ ዘፍጥረት 1፥1 በመጀመሪያ ኤሎሂም ሰማይን እና ምድርን ፈጠረ። בְּרֵאשִׁ֖ית בָּרָ֣א אֱלֹהִ֑ים אֵ֥ת הַשָּׁמַ֖יִם וְאֵ֥ת הָאָֽרֶץ׃ ዘፍጥረት 1፥5 ኤሎሂምም ብርሃኑን "ቀን" ብሎ ጠራው፥ ጨለማውንም ሌሊት፡ አለው። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ አንድ ቀን። וַיִּקְרָ֨א אֱלֹהִ֤ים לָאֹור֙ יֹ֔ום וְלַחֹ֖שֶׁךְ קָ֣רָא לָ֑יְלָה וַֽיְהִי־עֶ֥רֶב וַֽיְהִי־בֹ֖קֶר יֹ֥ום אֶחָֽד׃ פ "ዮም" י֥וֹם ማለት በነጠላ "ቀን" ማለት ሲሆን ይህ የመጀመሪያ ቀን ስለሆነ "አንድ" ለሚለው "ኤኻድ" אֶחָֽד በማለት ይነግረናል። ዘጸአት ደግሞ በስድስት ቀናት ይለናል፦ ዘጸአት 31፥17 ያህዌህ ሰማይን እና ምድርን በስድስት ቀናት ፈጠረ። כִּי־שֵׁ֣שֶׁת יָמִ֗ים עָשָׂ֤ה יְהוָה֙ אֶת־הַשָּׁמַ֣יִם וְאֶת־הָאָ֔רֶץ "ያሚም" יָמִ֗ים ማለት "ቀናት" ማለት ሲሆን "ዮም" י֥וֹם ለሚለው ቃል ብዜት ነው፥ "ሼሼት" שֵׁ֣שֶׁת ማለት "ስድስት" ማለት ነው። ኤሎሂም ሰማይን እና ምድርን የፈጠረው በስድስት ቀናት ወይም በመጀመርያው ቀን? "ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ አንድ ቀን" "ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ ሁለተኛ ቀን" "ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ ሦስተኛ ቀን" የሚሉ አገላለፆችን ስናይ "ቀን" የተባለው 12 ሰዓት የያዘውን የመአልት ክፍል እና 12 ሰዓት የያዘውን የሌሊት ክፍል በጥቅሉ ባለ 24 ሰዓቱን እንደሆነ አመላካች ነው። በቁርኣን ግን ፍጥረት የተፈጠረበት "ቀን" የሚለው ባለ 24 ሰዓት ቀን ሳይሆን በትንሹ አንድ ሺህ ዓመት ነው፦ 22፥47 እጌታህም ዘንድ አንዱ ቀን ከምትቆጥሩት ቀን እንደ ሺህ ዓመት ነው፡፡ إِنَّ يَوْمًا عِندَ رَبِّكَ كَأَلْفِ سَنَةٍ مِّمَّا تَعُدُّونَ ተፍሢር ኢብኑ ዐባሥ 7፥53 "ጌታችሁ ያ ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አሏህ ነው" ከአያሙል ዱንያ እያንዳንዱ ቀን አንድ ሺህ ዓመት ነው"። { إِنَّ رَبَّكُمُ ٱللَّهُ ٱلَّذِي خَلَقَ ٱلسَمَاوَاتِ وَٱلأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ } من أيام الدنيا طول كل يوم ألف سنة ሌላው ሰማያትን እና ምድርን እንዲሁ በውስጣቸው ያለው ሁሉ ኅልቅቆ መሳፍርት ፍጥረት ሁሉ በጥቅሉ በስድስት ቀናት ውስጥ እንደፈጠ አሏህ ነግሮናል፥ ባይብል ላይ መላእክት መቼ እንደተፈጠሩ በግልጽ አይናገርም። ከዚያ ይልቅ በጥቅሉ አምላክ ከጥንት ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሠራውን ሥራ ሰው መርምሮ እንዳማያገኝ ይናገራል፦ መክብብ 3፥11 አምላክ ከጥንት ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሠራውን ሥራ ሰው መርምሮ እንዳያገኝ ዘላለምነትን በልቡ ሰጠው። גַּ֤ם אֶת־הָעֹלָם֙ נָתַ֣ן בְּלִבָּ֔ם מִבְּלִ֞י אֲשֶׁ֧ר לֹא־יִמְצָ֣א הָאָדָ֗ם אֶת־הַֽמַּעֲשֶׂ֛ה אֲשֶׁר־עָשָׂ֥ה הָאֱלֹהִ֖ים מֵרֹ֥אשׁ וְעַד־סֹֽוף׃ እኛም በሰማያት እና በምድር አፈጣጠር በማስተንተን፦ «ጌታችን ሆይ! ይህን በከንቱ አልፈጠርከውም፥ ጥራት ይገባህ! ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን» እንላለን፦ 3፥191 እነርሱም እነዚያ ቆመው፣ ተቀምጠውም እና በጎኖቻቸው ተጋድመው አሏህን የሚያወሱ፥ በሰማያት እና በምድር አፈጣጠር የሚያስተነትኑ፦ «ጌታችን ሆይ! ይህን በከንቱ አልፈጠርከውም፥ ጥራት ይገባህ! ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን» የሚሉ ናቸው፡፡ الَّذِينَ يَذْكُرُونَ اللَّهَ قِيَامًا وَقُعُودًا وَعَلَىٰ جُنُوبِهِمْ وَيَتَفَكَّرُونَ فِي خَلْقِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ رَبَّنَا مَا خَلَقْتَ هَـٰذَا بَاطِلًا سُبْحَانَكَ فَقِنَا عَذَابَ النَّارِ "ተፈኩር" تَفَكُّر የሚለው ቃል "ተፈከረ" تَفَكَّرَ ማለትም "አስተነተነ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ማስተንተን" ማለት ነው፥ የአሏህ ፍጥረት ማስተንተን የሥነ ፍጥረት ዕውቀታችንን ያጎለብተዋል። አምላካችን አሏህ ፍጥረቱን ከሚያስተነትኑ ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
ሥነ ፍጥረት ክፍል ሁለት በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 22፥47 እጌታህም ዘንድ አንዱ ቀን ከምትቆጥሩት ቀን እንደ ሺህ ዓመት ነው፡፡ إِنَّ يَوْمًا عِندَ رَبِّكَ كَأَلْفِ سَنَةٍ مِّمَّا تَعُدُّونَ ሰማይን ከፈጠረ በኃላ በሁለት ቀን የፈጠራትን ምድርን የእንቁላል ቅርጽ አርጎ ዘረጋት፥ "ዘረጋ" እንጂ "ፈጠረ" አይልም። "ዘረጋ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ደሓ" دَحَا ሲሆን የስም መደቡ "አድ ደሕያ” الدِّحْيَّة ነው፦ 79፥30 ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡ وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا "ከዚህ በኋላ" ማለት ከሰማይ መፈጠር በኃላ ማለት ነው፥ "አድ ደሕያ” الدِّحْيَّة ማለት “የሰጎን እንቁላል” ማለት ሲሆን አሏህ ምድርን “የሰጎን እንቁላል ቅርጽ አደረጋት” የሚል ትርጉም አለው። ፦ Dr. Kamal Omar Translation ፦ Ali Unal Translation ፦ Shabbir Ahmed Translation፦ “የሰጎን እንቁላል ቅርጽ አደረጋት”He made the earth egg-shaped” ብለው ተርጉመውታል። አሏህ ምድርን እንደ ሰጎን እንቁላል ቅርጽ አርጎ ያደላደላት ለእኛ ስለሆነ "ለእናንተ" በማለት ይናገራል፦ 55፥10 ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡ وَالْأَرْضَ وَضَعَهَا لِلْأَنَامِ 71፥19 አላህም ምድርን “ለእናንተ” ምንጣፍ አደረጋት፡፡ وَاللَّهُ جَعَلَ لَكُمُ الْأَرْضَ بِسَاطًا 2፥29 እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ هُوَ ٱلَّذِى خَلَقَ لَكُم مَّا فِى ٱلْأَرْضِ جَمِيعًۭا አሏህ ምድርን እንደ ሰጎን እንቁላል ቅርጽ አርጎ አደላድሎ በምድር ያለውን ማዕድናት፣ እጽዋት እና እንስሳት ለእኛ ፈጠረ፥ "በምድር ያለውን ሁሉ" የሚለው ማዕድናትን፣ እጽዋትን እና እንስሳትን ያካትታል። ከዚያ በጭስ መልክ የነበረችውን ሰማይ ሰባት ሰማያት አርጎ ጨረሳት አስተካከላት፦ 41፥12 በሁለት ቀናት ውስጥ ሰባት ሰማያት "አደረጋቸው"፡፡ فَقَضَىٰهُنَّ سَبْعَ سَمَٰوَاتٍۢ فِى يَوْمَيْنِ 2፥29 ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፥ ሰባት ሰማያትም "አደረጋቸው"፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ ثُمَّ ٱسْتَوَىٰٓ إِلَى ٱلسَّمَآءِ فَسَوَّىٰهُنَّ سَبْعَ سَمَٰوَٰتٍۢ ۚ وَهُوَ بِكُلِّ شَىْءٍ عَلِيمٌۭ "ወደ ሰማይ አሰበ" "ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ" ማለቱ በራሱ ሰማይ በጋዝ ደረጃ ተፈጥራ እንደነበረ ጉልህ ማሳያ ነው፥ "ከዚያም" ማለት ምድር እና ምድር ላይ ያለውን ከፈጠረ በኃላ ማለት ነው። 41፥12 ላይ "አደረገ" ለሚለው የገባው ቃል "ቀዷ" قَضَىٰ ሲሆን "ጨረሰ" በሚል ይመጣል፦ 27፥29 ሙሳም ጊዜውን በ-"ጨረሰ" እና ከቤተሰቦቹ ጋር በኼደ ጊዜ ከጡር ተራራ ጎን እሳትን አየ፡፡ فَلَمَّا قَضَىٰ مُوسَى الْأَجَلَ وَسَارَ بِأَهْلِهِ آنَسَ مِن جَانِبِ الطُّورِ نَارًا እዚህ አንቀጽ ላይ "ጨረሰ" ለሚለው የገባው "ቀዷ" قَضَىٰ እንደሆነ በአጽንዖት ልብ አድርግ! በተጨማሪ 2፥29 ላይ "አደረገ" ለሚለው የገባው ቃል "ሠዋ" سَوَّىٰ ሲሆን "አስተካከለ" በሚል ይመጣል፦ 87፥2 የዚያን ሁሉን ነገር የፈጠረውን እና ያስተካከለውን፡፡ الَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ እዚህ አንቀጽ ላይ "ያስተካከለ" ለሚለው የገባው "ሠዋ" سَوَّىٰ እንደሆነ በአንክሮት ልብ አድርግ! ስለዚህ ምድር እንደ ሰጎን እንቁላል ከመደላደሏ በፊት የፈጠራትን ጭሳዊ ሰማይ ሰባት ሰማያት አርጎ ፈጸማት አስተካከላት። "ቀዷሁነ" قَضَىٰهُنَّ "ሠዋሁነ" سَوَّىٰهُنَّ በሚል መድረሻ ቅጥያ ላይ ያለው "ሁነ" هُنَّ የሚለው ሦስተኛ አንስታይ መደብ "ሂየ" ‏هِيَ ለሚለው ብዜት ነው፥ "ሂየ" ‏هِيَ ማለት "እርሷ" ማለት ሲሆን "ሠማእ" سَّمَآء የሚለውን ተክቶ የመጣ ነው። ሰማይን ሰባት ሰማያት አድርጎ የጨረሰው እና ያስተካከለው በሁለት ቀናት ውስጥ ነው፥ እነዚህ "ሁለት ቀኖች" የተባሉት አምስተኛው ቀን "አል ኸሚሥ" ٱلْخَمِيس እና ስድስተኛው ቀን "አል ጁሙዓህ" ٱلْجُمُعَة እንደሆኑ ሙፈሢሮች አስቀምጠዋል፦ ተፍሢር ኢብኑ ከሲር 41፥12 "በሁለት ቀናት ውስጥ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው" ከዚያ ፈጽሞ በሁለት ቀናት ውስጥ ሰባት ሰማያት አስተካከላቸው፥ ሌላው ሁለቱ ቀናት አምስተኛው ቀን እና ስድስተኛው ቀን ናቸው። ( فقضاهن سبع سموات في يومين ) أي : ففرغ من تسويتهن سبع سموات في يومين ، أي : آخرين ، وهما يوم الخميس ويوم الجمعة .
إظهار الكل...
ሥነ ፍጥረት ክፍል አንድ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 7፥54 ጌታችሁ ያ ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀናት ውስጥ የፈጠረ አሏህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّام አምላካችን አሏህ ሰማያትን፣ ምድርን እና በመካከላቸው ያለውን ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠረ፦ 50፥38 ሰማያትን፣ ምድርን እና በመካከላቸው ያለውን ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ ድካምም ምንም አልነካንም፡፡ وَلَقَدْ خَلَقْنَا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ وَمَا مَسَّنَا مِن لُّغُوبٍ "ፊ" فِي ማለት "ውስጥ" ማለት ሲሆን በጥቅል ስድስት ቀናት ውስጥ ሰማያትን እና ምድርን እንደፈጠረ ጉልኅ ማሳያ ነው፦ 7፥54 ጌታችሁ ያ ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀናት ውስጥ የፈጠረ አሏህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّام "በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አሏህ ነው" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈጠረ" ለሚለው የገባው ቃል "ኸለቀ" خَلَقَ ሲሆን "ፊ" فِي የሚለው መስተዋድድ በጥቅል አገላለጽ ፍጥረት በስድስት ቀናት ውስጥ መፈጠራቸውን አመላካች ነው። በተናጥል ሌላ አንቀጽ ላይ ምድርን በሁለት ቀናት ውስጥ መፍጠሩትን ይናገራል፦ 41፥9 በላቸው «እናንተ በዚያ "ምድርን በሁለት ቀናት ውስጥ በፈጠረው አምላክ በእርግጥ ትክዳላችሁን?" ለእርሱም ባለንጣዎችን ታደርጋላችሁን? ያ ይህንን የሠራው የዓለማት ጌታ ነው፡፡ قُلْ أَئِنَّكُمْ لَتَكْفُرُونَ بِٱلَّذِى خَلَقَ ٱلْأَرْضَ فِى يَوْمَيْنِ وَتَجْعَلُونَ لَهُۥٓ أَندَادًۭا ۚ ذَٰلِكَ رَبُّ ٱلْعَٰلَمِينَ እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈጠረ" ለሚለው የገባው ቃል "ኸለቀ" خَلَقَ ሲሆን "ሁለት ቀናት" የተባሉት የመጀመሪያው ቀን "አል አሐድ" ٱلْأحَد እና ሁለተኛው ቀን "አል ኢስነይን" ٱلْاِثْنَيْن‎ እንደሆኑ ሙፈሢሮች አስቀምጠዋል፦ ተፍሢር ኢብኑ ከሲር 41፥9 "ምድርን በሁለት ቀናት ውስጥ በፈጠረው" ሲል "የመጀመሪያው ቀን እና ሁለተኛው ቀን ነው" ማለት ነው"። فقوله : ( خلق الأرض في يومين ) يعني : يوم الأحد ويوم الاثنين . ፨ "አሐድ" أحَد ማለት "አንድ" ማለት ሲሆን "እሑድ" ማለት ነው፥ "እሑድ" የሚለው የግዕዙ ቃል በራሱ “አሐደ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አንድ" ማለት ነው። ፨ "ኢስነይን" اِثْنَيْن‎ ማለት "ሁለት" ማለት ሲሆን "ሰኞ" ማለት ነው፥ "ሰኞ" ማለት "ሰነየ" ማለትም "ደገመ" ከሚል የመጣ ሲሆን "ሁለተኛ" ማለት ነው። አሏህ በምድር ከበላይዋ የረጉ ጋራዎችን አደረገ፥ በውስጧም ባረከ፦ 42፥10 በእርሷ ከበላይዋ የረጉ ጋራዎችን አደረገ፥ በውስጧም ባረከ፡፡ وَجَعَلَ فِيهَا رَوَٰسِىَ مِن فَوْقِهَا وَبَٰرَكَ فِيهَا "ባረከ" بَٰرَكَ ማለት "ባረከ" ማለት ሲሆን በውስጧም ምግቦችዋን በአራት ቀናት ውሰጥ ለጠያቂዎች ትክክል ሲኾኑ ወሰነ፦ 42፥10 "በውስጧም ምግቦችዋን በአራት ቀናት ውሰጥ ለጠያቂዎች ትክክል ሲኾኑ ወሰነ"፡፡ وَقَدَّرَ فِيهَآ أَقْوَٰتَهَا فِىٓ أَرْبَعَةِ أَيَّامٍۢ سَوَآءًۭ لِّلسَّآئِلِينَ "በአራት ቀናት ውሰጥ ለጠያቂዎች ትክክል ሲኾኑ ወሰነ" አለ እንጂ "በአራት ቀናት ውሰጥ ለጠያቂዎች ትክክል ሲኾኑ ፈጠረ" አላለም፥ "ወሰነ" ለሚለው የገባው ቃል "ቀደረ" قَدَّرَ ሲሆን "መጠነ" "አዘጋጀ" በሚል ይመጣል፦ 80፥19 ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው እና መጠነው፡፡ مِن نُّطْفَةٍ خَلَقَهُ فَقَدَّرَهُ 25፥2 ነገሩንም ሁሉ የፈጠረ እና በትክክልም ያዘጋጀው ነው፡፡ وَخَلَقَ كُلَّ شَيْءٍ فَقَدَّرَهُ تَقْدِيرًا እነዚህ አናቅጽ ላይ "ፈጠረ" ለሚለው የገባው ቃል "ኸለቀ" خَلَقَ ሲሆን "መጠነ" "አዘጋጀ" ለሚለው የገባው ቃል ግን "ቀደረ" قَدَّرَ ነው፥ በአራት ቀናት የመጠነው እና ያዘጋጀው ምግቧን እንጂ ፈጠረ አይልም። ምድርን የፈጠረበት 2 ቀናት እና ምግቧን የወሰነበትን 4 ቀናት ደምራችሁ 6 ቀናት ብላችሁ ለማጋጨት የሞከራችሁት ሙከራ ፉርሽ ሆኗል። ሲጀመር "ተዳኹል" تَدَاخُل የሚለው ቃል "ተዳኸለ" تَدَاخَلَ ማለትም "ተጠላለፈ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መጠላለፍ"intersection" ማለት ነው፥ አራት ቀናት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ተዳኹል የሆኑት "አል አሐድ" ٱلْأحَد "አል ኢስነይን" ٱلْاِثْنَيْن‎ "አል ሱላሳእ" ٱلْثُّلَاثَاء "አል አርቢዓእ" أَرْبِعَاء ናቸው፦ ተፍሢሩል ጀላለይን 41፥10 "በአራት ሙሉ ቀናት በሌላ አነጋገር በውስጧ ያለው የተራሮች አቀማመጥ ከሥስተኛው እና ከአራተኛው ቀን ጋር ተያይዞ የተከናወነው በትክክል "ሠዋእ" በተሳቢ ምክንያቱም ግሣዊ ስም ነው፥ አራቱ ቀናት ያነሱም ያልበዙም ለጠያቂዎች ሁሉ ስለ ምድር አፈጣጠር እና በውስጧ ስላለው ሁሉ በትክክል አራት ነበሩ"። "ሠዋእ" سَوَآء ማለት "በትክክል" ማለት ሲሆን በሰዋስው አወቃቀር አራት ቀናት በሁለት ቀናት ውስጥ ተለጣጥፎ"overlap" የመጣ ነው። ፨ "ሱላሳእ" ثُّلَاثَاء ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ማክሰኞ" ማለት ነው። "ማክሰኞ" ማለት "ማግስት" ማለት ነው፥ የእሁድ ማግስት "ሦስተኛ" ቀን ነው። ፨ "አርቢዓእ" أَرْبِعَاء ማለት "አራት" ማለት ሲሆን "ረቡዕ" ማለት ነው፥ "ረቡዕ" ማለት "ረበዓ" ከሚል የመጣ ሲሆን "አራተኛ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ምድርን በፈጠረበት ጊዜ ሰማይን ጋዝ አርጎ ፈጠራት፥ ሰማይ የተገነባችበት ጋዝ ምድር በተፈጠረች ጊዜ ከእርሷ የሚወጣውን ጋዝ ነበረ፦ 79፥27 ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? አሏህ ገነባት፡፡ أَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ السَّمَاءُ ۚ بَنَاهَا ተፍሢር ኢብኑ ከሲር 42፥11 እርሱ(ጋዙ) ምድር በተፈጠረች ጊዜ ከእርሷ የሚወጣው ጭስ ነው"። وهو : بخار الماء المتصاعد منه حين خلقت الأرض “ጭስ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ዱኻን” دُخَان ሲሆን “ጋዝ”gas" ማለት ነው፥ ሰማይ በጋዝ ደረጃ እያለች አሏህ ለሰማይ እና ለምድር፦ «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ እነርሱም፦ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፦ 42፥11 "ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ ٱسْتَوَىٰٓ إِلَى ٱلسَّمَآءِ وَهِىَ دُخَانٌۭ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ٱئْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًۭا قَالَتَآ أَتَيْنَا طَآئِعِينَ ኢሻላህ ይቀጥላል..... ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
ይህ የወንድም ሙከሚል ቻናል ነው። ጎራ ይበሉ፦ ttps://t.me/mukamil12/1488
إظهار الكل...
ሙቀረቡን በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 56፥11 እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡ أُولَـٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ "ሙቀረብ" مُقَرَّب የሚለው ቃል "ቀሪበ" قَرِبَ ማለትም "ቀረበ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ቀራቢ" "ባለሟል" ማለት ነው፥ "ሙቀረቡን" مُقَرَّبُون ወይም "ሙቀረቢን" مُقَرَّبِين ደግሞ የሙቀረብ ብዙ ቁጥር ሲሆን "ቀራቢዎች" "ባለሟሎች" ማለት ነው። ከአስሓቡል የሚን ለበጎ ሥራ ቀዳሚዎቹ ለገነት ቀዳሚዎች ሲሆኑ እነርሱ አሏህ ዘንድ "ሙቀረቡን" ናቸው፦ 56፥11 እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡ أُولَـٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ሲሆን እነርሱም "ሙቀረቡን" ናቸው፦ 83፥21 "ባለሟልዎቹ" ይጣዱታል፡፡ يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ 83፥28 "ባለሟሎቹ" ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡ عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ አንድ አማኝ ካመነ በኃላ የሚሠራው መልካም ሥራ ወደ አሏህ መቃረቢያ ሲሆን "ቁርባን" ይባላል፥ "ቁርባን" قُرْبَان ማለት "መቃረቢያ" ማለት ነው፦ 5፥35 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህን ፍሩ! ወደ እርሱም መቃረቢያ መልካም ሥራን ፈልጉ፡፡ ትድኑ ዘንድም በእርሱ መንገድ ታገሉ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَابْتَغُوا إِلَيْهِ الْوَسِيلَةَ وَجَاهِدُوا فِي سَبِيلِهِ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ 9፥99 ከአዕራቦችም በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን፣ የሚሰጣቸውን ምጽዋቶች አሏህ ዘንድ መቃረቢያዎች እና ወደ መልእክተኛው ጸሎቶች መዳረሻ አድርጎ የሚይዝ ሰው አለ፡፡ ንቁ! እርሷ ለእነርሱ በእርግጥ አቃራቢ ናት፥ አሏህ በችሮታው ውስጥ (በገነቱ) በእርግጥ ያስገባቸዋል፡፡ አሏህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ وَمِنَ الْأَعْرَابِ مَن يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَيَتَّخِذُ مَا يُنفِقُ قُرُبَاتٍ عِندَ اللَّهِ وَصَلَوَاتِ الرَّسُولِ ۚ أَلَا إِنَّهَا قُرْبَةٌ لَّهُمْ ۚ سَيُدْخِلُهُمُ اللَّهُ فِي رَحْمَتِهِ ۗ إِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيمٌ "አዕራብ" أَعْرَاب ማለት "ገጠሬ" ማለት ሲሆን ከዐረብ ገጠሬዎች በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን አምነው የሚሰጣቸውን ምጽዋቶች አሏህ ዘንድ መቃረቢያዎች አድርገው የሚይዙ ሰዎች አሉ፥ ስለዚህ አሏህ ዘንድ ከሰዎች መካከል ሙቀረቡን አሉ። በተመሳሳይ መላእክት የአሏህ ባመሟሎች ስለሆኑ "ሙቀረቢን" مُقَرَّبِين ተብለዋል፦ 4፥172 አልመሢሕ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ "ቀራቢዎች" የኾኑት መላእክት አይጠየፉም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ መላእክት ወደ መርየም መጥተው ለመርየም ያሏት "ባለሟል በኾነ ልጅ" ሳይሆን "ከባለሟሎችም በኾነ ልጅ" የሚል ነው፦ 3፥45 መላእክት ያሉትን አስታውስ፡- «መርየም ሆይ! አሏህ ከእርሱ በኾነው ቃል ስሙ አልመሢሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለም እና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ልጅ ያበስርሻል»። إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِّنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ እዚህ አንቀጽ ላይ "አል ሙቀረቢን" الْمُقَرَّبِين የተባሉ ከላይ እንደተገለጸው የአሏህ ባሮች ሲሆኑ ይህ አንቀጽ ጭራሽኑ ከሙቃሪቢን መካከል አንዱ ዒሣ መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፥ "ዒሣ ብቻ "ባለሟል" ነው" የሚል ሽታው ቁርኣን ላይ የለም። አምላካችን አሏህ ሙቀረቡን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
የሥላሴ እሳቤ "ድጋሚ ይታተም" ብላችሁ በጠየቃችሁት መሠረት ድጋሚ ታትሟል። የምትፈልጉ +251920781016 ዐብዱ ረሕማን ብላችሁ ደውላችሁ ውሰዱ!
إظهار الكل...
ቀጥተኛው መንገድ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 36፥4 "በቀጥታም መንገድ ላይ ነህ"፡፡ عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ "ሲሯጥ" صِرَٰط ማለት በመነሻ እና በመዳረሻ መካከል ያለ "መንገድ" ማለት ሲሆን እዚህ ዐውድ ላይ "መንገድ" እያልን የምንጦምረው እማሬአዊ የሆነውን የአስፋት መንገድ ሳይሆን ወደ ጀነት የሚያደርሰውን ፍካሬአዊ የሆነውን መንገድ ነው። አምላካችን አሏህን በብቸኝነት ማምለክ ወደ ጀነት የሚያደርስ "ቀጥተኛው መንገድ" ነው፦ 36፥61 "አምልኩኝ! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው" በማለትም አላዘዝኩምን? وَأَنِ ٱعْبُدُونِى ۚ هَٰذَا صِرَٰطٌۭ مُّسْتَقِيمٌۭ "ይህ" የሚለው አመልካች ተውላጠ ስም "አምልኩኝ" የሚለውን ቃል አመላካች ነው። ዒሣም በተልኮው አሏህን በብቸኝነት ማምለክ "ቀጥተኛ መንገድ" እንደሆነ አበክሮ እና አዘክሮ ነግሮናል፦ 3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነዉና "አምልኩት! ይህ "ቀጥተኛ መንገድ" ነው»። አላቸዉ። إِنَّ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبُّكُمْ فَٱعْبُدُوهُ ۗ هَٰذَا صِرَٰطٌۭ مُّسْتَقِيمٌۭ 43፥64 «አሏህ ጌታዬ ጌታችሁም ነውና "አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው»። إِنَّ اللَّهَ هُوَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۚ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ እነዚህም አናቅጽ ላይ "ይህ" የሚለው አመልካች ተውላጠ ስም "አምልኩት" የሚለውን ቃል አመላካች ነው። "ሙስተቂም" مُّسْتَقِيم ማለት "ቀጥተኛ" ማለት ሲሆን አምላካችን አሏህን በብቸኝነት ማምለክ ቀጥተኛ መንገድ ነው፥ ከዚያ ውጪ ያሉት መንገዶች የጥመት መንገዶች ናቸው፦ 6፥153 «ይህም ቀጥተኛ ሲኾን መንገዴ ነው፤ ተከተሉትም፡፡ የጥመት መንገዶችንም አትከተሉ፡፡ ከቀጥተኛው መንገዱ እናንተን ይለያዩዋችኋልና» በላቸው። وَأَنَّ هَـٰذَا صِرَاطِي مُسْتَقِيمًا فَاتَّبِعُوهُ ۖ وَلَا تَتَّبِعُوا السُّبُلَ فَتَفَرَّقَ بِكُمْ عَن سَبِيلِهِ ይህ አንዱን አምላክ በብቸንነት ማምለክ ለኢብራሂም የተገለጠ የኢብራሂም መንገድ ነው፥ አምላካችን አሏህ የኢብራሂምን መንገድ መርቶናል፦ 6፥161 «እኔ ጌታዬ ወደ "ቀጥተኛው መንገድ" ትክክለኛን ሃይማኖት ወደ እውነት አዘንባይ ሲኾን የአብርሃምን መንገድ መራኝ፡፡ እርሱም ከአጋሪዎቹ አልነበረም» በል፡፡ قُلْ إِنَّنِى هَدَىٰنِى رَبِّىٓ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ دِينًۭا قِيَمًۭا مِّلَّةَ إِبْرَٰهِيمَ حَنِيفًۭا ۚ وَمَا كَانَ مِنَ ٱلْمُشْرِكِينَ አሁንም "ቀጥተኛው መንገድ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! አንድ ሰው ከነበረበት ሺርክ እና ኩፍር ወደ አምላካችን አሏህ በንስሓ ከተመለሰ አሏህ በንስሓ የሚመለውን ሰው ወደ እርሱ ይመራዋል፦ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ "የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል"፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል" የሚለው በአጽንዖት ይሰመርበት! አንድ ሙሥሊም በቀጥተኛው መንገድ ላይ ስለሆነ አምላካችን አሏህ፦ "በቀጥታ መንገድ ላይ ነህ" ብሏል፦ 36፥4 "በቀጥታም መንገድ ላይ ነህ"፡፡ عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ 43፥43 ያንንም ወደ አንተ የተወረደልህን አጥብቀህ ያዝ! አንተ "በቀጥተኛው መንገድ ላይ ነህና"።فَاسْتَمْسِكْ بِالَّذِي أُوحِيَ إِلَيْكَ ۖ إِنَّكَ عَلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ ሙሥሊም በቀጥተኛው መንገድ እንደሆነ በቁና ጥቅስ ማቅረብ ይቻላል። አንድ ዳዒ ሙሥሊም በቀጥተኛ መንገድ ስለሆነ እና ይህም ቀጥተኛ መንገድ አሏህን በብቸኝነት ማምለክ እንደሆነ ተረድቶ ሰዎችን ወደ ቀጥተኛው መንገድ ይጣራል፦ 23፥73 አንተም ወደ "ቀጥተኛው መንገድ" በእርግጥ ትጠራቸዋለህ። وَإِنَّكَ لَتَدْعُوهُمْ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ 16፥125 "ወደ ጌታህ መንገድ" በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ አንድ ሙሥሊም በቀጥተኛ መንገድ ላይ ባይሆን ኖሮ ወደ ቀጥተኛ መንገድ መጥራቱ ትርጉም አልባ ይሆን ነበር። ይህ ቀጥተኛ መንገድ መነሻው ዱንያህ ሲሆን መዳረሻው አኺራ ነው፥ አሁን ጉዞ ላይ ነን። ለምሳሌ፦ እኔ ፒያሳ መሄድ ፈልጌ የፒያሳን መንገድ መነሻውን አየር ጤና አንድ ሰው ከመራኝ በኃላ መንገዱ በጉዞ ላይ ጦር ኃይሎች ጋር ስደርስ ወደ ኮልፌ መንገዱት እንዳልስት፣ ልደታ ጋር ስደርስ ወደ መርካቶ አሊያ ወደ ኦልድ ኤር ፓርት መንገዱን እንዳልስት፣ ሜክሲኮ ጋር ስደርስ ወደ መካኒሳ አሊያም ወደ ተክለ ሃይማኖት መንገዱን እንዳልስት፣ ብሔራዊ ጋር ስደርስ መንገዱን ወደ ፍሉ ውኃ እንዳልስት እስከመጨረሻው ምሪት ያስፈልገኛል። በተመሳሳይ ይህ ቀጥተኛ መንገድ መነሻውን አሏህ ከመራን በኃላ በጉዞ ላይ እያለን ከመንገዱ እንዳንወጣ ምሪት እስከመጨረሻው ለማግኘት አሏህን "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" እያልን በሶላት ላይ ስንቆም እንጠይቀዋለን፥ አሏህም እነዚያን ያመኑትን ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ መሪ ነው፦ 1፥6 "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን"። ٱهْدِنَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلْمُسْتَقِيمَ 22፥54 አሏህ እነዚያን ያመኑትን ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ "መሪ" ነው፡፡ وَإِنَّ اللَّهَ لَهَادِ الَّذِينَ آمَنُوا إِلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ አምላካችን አሏህ ሰዎችን ወደ ቀጥተኛው መንገድ የምንጠራ ዳዒዎች ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
"አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ ኢማን የሚጨምሩላቸው" የሚለው ይሰመርበት! በኢማም አቡ መንሱር አል ማቱሪዲይ የተቀመረው ማቱሪዲያህ የሚባለው ስሑት ዐቂዳህ፦ "ኢማን የማይጨምር እና የማይቀንስ ቋሚ ነው" የሚል እሳቤ በዚህ ጥቅስ ድባቅ ይገባል። ኢማኑ በአሏህ አንቀጾች እየጨመረ የሚሄድ ሙእሚን አሏህ ዘንድ ደረጃዎች አሉት፦ 8፥4 እነዚያ በእውነት አማኞች እነርሱ ብቻ ናቸው፡፡ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ደረጃዎች ምሕረት እና የከበረ ሲሳይም አላቸው፡፡ أُولَـٰئِكَ هُمُ الْمُؤْمِنُونَ حَقًّا ۚ لَّهُمْ دَرَجَاتٌ عِندَ رَبِّهِمْ وَمَغْفِرَةٌ وَرِزْقٌ كَرِيمٌ "ደረጃት" دَرَجَات የሚለው ቃል "ደረጃህ" دَرَجَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን አሏህ ዘንድ ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ተጀናህ ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4474 ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰማው ብሎ እንደተረከው፦ "እርሳቸውም አሉ፦ "ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ደረጃዎቿም ያላቸው እርቀት ልክ የሰማይ እና የምድር እርቀት ያክል ነው። ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፥ أَنَّ مُعَاذَ بْنَ جَبَلٍ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ ‏ "‏ الْجَنَّةُ مِائَةُ دَرَجَةٍ كُلُّ دَرَجَةٍ مِنْهَا مَا بَيْنَ السَّمَاءِ وَالأَرْضِ وَإِنَّ أَعْلاَهَا الْفِرْدَوْسُ አማኞች በእምነት የሚሠሩት መልካም ሥራ በሚሠሩት መልካም ሥራ መጠን የተለያየ ደረጃዎችን በጀነት ውስጥ ያገኙበታል፦ 20፥75 በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አላቸው፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ 3፥163 እነርሱ አላህ ዘንድ ባለ ደረጃዎች ናቸው፡፡ አላህም የሚሠሩትን ነገር ተመልካች ነው፡፡ هُمْ دَرَجَاتٌ عِندَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ بَصِيرٌ بِمَا يَعْمَلُونَ 6፥132 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ጌታህም ከሚሠሩት ሁሉ ዘንጊ አይደለም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۚ وَمَا رَبُّكَ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ 46፥19 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ሥራዎቻቸውንም ይሞላላቸው ዘንድ ይህንን መነዳቸው፥ እነርሱም አይበደሉም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۖ وَلِيُوَفِّيَهُمْ أَعْمَالَهُمْ وَهُمْ لَا يُظْلَمُونَ "ጀናህ" جَنَّة በ "ታ" ة መርቡጧህ በነጠላ ሲሆን አጠቃላይ ጀነትን ያመለክታል፥ በአጠቃላዩ ጀነት ውስጥ ለመግባት ቁልፉ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ሲሆን በጀነት ውስጥ ያሉትን ጀረጃዎች ውስጥ ለመግባት እና ለመመንዳት መልካም ሥራ ያስፈልጋል። በጀነት ውስጥ ያሉት መቶ የተለያዩ ደረጃዎች እራሱ "ጀናት" جَنَّات‎ ተብለዋል፥ "ጀናት" جَنَّات‎ በ "ታ" ت መፍቱሓህ ሲሆን በብዜት "ጀነቶች" "ገነቶች" ማለት ነው። እነዚህ የተለያየ ደረጃዎች የሆኑ ጀነቶች አምነው መልካም ለሚሠሩ የሚሰጥ ምንዳ፣ ትሩፋት፣ ወሮታ፣ ስርጉት፣ ትርሲት ነው፦ 31፥8 እነዚያ ያመኑ እና መልካሞችንም የሠሩ ለእነርሱ የጸጋ "ገነቶች" አላቸው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتُ النَّعِيمِ እዚህ አንቀጽ ላይ "ገነቶች" ለሚለው የገባው በብዙ ቁጥር "ጀናት" جَنَّات‎ እንደሆነ ልብ አድርግ! እያንዳንዱ ደረጃ "ጀነቱል ዐድን" جَنَّةُ العَدْن "ጀነቱ አን-ነዒም" جَنَّةُ النَّعِيمِ "ጀነቱል መእዋ" جَنَّةُ المَأْوَىٰ "ጀነቱል ፊርደውሥ" جَنَّةُ الفِرْدَوْسُ እየተባለ ይጠራል። አምላካችን አሏህ የኢማንን ኃይል ተረድተው መልካም ሥራ ከሚሠሩ ሙእሚን ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
ቁወቱል ኢማን በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 92፥6 በመልካሚቱም እምነት ያረጋገጠ። وَصَدَّقَ بِالْحُسْنَىٰ "ቁዋህ" قُوَّة የሚለው ቃል "ቀዊየ" قَوِيَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ኃይል" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن የሚለው ቃል "አሚነ" أَمِنَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "እምነት" ማለት ነው። በጥቅሉ "ቁወቱል ኢማን" قُوَّة الإِيمَان ማለት "የእምነት ኃይል" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ትልቁ የኢማን ቅርንጫፍ ነው፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60 አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ “ላ ኢላሀ ኢለሏህ” ማለት ነው። ትንሹ ደግሞ ከመንገድ ላይ እንቅፋት ማስወገድ ነው፥ ሐያእ የኢማን ቅርንጫፍ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَأَدْنَاهَا إِمَاطَةُ الأَذَى عَنِ الطَّرِيقِ وَالْحَيَاءُ شُعْبَةٌ مِنَ الإِيمَانِ ‏ "ሐያእ" حَيَاء ማለት "ዓይናፋርነት" "ጨዋነት" ማለት ነው፥ ሐያእ ከኢማን ነው። ኢማን ደግሞ ወደ ጀነት ይመራል፦ ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 115 አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ሐያእ ከኢማን ነው፥ ኢማን ደግሞ ወደ ጀነት ይመራል። ብልግና ከብሉሽነት ነው፥ ብሉሽነት ወደ እሳት ይመራል”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَيَاءُ مِنَ الإِيمَانِ وَالإِيمَانُ فِي الْجَنَّةِ وَالْبَذَاءُ مِنَ الْجَفَاءِ وَالْجَفَاءُ فِي النَّارِ ‏ "በዛእ" بَذَاء ማለት ደግሞ "ዓይናውጣነት" "ብልግና" ማለት ነው፥ ብልግና ከብሉሽነት(ኩፍር) ሲሆን ኩፍር ወደ እሳት ይመራል። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" መልካሚቱም እምነት ናት፦ 92፥6 በመልካሚቱም እምነት ያረጋገጠ። وَصَدَّقَ بِالْحُسْنَىٰ 92፥7 ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْيُسْرَىٰ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه በምትባለው መልካሚቱም እምነት ያረጋገጠ አሏህ መልካም ሥራን ያገራለታል፥ "ዩሥር" يُسْرَىٰ ማለት "ቀላል" "ገር" "መልካም" ማለት ሲሆን ኢማን ወደ ጀነት የሚያመራው በመልካም ሥራ ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የምትለዋን መልካሚቱን እምነት ሰምቶ የካደ አሏህ መልካም ሥራን ያከብድበታል፦ 92፥9 በመልካሚቱ እምነት ያሰተባበለም። وَكَذَّبَ بِالْحُسْنَىٰ 92፥10 ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْعُسْرَىٰ "ዑሥራ" عُسْرَىٰ ማለት "ከባድ" "ሸካራ" "ክፉ" ማለት ሲሆን ኩፍር ወደ እሳት የሚመራው በመጥፎ ሥራ ነው። ኢማን የሚጨምር እና የሚቀንስ ነው፦ 8፥2 ፍጹም ምእምናን እነዚያ አሏህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በእነርሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ ኢማን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَإِذَا تُلِيَتْ عَلَيْهِمْ آيَاتُهُ زَادَتْهُمْ إِيمَانًا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ
إظهار الكل...
31፥8 እነዚያ ያመኑ እና መልካሞችንም የሠሩ ለእነርሱ የጸጋ "ገነቶች" አላቸው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتُ النَّعِيمِ እዚህ አንቀጽ ላይ "ገነቶች" ለሚለው የገባው በብዙ ቁጥር "ጀናት" جَنَّات‎ እንደሆነ ልብ አድርግ! እያንዳንዱ ደረጃ "ጀነቱል ዐድን" جَنَّةُ العَدْن "ጀነቱ አን-ነዒም" جَنَّةُ النَّعِيمِ "ጀነቱል መእዋ" جَنَّةُ المَأْوَىٰ "ጀነቱል ፊርደውሥ" جَنَّةُ الفِرْدَوْسُ እየተባለ ይጠራል። አምላካችን አሏህ የኢማንን ኃይል ተረድተው መልካም ሥራ ከሚሠሩ ሙእሚን ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
ቁወቱል ኢማን በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 92፥6 በመልካሚቱም እምነት ያረጋገጠ። وَصَدَّقَ بِالْحُسْنَىٰ "ቁዋህ" قُوَّة የሚለው ቃል "ቀዊየ" قَوِيَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ኃይል" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن የሚለው ቃል "አሚነ" أَمِنَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "እምነት" ማለት ነው። በጥቅሉ "ቁወቱል ኢማን" قُوَّة الإِيمَان ማለት "የእምነት ኃይል" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ትልቁ የኢማን ቅርንጫፍ ነው፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60 አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ “ላ ኢላሀ ኢለሏህ” ማለት ነው። ትንሹ ደግሞ ከመንገድ ላይ እንቅፋት ማስወገድ ነው፥ ሐያእ የኢማን ቅርንጫፍ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَأَدْنَاهَا إِمَاطَةُ الأَذَى عَنِ الطَّرِيقِ وَالْحَيَاءُ شُعْبَةٌ مِنَ الإِيمَانِ ‏ "ሐያእ" حَيَاء ማለት "ዓይናፋርነት" "ጨዋነት" ማለት ነው፥ ሐያእ ከኢማን ነው። ኢማን ደግሞ ወደ ጀነት ይመራል፦ ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 115 አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ሐያእ ከኢማን ነው፥ ኢማን ደግሞ ወደ ጀነት ይመራል። ብልግና ከብሉሽነት ነው፥ ብሉሽነት ወደ እሳት ይመራል”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَيَاءُ مِنَ الإِيمَانِ وَالإِيمَانُ فِي الْجَنَّةِ وَالْبَذَاءُ مِنَ الْجَفَاءِ وَالْجَفَاءُ فِي النَّارِ ‏ "በዛእ" بَذَاء ማለት ደግሞ "ዓይናውጣነት" "ብልግና" ማለት ነው፥ ብልግና ከብሉሽነት(ኩፍር) ሲሆን ኩፍር ወደ እሳት ይመራል። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" መልካሚቱም እምነት ናት፦ 92፥6 በመልካሚቱም እምነት ያረጋገጠ። وَصَدَّقَ بِالْحُسْنَىٰ 92፥7 ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْيُسْرَىٰ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه በምትባለው መልካሚቱም እምነት ያረጋገጠ አሏህ መልካም ሥራን ያገራለታል፥ "ዩሥር" يُسْرَىٰ ማለት "ቀላል" "ገር" "መልካም" ማለት ሲሆን ኢማን ወደ ጀነት የሚያመራው በመልካም ሥራ ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የምትለዋን መልካሚቱን እምነት ሰምቶ የካደ አሏህ መልካም ሥራን ያከብድበታል፦ 92፥9 በመልካሚቱ እምነት ያሰተባበለም። وَكَذَّبَ بِالْحُسْنَىٰ 92፥10 ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْعُسْرَىٰ "ዑሥራ" عُسْرَىٰ ማለት "ከባድ" "ሸካራ" "ክፉ" ማለት ሲሆን ኩፍር ወደ እሳት የሚመራው በመጥፎ ሥራ ነው። ኢማን የሚጨምር እና የሚቀንስ ነው፦ 8፥2 ፍጹም ምእምናን እነዚያ አሏህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በእነርሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ ኢማን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَإِذَا تُلِيَتْ عَلَيْهِمْ آيَاتُهُ زَادَتْهُمْ إِيمَانًا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ "አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ ኢማን የሚጨምሩላቸው" የሚለው ይሰመርበት! በኢማም አቡ መንሱር አል ማቱሪዲይ የተቀመረው ማቱሪዲያህ የሚባለው ስሑት ዐቂዳህ፦ "ኢማን የማይጨምር እና የማይቀንስ ቋሚ ነው" የሚል እሳቤ በዚህ ጥቅስ ድባቅ ይገባል። ኢማኑ በአሏህ አንቀጾች እየጨመረ የሚሄድ ሙእሚን አሏህ ዘንድ ደረጃዎች አሉት፦ 8፥4 እነዚያ በእውነት አማኞች እነርሱ ብቻ ናቸው፡፡ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ደረጃዎች ምሕረት እና የከበረ ሲሳይም አላቸው፡፡ أُولَـٰئِكَ هُمُ الْمُؤْمِنُونَ حَقًّا ۚ لَّهُمْ دَرَجَاتٌ عِندَ رَبِّهِمْ وَمَغْفِرَةٌ وَرِزْقٌ كَرِيمٌ "ደረጃት" دَرَجَات የሚለው ቃል "ደረጃህ" دَرَجَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን አሏህ ዘንድ ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ተጀናህ ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4474 ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰማው ብሎ እንደተረከው፦ "እርሳቸውም አሉ፦ "ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ደረጃዎቿም ያላቸው እርቀት ልክ የሰማይ እና የምድር እርቀት ያክል ነው። ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፥ أَنَّ مُعَاذَ بْنَ جَبَلٍ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ ‏ "‏ الْجَنَّةُ مِائَةُ دَرَجَةٍ كُلُّ دَرَجَةٍ مِنْهَا مَا بَيْنَ السَّمَاءِ وَالأَرْضِ وَإِنَّ أَعْلاَهَا الْفِرْدَوْسُ አማኞች በእምነት የሚሠሩት መልካም ሥራ በሚሠሩት መልካም ሥራ መጠን የተለያየ ደረጃዎችን በጀነት ውስጥ ያገኙበታል፦ 20፥75 በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አላቸው፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ 3፥163 እነርሱ አላህ ዘንድ ባለ ደረጃዎች ናቸው፡፡ አላህም የሚሠሩትን ነገር ተመልካች ነው፡፡ هُمْ دَرَجَاتٌ عِندَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ بَصِيرٌ بِمَا يَعْمَلُونَ 6፥132 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ጌታህም ከሚሠሩት ሁሉ ዘንጊ አይደለም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۚ وَمَا رَبُّكَ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ 46፥19 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ሥራዎቻቸውንም ይሞላላቸው ዘንድ ይህንን መነዳቸው፥ እነርሱም አይበደሉም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۖ وَلِيُوَفِّيَهُمْ أَعْمَالَهُمْ وَهُمْ لَا يُظْلَمُونَ "ጀናህ" جَنَّة በ "ታ" ة መርቡጧህ በነጠላ ሲሆን አጠቃላይ ጀነትን ያመለክታል፥ በአጠቃላዩ ጀነት ውስጥ ለመግባት ቁልፉ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ሲሆን በጀነት ውስጥ ያሉትን ጀረጃዎች ውስጥ ለመግባት እና ለመመንዳት መልካም ሥራ ያስፈልጋል። በጀነት ውስጥ ያሉት መቶ የተለያዩ ደረጃዎች እራሱ "ጀናት" جَنَّات‎ ተብለዋል፥ "ጀናት" جَنَّات‎ በ "ታ" ت መፍቱሓህ ሲሆን በብዜት "ጀነቶች" "ገነቶች" ማለት ነው። እነዚህ የተለያየ ደረጃዎች የሆኑ ጀነቶች አምነው መልካም ለሚሠሩ የሚሰጥ ምንዳ፣ ትሩፋት፣ ወሮታ፣ ስርጉት፣ ትርሲት ነው፦
إظهار الكل...
፨ "ገይሪ ሹሩጢይ" غَيْرِ شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ አልባ"unconditional" ማለት ሲሆን በጥቅሉ "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ አልባ ምርጫ"unconditional election" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፦ 28፥68 ጌታህም የሚሻውን ይፈጥራል፤ ይመርጣልም፡፡ ለእነርሱ ምርጫ የላቸውም፡፡ አሏህ ከማይግገባው ሁሉ ጠራ፡፡ ከሚያጋሯቸውም ላቀ፡፡ وَرَبُّكَ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ وَيَخْتَارُ ۗ مَا كَانَ لَهُمُ الْخِيَرَةُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ وَتَعَالَىٰ عَمَّا يُشْرِكُونَ "የሚሻውን ይፈጥራል" በሚል ኃይለ ቃል "ይመርጣል" የሚለው ቃል አሏህ የሚሻውን ሰው፣ የሚሻውን እንስሳ፣ የሚሻውን አታክልት፣ የሚሻውን ማዕድን አርጎ መፍጠሩ የእርሱ ሁኔታዊ አልባ ምርጫ ነው፥ "ለእነርሱ ምርጫ የላቸውም" ማለት ፍጡራን "ይህንን ሆኜ ልፈጠር" የሚል ምርጫ የላቸውም። ወንድነት እና ሴትነት የእኛ ምርጫ ሳይሆን የእርሱ ምርጫ ብቻ ነው፦ 42፥49 የሰማያትና የምድር ንግሥና የአሏህ ነው፡፡ የሚሻውን ይፈጥራል፤ ለሚሻው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ወንዶችን ይሰጣል፡፡ لِّلَّهِ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ يَهَبُ لِمَن يَشَاءُ إِنَاثًا وَيَهَبُ لِمَن يَشَاءُ الذُّكُورَ "የሚሻውን ይፈጥራል" በሚል ኃይለ ቃል "ለሚሻው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ወንዶችን ይሰጣል" የሚለው ቃል ሴት መሆን እና ወንድ መሆን የአሏህ ሁኔታዊ አልባ ምርጫ ነው፥ የእኛ ምርጫ፣ ድርሻ፣ ፈቃድ ስለሌለበት ወንድነት እና ሴትነት ቅጣት እና ሽልማት አሊያም ተጠያቂነት የለበትም። አምላካችን አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፦ 40፥7 እነዚያ "ዙፋኑን የሚሸከሙት" እና እነዚያ በዙሪያው ያሉት በጌታቸው ምስጋና ያወድሳሉ፡፡ በእርሱም ያምናሉ፡፡ الَّذِينَ يَحْمِلُونَ الْعَرْشَ وَمَنْ حَوْلَهُ يُسَبِّحُونَ بِحَمْدِ رَبِّهِمْ وَيُؤْمِنُونَ بِهِ 22፥75 አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፥ ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል። አላህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ اللَّهُ يَصْطَفِي مِنَ الْمَلَائِكَةِ رُسُلًا وَمِنَ النَّاسِ ۚ إِنَّ اللَّهَ سَمِيعٌ بَصِيرٌ "ከሩቢዩን" كَرُوبِيُّون የሚባሉት መላእክት የአሏህን ዐርሽ የሚሸከሙ ሲሆን በዐርሹ ዙሪያ ካሉት መላእክት ወደ ሰዎች የሚልካቸው መላእክት የእርሱ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነው። "ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል" ስለሚል አሏህ ከሰዎች ለመልእክተኛነት መምረጡ ይህ የእርሱ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነው፦ 2፥105 አሏህም በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ وَاللَّهُ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۚ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ 3፥74 በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አሏህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۗ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ አሏህ አንድ ሰው በነቢይነት ቢመርጠው ሆነ ባይመርጠው ሽልማት እና ቅጣት አሊያም ተጠያቂነት ስለሌለበት ይህ "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ነው። የአሏህን ምርጫ "አሚን" ብሎ መቀበል ከአርካኑል ኢማን ክፍል የሆነውን ቀደርን መቀበል ነው፥ አሏህ የእርሱን ምርጫ "አሚን" ብለው ከሚቀበሉት ምእመናን ያርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
የአሏህ ምርጫ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "ኢንቲኻብ" اِنْتِخَاب ማለት "ምርጫ"election" ማለት ነው፥ ኢንቲኻብ እራሱ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ እና "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ። ፨ "ሹሩጢይ" شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ"conditional" ማለት ሲሆን በጥቅሉ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ ምርጫ"conditional election" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ አደም በሠራው ኃጢአት "ጌታችን ሆይ! እራሳችችንን በደልን፥ ለእኛ ባትምረን እና ባታዝንልን በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን" ብሎ ተጸጸተ፦ 7፥23 «ጌታችን ሆይ! እራሳችችንን በደልን፥ ለእኛ ባትምረን እና ባታዝንልን በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን» አሉ፡፡ قَالَا رَبَّنَا ظَلَمْنَا أَنفُسَنَا وَإِن لَّمْ تَغْفِرْ لَنَا وَتَرْحَمْنَا لَنَكُونَنَّ مِنَ الْخَاسِرِينَ አደም ተጸጽቶ በንስሓ ወደ አሏህ ሲመለስ አሏህ ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፥ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፦ 2፥37 አደምም ከጌታው ቃላትን ተቀበለ፡፡ በእርሱ ላይም ጌታው ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፥ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ فَتَلَقَّىٰ آدَمُ مِن رَّبِّهِ كَلِمَاتٍ فَتَابَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّهُ هُوَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ አደም ተጸጽቶ ንስሓ ወደ አሏህ በመግባቱ አሏህ ጸጸትን በመቀበል መረጠው፦ 20፥122 ከዚያም "ጌታው መረጠው" ከእርሱም ጸጸቱን ተቀበለው መራውም፡፡ ثُمَّ اجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَتَابَ عَلَيْهِ وَهَدَىٰ "ጌታው መረጠው" የሚለው ይሰመርበት! ማንኛውም ሰው ከነበረበት ኩፍር ወይም ሺርክ አሊያም ዘንብ ወደ አሏህ በንስሓ ቢመለስ አሏህ ወደ ራሱ ለጀነት ይመርጠዋል፦ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል" የሚለው "ዓም" ሆኖ የመጣ ነው፥ "ዓም" عَامّ ማለት "ጥቅል"general" ማለት ነው። ነገር ግን "አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል" የሚለው ዓም "የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል" በሚል "ኻስ" ሆኖ እዛው ላይ መጥቷል፥ "ኻስ" خَاصّ ማለት "ተናጥል"specifical" ማለት ነው። መመራትን ሰው የሚያገኘው በማመን መሆኑ "ኻስ" ሆኖ የሚመጣ ነው፦ 22፥54 አሏህ እነዚያን ያመኑትን ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ "መሪ" ነው፡፡ وَإِنَّ اللَّهَ لَهَادِ الَّذِينَ آمَنُوا إِلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ "እነዚያን ያመኑትን" የሚለው ይሰመርበት! ያላመነው እና ንስሓ ያልገባ ሰው የሸይጧን ተከታይ ነው፥ ሸይጧን የተከተለውን ሰው ወደ ጀሀነም ይመራዋል፦ 22፥4 "እነሆ! የተከተለውን ሰው እርሱ ያጠመዋል፡፡ ወደ ነዳጅ እሳት ስቃይም ይመራዋል" ማለት በእርሱ ላይ ተጽፏል፡፡ كُتِبَ عَلَيْهِ أَنَّهُ مَن تَوَلَّاهُ فَأَنَّهُ يُضِلُّهُ وَيَهْدِيهِ إِلَىٰ عَذَابِ السَّعِيرِ ወደ ጀሀነም የሚገባ ሰው አሏህ ለጀነት ያልመረጠው በገዛ ፈቃዱ ሸይጧንን በመከተሉ ነው፥ ይህ የእኛ ጣልቃ ገብነት እና ድርሻ ያለበት የአሏህ ምርጫ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ ይባላል።
إظهار الكل...
አሏህ አንድ ሰው በነቢይነት ቢመርጠው ሆነ ባይመርጠው ሽልማት እና ቅጣት አሊያም ተጠያቂነት ስለሌለበት ይህ "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ነው። የአሏህን ምርጫ "አሚን" ብሎ መቀበል ከአርካኑል ኢማን ክፍል የሆነውን ቀደርን መቀበል ነው፥ አሏህ የእርሱን ምርጫ "አሚን" ብለው ከሚቀበሉት ምእመናን ያርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
የአሏህ ምርጫ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "ኢንቲኻብ" اِنْتِخَاب ማለት "ምርጫ"election" ማለት ነው፥ ኢንቲኻብ እራሱ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ እና "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ። ፨ "ሹሩጢይ" شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ"conditional" ማለት ሲሆን በጥቅሉ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ ምርጫ"conditional election" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ አደም በሠራው ኃጢአት "ጌታችን ሆይ! እራሳችችንን በደልን፥ ለእኛ ባትምረን እና ባታዝንልን በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን" ብሎ ተጸጸተ፦ 7፥23 «ጌታችን ሆይ! እራሳችችንን በደልን፥ ለእኛ ባትምረን እና ባታዝንልን በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን» አሉ፡፡ قَالَا رَبَّنَا ظَلَمْنَا أَنفُسَنَا وَإِن لَّمْ تَغْفِرْ لَنَا وَتَرْحَمْنَا لَنَكُونَنَّ مِنَ الْخَاسِرِينَ አደም ተጸጽቶ በንስሓ ወደ አሏህ ሲመለስ አሏህ ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፥ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፦ 2፥37 አደምም ከጌታው ቃላትን ተቀበለ፡፡ በእርሱ ላይም ጌታው ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፥ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ فَتَلَقَّىٰ آدَمُ مِن رَّبِّهِ كَلِمَاتٍ فَتَابَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّهُ هُوَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ አደም ተጸጽቶ ንስሓ ወደ አሏህ በመግባቱ አሏህ ጸጸትን በመቀበል መረጠው፦ 20፥122 ከዚያም "ጌታው መረጠው" ከእርሱም ጸጸቱን ተቀበለው መራውም፡፡ ثُمَّ اجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَتَابَ عَلَيْهِ وَهَدَىٰ "ጌታው መረጠው" የሚለው ይሰመርበት! ማንኛውም ሰው ከነበረበት ኩፍር ወይም ሺርክ አሊያም ዘንብ ወደ አሏህ በንስሓ ቢመለስ አሏህ ወደ ራሱ ለጀነት ይመርጠዋል፦ 42፥13 አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል፡፡ اللَّهُ يَجْتَبِي إِلَيْهِ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي إِلَيْهِ مَن يُنِيبُ "አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል" የሚለው "ዓም" ሆኖ የመጣ ነው፥ "ዓም" عَامّ ማለት "ጥቅል"general" ማለት ነው። ነገር ግን "አሏህ የሚሻውን ሰው ወደ እርሱ ይመርጣል" የሚለው ዓም "የሚመለስንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል" በሚል "ኻስ" ሆኖ እዛው ላይ መጥቷል፥ "ኻስ" خَاصّ ማለት "ተናጥል"specifical" ማለት ነው። መመራትን ሰው የሚያገኘው በማመን መሆኑ "ኻስ" ሆኖ የሚመጣ ነው፦ 22፥54 አሏህ እነዚያን ያመኑትን ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ "መሪ" ነው፡፡ وَإِنَّ اللَّهَ لَهَادِ الَّذِينَ آمَنُوا إِلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ "እነዚያን ያመኑትን" የሚለው ይሰመርበት! ያላመነው እና ንስሓ ያልገባ ሰው የሸይጧን ተከታይ ነው፥ ሸይጧን የተከተለውን ሰው ወደ ጀሀነም ይመራዋል፦ 22፥4 "እነሆ! የተከተለውን ሰው እርሱ ያጠመዋል፡፡ ወደ ነዳጅ እሳት ስቃይም ይመራዋል" ማለት በእርሱ ላይ ተጽፏል፡፡ كُتِبَ عَلَيْهِ أَنَّهُ مَن تَوَلَّاهُ فَأَنَّهُ يُضِلُّهُ وَيَهْدِيهِ إِلَىٰ عَذَابِ السَّعِيرِ ወደ ጀሀነም የሚገባ ሰው አሏህ ለጀነት ያልመረጠው በገዛ ፈቃዱ ሸይጧንን በመከተሉ ነው፥ ይህ የእኛ ጣልቃ ገብነት እና ድርሻ ያለበት የአሏህ ምርጫ "ኢንቲኻብ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب شُرْطِيّ ይባላል። ፨ "ገይሪ ሹሩጢይ" غَيْرِ شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ አልባ"unconditional" ማለት ሲሆን በጥቅሉ "ኢንቲኻብ ገይሪ ሹሩጢይ" اِنْتِخَاب غَيْرِ شُرْطِيّ ማለት "ሁኔታዊ አልባ ምርጫ"unconditional election" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፦ 28፥68 ጌታህም የሚሻውን ይፈጥራል፤ ይመርጣልም፡፡ ለእነርሱ ምርጫ የላቸውም፡፡ አሏህ ከማይግገባው ሁሉ ጠራ፡፡ ከሚያጋሯቸውም ላቀ፡፡ وَرَبُّكَ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ وَيَخْتَارُ ۗ مَا كَانَ لَهُمُ الْخِيَرَةُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ وَتَعَالَىٰ عَمَّا يُشْرِكُونَ "የሚሻውን ይፈጥራል" በሚል ኃይለ ቃል "ይመርጣል" የሚለው ቃል አሏህ የሚሻውን ሰው፣ የሚሻውን እንስሳ፣ የሚሻውን አታክልት፣ የሚሻውን ማዕድን አርጎ መፍጠሩ የእርሱ ሁኔታዊ አልባ ምርጫ ነው፥ "ለእነርሱ ምርጫ የላቸውም" ማለት ፍጡራን "ይህንን ሆኜ ልፈጠር" የሚል ምርጫ የላቸውም። ወንድነት እና ሴትነት የእኛ ምርጫ ሳይሆን የእርሱ ምርጫ ብቻ ነው፦ 42፥49 የሰማያትና የምድር ንግሥና የአሏህ ነው፡፡ የሚሻውን ይፈጥራል፤ ለሚሻው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ወንዶችን ይሰጣል፡፡ لِّلَّهِ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ يَهَبُ لِمَن يَشَاءُ إِنَاثًا وَيَهَبُ لِمَن يَشَاءُ الذُّكُورَ "የሚሻውን ይፈጥራል" በሚል ኃይለ ቃል "ለሚሻው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ወንዶችን ይሰጣል" የሚለው ቃል ሴት መሆን እና ወንድ መሆን የአሏህ ሁኔታዊ አልባ ምርጫ ነው፥ የእኛ ምርጫ፣ ድርሻ፣ ፈቃድ ስለሌለበት ወንድነት እና ሴትነት ቅጣት እና ሽልማት አሊያም ተጠያቂነት የለበትም። አምላካችን አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፦ 40፥7 እነዚያ "ዙፋኑን የሚሸከሙት" እና እነዚያ በዙሪያው ያሉት በጌታቸው ምስጋና ያወድሳሉ፡፡ በእርሱም ያምናሉ፡፡ الَّذِينَ يَحْمِلُونَ الْعَرْشَ وَمَنْ حَوْلَهُ يُسَبِّحُونَ بِحَمْدِ رَبِّهِمْ وَيُؤْمِنُونَ بِهِ 22፥75 አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፥ ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል። አላህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ اللَّهُ يَصْطَفِي مِنَ الْمَلَائِكَةِ رُسُلًا وَمِنَ النَّاسِ ۚ إِنَّ اللَّهَ سَمِيعٌ بَصِيرٌ "ከሩቢዩን" كَرُوبِيُّون የሚባሉት መላእክት የአሏህን ዐርሽ የሚሸከሙ ሲሆን በዐርሹ ዙሪያ ካሉት መላእክት ወደ ሰዎች የሚልካቸው መላእክት የእርሱ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነው። "ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል" ስለሚል አሏህ ከሰዎች ለመልእክተኛነት መምረጡ ይህ የእርሱ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነው፦ 2፥105 አሏህም በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ وَاللَّهُ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۚ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ 3፥74 በችሮታው (በነቢይነት) የሚሻውን ይመርጣል፡፡ አሏህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው፡፡ يَخْتَصُّ بِرَحْمَتِهِ مَن يَشَاءُ ۗ وَاللَّهُ ذُو الْفَضْلِ الْعَظِيمِ
إظهار الكل...
የረመዷን ስጦታ ረመዷን ሙባረክ ያ ሙሥሊሙን ወሙሥሊማት! በ 18 አርስት የተሰደረ መጣጥፍ በረመዷን ወር እንካችሁ ብለናል። ሊንኩን በማስፈንጠር ያግኙት! 1. ሶውም https://t.me/Wahidcom/3136 2. የጦም ትሩፋት https://t.me/Wahidcom/3470 3. ረመዷን https://t.me/Wahidcom/2727 4.. የረመዷን ወር https://t.me/Wahidcom/3107 5. የክርስትና ጦም https://t.me/Wahidcom/3176 6. የጨረቃ አቆጣጠር https://t.me/Wahidcom/2717 7. ጨረቃ እና ኮከብ https://t.me/Wahidcom/2360 8. የሚታሰሩ ሰይጣናት https://t.me/Wahidcom/2724 9. ሡሑር https://t.me/Wahidcom/2726 10. ተራዊህ https://t.me/Wahidcom/833 11. ኢዕቲካፍ https://t.me/Wahidcom/2286 12. ለይለቱል ቀድር https://t.me/Wahidcom/2289 13. መሓላ እና ማካካሻው https://t.me/Wahidcom/2336 14. ጦመኛ https://t.me/Wahidcom/3120 15. የተባረከ ወር https://t.me/Wahidcom/3707 16. ዘካቱል ማል https://t.me/Wahidcom/3126 17. ዘካቱል ፊጥር https://t.me/Wahidcom/3156 18. ተሀጁድ https://t.me/Wahidcom/3152 ሁሉም ቦታ ለሁሉም ሰው እንዲዳረስ አሰራጩ! ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
إظهار الكل...
የተባረከ ወር በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥185 የረመዷን ወር በእርሱ ውስጥ ቁርኣን ለሰዎች መሪ፣ የመመሪያ ግልጽ ማስረጃ እና ፉርቃን ሲሆን የተወረደበት ነው። شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ አምላካችን አሏህ በቁርኣን ከተገለጹት ስሞቹ አንዱ "አል-ከሪም" الْكَرِيم ሲሆን ትርጉሙ "ቸሩ" "ለጋሱ" ማለት ነው፦ 82፥6 አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ? يَا أَيُّهَا الْإِنسَانُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ الْكَرِيمِ 27፥40 እርሱ ዘንድ ረግቶ ባየውም ጊዜ «ይህ ከጌታዬ ችሮታ ነው፥ የማመሰግን ወይም የምክድ መኾኔን ሊፈትነኝ ቸረልኝ፡፡ ያመሰገነም ሰው የሚያመሰግነው ለራሱ ነው፥ የካደም ሰው ጌታዬ ከእርሱ ተብቃቂ ቸር ነው» አለ፡፡ فَلَمَّا رَآهُ مُسْتَقِرًّا عِندَهُ قَالَ هَـٰذَا مِن فَضْلِ رَبِّي لِيَبْلُوَنِي أَأَشْكُرُ أَمْ أَكْفُرُ ۖ وَمَن شَكَرَ فَإِنَّمَا يَشْكُرُ لِنَفْسِهِ ۖ وَمَن كَفَرَ فَإِنَّ رَبِّي غَنِيٌّ كَرِيمٌ "ከሪም" كَرِيم የሚለው ቃል እንደየ ዐውዱ ዘርፈ ብዙ እና መጠነ ሰፊ ትርጉም አለው፥ "የተባረከ" "የተከበረ" "ቅዱስ" "ክቡር" "ብፁዕ" "ንኡድ" "ውዱስ" "ስቡህ" "እኩት" "እጹብ" የሚል ፍቺ አለው። ለምሳሌ፦ መልአኩ ጂብሪል "ከሪም" كَرِيم ተብሏል፦  81፥19 እርሱ የ-"ክቡር" መልእክተኛ ቃል ነው፡፡ إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ እዚህ ዐውድ ላይ ጂብሪል "ክቡር" ለተባለበት የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم ሲሆን "ንኡድ"noble" ለማለት እንጂ "ለጋሽ" "ቸር" ለማለት ተፈልጎ አይደለም፥ በተመሳሳይ ነቢያችን"ﷺ" ደግሞ "ከሪም" كَرِيم ተብለዋል፦ 69፥40 እርሱ የ-"ተከበረ" መልእክተኛ ቃል ነው፡፡ إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ እዚህ ዐውድ ላይ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" "ክቡር" ለተባሉበት የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم ሲሆን "ንኡድ"noble" ለማለት እንጂ "ለጋሽ" "ቸር" ለማለት ተፈልጎ አይደለም። ስለዚህ አንድ ምንነት ወይም ማንነት "ከሪም" كَرِيم ስለተባለ አሏህ ከተወሰፈበትን ወስፍ ጋር ማምታታት አግባብ አይደለም። ቁርኣን "ከሪም" كَرِيم ተብሏል፦  56፥77 እርሱ "የከበረ" ቁርኣን ነው። إِنَّهُۥ لَقُرْءَانٌۭ كَرِيمٌۭ እዚህ አንቀጽ ላይ ቁርኣን "የተከበረ" ለተባለበት የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم ሲሆን ሌላ አንቀጽ ላይ በተለዋዋጭ ቃል "ሙባረክ" مُّبَارَك ተብሏል፦ 6፥155 ይህም ያወረድነው የኾነ "የተባረከ" መጽሐፍ ነው፡፡ وَهَـٰذَا كِتَابٌ أَنزَلْنَاهُ مُبَارَكٌ እዚህ አንቀጽ ላይ ቁርኣን "የተባረከ" ለተባለበት የገባው ቃል "ሙባረክ" مُّبَارَك ሲሆን "ሙባረክ" እና "ከሪም" የቃላት ልዩነት እንጂ የአሳብ ልዩነት የላቸውም። አትክልቶችን እና የሚታጨድን አዝመራ ፍሬ የሚበቅልበት ውኃ "ሙባረክ" مُّبَارَك ተብሏል፦ 50፥9 ከሰማይም "ቡሩክን" ውኃ አወረድን፡፡ በእርሱም አትክልቶችን እና የሚታጨድን አዝመራ ፍሬ አበቀልን፡፡ وَنَزَّلْنَا مِنَ السَّمَاءِ مَاءً مُّبَارَكًا فَأَنبَتْنَا بِهِ جَنَّاتٍ وَحَبَّ الْحَصِيدِ እዚህ አንቀጽ ላይ ውኃ "ቡሩክ(የተባረከ) ለተባለበት የገባው ቃል "ሙባረክ" مُّبَارَك ሲሆን ሌላ አንቀጽ ላይ በተለዋዋጭ ቃል "ከሪም" كَرِيم ተብሏል፦ 79፥30 ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡ وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا 79፥31 ውኃን እና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءَهَا وَمَرْعَاهَا 26፥7 ወደ ምድርም በውስጧ "ከ"መልካም" በቃይ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን?፡፡ أَوَلَمْ يَرَوْا إِلَى الْأَرْضِ كَمْ أَنبَتْنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوْجٍ كَرِيمٍ እዚህ አንቀጽ ላይ "መልካም" ለሚለው የገባው ቃል "ከሪም" كَرِيم እንደሆነ ልብ አድርግ! "ሙባረክ" እና "ከሪም" ተለዋዋጭ ቃላት እንደሆኑ ለመረዳት ከላይ የቀረቡት ናሙናዎች በቂ ማሳያ ናቸው። እዚህ ድረስ ከተግባባን የረመዷን ወር ቁርኣን የወረደበት ወር ነው፦ 2፥185 የረመዷን ወር በእርሱ ውስጥ ቁርኣን ለሰዎች መሪ፣ የመመሪያ ግልጽ ማስረጃ እና ፉርቃን ሲሆን የተወረደበት ነው። شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ "ፉርቃን" فُرْقَان ማለት "እውነት ከሐሰት፣ ትክክሉን ከስህተት፣ መልካሙን ከክፉ የሚለይ ሚዛን" ማለት ነው። "ሸህሩ ረመዷን" شَهْرُ رَمَضَان ማለት "የረመዳን ወር" ማለት ነው፥ "ረመዷን" رَمَضَان ደግሞ የዘጠነኛው ወር ስም ነው። "ረመዷን" የወር ስም እንጂ የጦም ስም አይደለም፥ ነገር ግን ይህ ወር ቁርኣን የተወረደበት ወር በመሆኑ "ሸህሩ ሙባረክ" شَهْرُ مُّبَارَك ማለትም "የተባረከ ወር" ተብሏል፦ ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 22, ሐዲስ 17 አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የተባረከው ወር ረመዷን መጣላችሁ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ أَتَاكُمْ رَمَضَانُ شَهْرٌ مُبَارَكٌ ከዚህ አንጻር "ረመዷን ሙባረክ" رَمَضَان مُّبَارَك የሚለውን በቋንቋዬ ተርጉሜ "የተባረከ ረመዷን" ብል የቃላት ልዩነት እንጂ የአሳብ ልዩነት ከሌለው "ረመዷን ከሪም" رَمَضَان كَرِيم ሲባል "መልካም ረመዷን" "የተከበረ ረመዷን" ብል የቃላት እንጂ የአሳብ ልዩነት የለውም። "ኢማን" إِيمَان የሚለውን ቃል ቁርኣን እና ሐዲስ ውስጥ በቁናህ ታገኘዋለህ፥ ቅሉ ግን የኢማን ተለዋዋጭ ቃል "ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለውን በስም መደብ ቁርኣን ውስጥ አታገኘውም። ነገር ግን ዐቂዳህ እያልን እንማራለን እናስተምራለን፥ "ሙባረክ" እና "ከሪም" የሚለውን በዚህ ስሌት እና ሒሣብ መረዳት ይቻላል። ስለዚህ "ረመዷን ሙባረክ" رَمَضَان مُّبَارَك እና "ረመዷን ከሪም" رَمَضَان كَرِيم ተለዋዋጭ ቃላት እስከሆኑ ድረስ መርጠን መጠቀም እንችላለን። "አሏሁ አዕለም! ይህ ሙግት የቋንቋን ሙግት ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ሙግት ነው። "ረመዷን ከሪም" رَمَضَان كَرِيم ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
"ኤኻድ እና ያኺድ" በሚል ርእስ ዙሪያ ዳሰሳ እና ሐተታ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/t2OwjlluSN0?si=Mm8ABvNu3B3XMXlT ያዳመጣችሁ ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!
إظهار الكل...
ሶሉ ዐላ ነቢይና"ﷺ" በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡ 94፥4 መወሳትህንም ለአንተ ከፍ አድርገንልሀል። وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ አንድ ሙሥሊም በአዛን፣ በቂያም፣ በሸሀዳህ "ሙሐመድ የአሏህ መልእክተኛ ነው" ብለን እናውጃለን፥ አምላካችን አሏህ መወሳት ለነቢያችን"ﷺ" ከፍ አድርጎላቸዋል። እንዲሁ ስማቸው ሲወሳ "የአሏህ ረድኤት እና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን" በማለት መወሳትን ከፍ እናደርግላቸዋለን፦ 94፥4 መወሳትህንም ለአንተ ከፍ አድርገንልሀል። وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ "አሏሁመ ሶሊ ዐላ ሙሐመድ ወአሊ ሙሐመድ" ٱللّٰهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَآلِ مُحَمَّدٍ "ሶለላሁ ዐለይሂ ወሠለም" صَلَّى ٱللَّٰهُ عَلَيْهِ وَسَلَّم ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
"የአብርሃሙ ሥላሴ" በሚል ርእስ ዙሪያ ዳሰሳ እና ሐተታ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/GMhX99TrVJI?si=eeVZkONW3y3GIzvW ያዳመጣችሁ ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!
إظهار الكل...
በስልጥኛ ደርሥ ተለቋል። አንብቡ፦ https://t.me/wahidcomselitiy/26
إظهار الكل...
የሃይማኖት ንጽጽር ኮርስ በወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" 11ኛ ዙር የሙቃረናህ ደርሥ! "ሙቃረናህ" مُقَارَنَة የሚለው ቃል "ቃረነ" قَارَنَ ማለትም "አነጻጸረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ንጽጽር" ማለት ነው፥ ሙቃረናህ የሃይማኖት ንጽጽር"Comparative Religion" ሲሆን በእሥልምና እና በክርስትና መካከል ያለው የሥነ-መለኮት አንድነት እና ልዩነት እየተነጻጸረ የሚቀርብበት ጥናት ነው። ደርሡ (ትምህርቱ) የሚፈጀው 7 ወር ኢንሻሏህ ሲሆን ሁለት ተርም አለው። ፨ የመጀመሪያው ተርም ዐጽመ አሳብ በፈጣሪ እሳቦት ላይ የሚያውጠነጥነው፦ በሥላሴ"trinity" እሳቤ፣ በነገረ-ክርስቶስ ጥናት"Christology"፣ በነገረ-ማርያም ጥናት"Mariology"፣ በነገረ-መላእክት ጥናት"angelology"፣ በነገረ-ምስል ጥናት"Iconlogy" ላይ ነው። ፨ የሁለተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በቅዱሳን መጽሐፍት ላይ የሚያውጠነጥነው፦ በአህሉል ኪታብ"People of the Book"፣ በመጽሐፍት"scriptures"፣ በመጽሐፍ አጠባበቅ"preservation"፣ በመጽሐፍት ልኬት"Standardization"፣ በባይብል ግጭት"Contradiction"፣ በኦሪት"Torah"፣ በወንጌል"Gospel" ላይ ነው። አባሪ ኮርሶች፦ 1. ዐቂዳህ"creed" 2. ሥነ ምግባር"ethics" 3. ሥነ አመክንዮ"logic" 4. ሥነ ልቦና"psychology" 5. ሥነ ቋንቋ"linguistics" ናቸው። ለመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩት አድሚናት በውስጥ ያናግሩ! ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa እኅት አበባ፦ http://t.me/selemtewa ቦታ ሳይያዝ ይመዝገቡ! መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንልዎ! ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
إظهار الكل...
"ኑ እንውረድ" በሚል ደርሥ ተለቊል፥ በነገረ ሥላሴ"triadology" ከሚጠቀሱ ተወዳጆች ጥቅሳት አንዱ ዘፍጥረት 11፥6-7 ነው። በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/Ihf-WhiGhHk?si=Sko8EK2kj8qupQBd
إظهار الكل...
ሐውቀላህ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 11፥73 «ከአሏህ ትዕዛዝ ትደነቂያለሽን የአላህ ችሮታና በረከቶቹ በእናንተ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ይሁን "እርሱ አሏህ ምስጉን ክቡር ነውና» አሉ፡፡ قَالُوا أَتَعْجَبِينَ مِنْ أَمْرِ اللَّهِ ۖ رَحْمَتُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُهُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الْبَيْتِ ۚ إِنَّهُ حَمِيدٌ مَّجِيدٌ "መጅድ" مَجْد የሚለው ቃል "መጀደ" مَجَدَ ማለትም "አከበረ" "ከፍ አረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ክብር" "ከፍታ" ማለት ነው። በቁርኣን ከተጠቀሱ የአሏህ የተዋቡ ስሞች መካከል “አል-መጂድ” الْمَّجِيد ሲሆን “እጅግ በጣም የተከበረ” ማለት ነው፦ 11፥73 «ከአላህ ትዕዛዝ ትደነቂያለሽን የአላህ ችሮታና በረከቶቹ በእናንተ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ይሁን "እርሱ አሏህ ምስጉን ክቡር ነውና» አሉ፡፡ قَالُوا أَتَعْجَبِينَ مِنْ أَمْرِ اللَّهِ ۖ رَحْمَتُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُهُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الْبَيْتِ ۚ إِنَّهُ حَمِيدٌ مَّجِيدٌ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 48 አቡ ሑመይድ አሥ-ሣዒዲይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ”ሰዎች፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! በእርሶ ላይ እንዴት ረድኤት እናውርድ? አሉ፤ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አሏህ ሆይ! ረድኤትን በኢብራሂም ቤተሰብ ላይ እንዳወረድክ በሙሐመድ፣ በባልተቤቶቹ እና በዝርዮቹ ላይ አውርድ! በረከትን በኢብራሂም ቤተሰብ ላይ እንዳወረድክ በሙሐመድ፣ በባልተቤቶቹ እና በዝርዮቹ ላይ አውርድ! አንተ የተመሰገንክ እና የተከበርክ ነህ" አሉ። أَخْبَرَنِي أَبُو حُمَيْدٍ السَّاعِدِيُّ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّهُمْ قَالُوا يَا رَسُولَ اللَّهِ كَيْفَ نُصَلِّي عَلَيْكَ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ قُولُوا اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَأَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَأَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ ‏”‌‏.‏ ይህ አሏህ በአምልኮ ከፍ ከፍ ማድረግ "ሐውቀላህ" حَوْقَلَة ይባላል። ይህም ተዝኪራ "ላ ሀውለ ወላ ቁውወተ ኢላ ቢላህ" لا حَوْلَ وَلا قُوَّةَ إِلا بالله ነው። "ላ ሀውለ ወላ ቁውወተ ኢላ ቢላህ" ማለት "በአሏህ ቢሆን እንጂ ብልሃት ሆነ ኃይል የለም" ማለት ነው፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 33, ሐዲስ 170 አቢ ዘር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ"፦ "ከጀነት ሃብት አንዱን ሃብት ልጠቁምህን? አሉኝ። እኔም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! አዎ" አልኩኝ። እርሳቸውም፦ "በአሏህ ቢሆን እንጂ ብልሃት ሆነ ኃይል የለም" ነው፥ አሉ"። عَنْ أَبِي ذَرٍّ، قَالَ قَالَ لِي رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏"‏ أَلاَ أَدُلُّكَ عَلَى كَنْزٍ مِنْ كُنُوزِ الْجَنَّةِ ‏"‏ ‏.‏ قُلْتُ بَلَى يَا رَسُولَ اللَّهِ ‏.‏ قَالَ ‏"‏ لاَ حَوْلَ وَلاَ قُوَّةَ إِلاَّ بِاللَّهِ ‏ "አሏሁመ ሶሊ ዐላ ሙሐመድ ወአሊ ሙሐመድ" ٱللّٰهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَآلِ مُحَمَّدٍ "ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሠለም" صَلَّى ٱللَّٰهُ عَلَيْهِ وَسَلَّم ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
"ከእኛ እንደ አንዱ" በሚል ደርሥ ተለቊል፥ በነገረ ሥላሴ"triadology" ከሚጠቀሱ ተወዳጆች ጥቅሳት አንዱ ዘፍጥረት 3፥22 ነው። በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/t8ZAOLTG-6A?si=OwC0Yl-DKEgRK32D ያዳመጣችሁ ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!
إظهار الكل...
"እንፍጠር" በሚል ትምህርት ተለቋል። ፈጣሪ “እንፍጠር” ሲል ምን ማለት ነው? "እንፍጠር" ያለው ማን ነው? "እንፍጠር" ያለው ለእነማን ነው? በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/EJA9f_jrPwE?si=ut1YQ8G7a4DatjVc ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
إظهار الكل...
ሰማይ እና ምድር በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 41፥11 ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ اسْتَوَىٰ إِلَى السَّمَاءِ وَهِيَ دُخَانٌ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ائْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًا قَالَتَا أَتَيْنَا طَائِعِينَ አምላካችን አሏህ ሰማይን ጭስ"gas" አርጎ ከፈጠራት በኃላ በጭስ ደረጃ እያለች ለእርሷ እና ለምድር፦ "ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ" አላቸው፥ እነርሱም፦ "ታዛዦች ኾነን መጣን" አሉ፦ 41፥11 ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ اسْتَوَىٰ إِلَى السَّمَاءِ وَهِيَ دُخَانٌ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ائْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًا قَالَتَا أَتَيْنَا طَائِعِينَ አሏህ ሰማይ እና ምድርን «ኑ» ሲላቸው እነርሱም፦ «ታዛዦች ኾነን መጣን» ማለታቸው የሚያስቅ እና የሚያሳልቅ ከሆነ እንግዲያውስ ያህዌህ በባይብል ምድርን እና ሰማያትን ሲጠራቸው በአንድነት እንደሚቆሙ ይናገራል፦ ኢሳይያስ 48፥13 እጄም ምድርን መሥርታለች ቀኜም ሰማያትን ዘርግታለች፥ በጠራኋቸው ጊዜ በአንድነት ይቆማሉ። אַף־יָדִי֙ יָ֣סְדָה אֶ֔רֶץ וִֽימִינִ֖י טִפְּחָ֣ה שָׁמָ֑יִם קֹרֵ֥א אֲנִ֛י אֲלֵיהֶ֖ם יַעַמְד֥וּ יַחְדָּֽו׃ "በአንድነት" ለሚለው የገባው ቃል "የሕዳው" יַחְדָּֽו ሲሆን "አንድ ላይ"together" ማለት ነው፥ የሚጠራቸው መቼ ነው? በአንድ ላይ ሲቆሙ የሚቆሙት አየር ላይ ነው ወይስ ሥፍራ አላቸው? እንኳን ሰማይ እና ምድር ከዋክብትም ሲጠራቸው፦ "ፈጣሪያችን ወደ አንተ መጣን" ይላሉ፦ መጽሐፈ ባሮክ 3፥29(1980 ዕትም) "ይጠራቸዋል እርሱን የሚመስል ሌላ የለምና "ፈጣሪያችን ወደ አንተ መጣን" ይላሉ። Book of Baruch 3፥35 when he calls them, they answer፦ "Here we are" they shine to delight their Creator" "ወሒድ ይህ እኮ ፈሊጣዊ አገላለጽ"idiomatic expression" ነው" ካላችሁ እንግዲያውስ "ኢስጢላሕ" اِصْطِلَاح ማለት "ፈሊጣዊ አገላለጽ" ማለት ነውና አሏህ ሰማይ እና ምድርን «ኑ» ሲላቸው እነርሱም፦ «ታዛዦች ኾነን መጣን» ማለታቸው የሚያስቅ እና የሚያሳልቅ ነገር ሳይሆን ኢስጢላሕ ነው። ቢያንስ ቢያንስ የራሳችሁ መጽሐፍ አታነቡምን? አለዚያ እንደዚህ በሰፈራችሁት ቁና መሰፈራችሁ አይቀርም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
"ኤሎሂም" በሚል ትምህርት ተለቋል። "ኤሎሂም" ማለት ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ሲሆን ፈጣሪ “ኤሎሂም” ሲባል ምን ማለት ነው? "አማልክት" የተባሉት ሥላሴ ከሆኑ ሥላሴ አማልክት ናቸው? እነዚህ የመሳሰሉ እሳቦት ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/DYDqQqemDFk?si=qYY0t9HgIv-F0cvi ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
إظهار الكل...
"እጆች" የሚለው ቃል "እጅ" ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "ጭቃ" ማለት "የውኃ እና የአፈር ቅልቅል ነው። ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጁ ለውሶ ሠራው፦ ኢዮብ 10፥8 እጅህ ለወሰችኝ ሠራችኝም። יָדֶ֣יךָ עִ֭צְּבוּנִי וַֽיַּעֲשׂ֑וּנִי ኢዮብ 33፥6 እኔ ደግሞ ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ። מֵ֝חֹ֗מֶר קֹרַ֥צְתִּי גַם־אָֽנִי׃ ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጆቹ ካበጀ እና ከሠራ እጆቹ ቀኝ እና ግራ ናቸው፥ ምክንያቱም ፈጣሪ ቀኝ እና ግራ ካለው ቀኝ እና ግራ እጆች አሉት፦ 1ኛ ነገሥት 22፥19 ሚክያስም አለ፦ እንግዲህ የያህዌህን ቃል ስማ! ያህዌህ በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ "በቀኙ" እና "በግራው" ቆመው አየሁ። וַיֹּ֕אמֶר לָכֵ֖ן שְׁמַ֣ע דְּבַר־יְהוָ֑ה רָאִ֤יתִי אֶת־יְהוָה֙ יֹשֵׁ֣ב עַל־כִּסְאֹ֔ו וְכָל־צְבָ֤א הַשָּׁמַ֙יִם֙ עֹמֵ֣ד עָלָ֔יו מִימִינֹ֖ו וּמִשְּׂמֹאלֹֽו׃ እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀኝ" ለሚለው የገባው ቃል "የሚን" יָמִין ሲሆን "ግራ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሸሙል" שְׂמֹאול ነው። "ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱም "ፈጣሪ እጅ አለው" ሲባል የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም" ብለዋል፦ ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30 “ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”። እርማችሁን አውጡ! ሠለስቱ ምዕት ፈጣሪ እጅ እንዳለው እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጆች እንዳሉት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦ መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62 “እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”። ስለዚህ "አሏህ እጆች አሉት" ሲባል በደምሳሳው የምትተቹ ሰዎች መጽሐፋችሁ ላይ ያህዌህ እጆች እንዳሉት ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን? የመነቸከ ሙግት ከምትሟገቱ ይልቅ የፋፋና የዳበረ እንዲሁ የላመና የጣመ ሙግት ለማደራጀት እና ለማዋቀር መሞከር አይሻላችሁምን? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
የአሏህ እጆች በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦ 42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦ 76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም። ይህንን መረዳት ይዘን ቁርኣን ላይ አምላካችን አሏህ እጆች እንዳሉት ይናገራል፦ 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ "ሁለት እጆች" ለሚለው የገባው "የደይየ" ِيَدَىَّ ሲሆን ሙሰና"dual" እንደሆነ ልብ አድርግ! አምላካችን አሏህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ እጆች አሉት፥ የእርሱ እጆች ፍጥረታዊ ሳይሆኑ መለኮታዊ እንዲሁ ሰዋዊ ሳይሆኑ አምላካዊ ናቸው። የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው፦ ሚስካቱል መሷሒብ መጽሐፍ 18, ሐዲስ 30 ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር ኢብኑ አል ዓሲ እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ፍትኸኞች አሏህ ዘንድ በብርሃን መንበሮች ላይ ከአር ረሕማን በስ ተቀኝ በኩል ይሆናሉ፥ "ሁለቱም እጆቹ ቀኝ ናቸው"። وَعَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: إِنَّ الْمُقْسِطِينَ عِنْدَ اللَّهِ عَلَى مَنَابِرَ مِنْ نُورٍ عَنْ يَمِينِ الرَّحْمَنِ وَكِلْتَا يَدَيْهِ يمينٌ "የሚን" يَمِين ማለት "ጠንካራ" "አውንታዊ" "ሙሉነት" በሚል ትርጉም ይመጣል፥ "ሸማል" شِّمَال ማለት "ደካማ" "አሉታዊ" "ጎዶሎነት" በሚል ትርጉም ይመጣል። በዐማርኛችን "በቀኝ አውለኝ" እና "ግራ ያጋባል" በሚል ዐውድ ቀኝ እና ግራ አውንታዊ እና አሉታዊ ነገር ለማመልከት ይመጣሉ፥ እሩቅ ስንሄድ "left" የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "ደካማ"weak" ማለት ነው። ስለዚህ "የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው" ማለት "ጠንካራ፣ አውንታዊ፣ ሙሉ ናቸው" ማለት ነው እንጂ አሏህ ቀኝ እና ግራ የሆኑ እጆች አሉት፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52 ሐዲስ 7 ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ዐዘ ወጀል በፍርዱ ቀን ሰማያትን ይይዛል፥ ከዚያም በቀኝ እጁ ያረግና፦ "እኔ ንጉሡ ነኝ፥ ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል፥ ከዚያም ምድርን በግራ እጁ አድርጎ፦ "ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል። عَبْدُ اللَّهِ بْنُ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ يَطْوِي اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ السَّمَوَاتِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ثُمَّ يَأْخُذُهُنَّ بِيَدِهِ الْيُمْنَى ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ثُمَّ يَطْوِي الأَرَضِينَ بِشِمَالِهِ ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ‏"‏ ‏.‏ "በቀኝ እጁ" እና "በግራ እጁ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! የእርሱን እጆች ትርጉም በመስጠት ሳናራቁጥ እና ከፍጡራን እጆች ጋር ሳናነጻጽር እርሱ በነገረን መሠረት እንቀበላለን። ወደ ባይብሉ ስንገባ ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር ያበጀው በእጆቹ ነው፦ መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም። יָדֶ֣יךָ עָ֭שׂוּנִי וַֽיְכֹונְנ֑וּנִי ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር "አበጀው"። וַיִּיצֶר֩ יְהוָ֨ה אֱלֹהִ֜ים אֶת־הָֽאָדָ֗ם עָפָר֙ מִן־הָ֣אֲדָמָ֔ה
إظهار الكل...
እርማችሁን አውጡ! ሠለስቱ ምዕት ፈጣሪ እጅ እንዳለው እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጆች እንዳሉት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦ መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62 “እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”። ስለዚህ "አሏህ እጆች አሉት" ሲባል በደምሳሳው የምትተቹ ሰዎች መጽሐፋችሁ ላይ ያህዌህ እጆች እንዳሉት ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን? የመነቸከ ሙግት ከምትሟገቱ ይልቅ የፋፋና የዳበረ እንዲሁ የላመና የጣመ ሙግት ለማደራጀት እና ለማዋቀር መሞከር አይሻላችሁምን? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
የአሏህ እጆች በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦ 42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦ 76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም። ይህንን መረዳት ይዘን ቁርኣን ላይ አምላካችን አሏህ እጆች እንዳሉት ይናገራል፦ 38፥75 አሏህም «ኢብሊሥ ሆይ! "በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ "ሁለት እጆች" ለሚለው የገባው "የደይየ" ِيَدَىَّ ሲሆን ሙሰና"dual" እንደሆነ ልብ አድርግ! አምላካችን አሏህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ እጆች አሉት፥ የእርሱ እጆች ፍጥረታዊ ሳይሆኑ መለኮታዊ እንዲሁ ሰዋዊ ሳይሆኑ አምላካዊ ናቸው። የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው፦ ሚስካቱል መሷሒብ መጽሐፍ 18, ሐዲስ 30 ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር ኢብኑ አል ዓሲ እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ፍትኸኞች አሏህ ዘንድ በብርሃን መንበሮች ላይ ከአር ረሕማን በስ ተቀኝ በኩል ይሆናሉ፥ "ሁለቱም እጆቹ ቀኝ ናቸው"። وَعَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: إِنَّ الْمُقْسِطِينَ عِنْدَ اللَّهِ عَلَى مَنَابِرَ مِنْ نُورٍ عَنْ يَمِينِ الرَّحْمَنِ وَكِلْتَا يَدَيْهِ يمينٌ "የሚን" يَمِين ማለት "ጠንካራ" "አውንታዊ" "ሙሉነት" በሚል ትርጉም ይመጣል፥ "ሸማል" شِّمَال ማለት "ደካማ" "አሉታዊ" "ጎዶሎነት" በሚል ትርጉም ይመጣል። በዐማርኛችን "በቀኝ አውለኝ" እና "ግራ ያጋባል" በሚል ዐውድ ቀኝ እና ግራ አውንታዊ እና አሉታዊ ነገር ለማመልከት ይመጣሉ፥ እሩቅ ስንሄድ "left" የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "ደካማ"weak" ማለት ነው። ስለዚህ "የአሏህ እጆች ቀኝ ናቸው" ማለት "ጠንካራ፣ አውንታዊ፣ ሙሉ ናቸው" ማለት ነው እንጂ አሏህ ቀኝ እና ግራ የሆኑ እጆች አሉት፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52 ሐዲስ 7 ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህም መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ዐዘ ወጀል በፍርዱ ቀን ሰማያትን ይይዛል፥ ከዚያም በቀኝ እጁ ያረግና፦ "እኔ ንጉሡ ነኝ፥ ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል፥ ከዚያም ምድርን በግራ እጁ አድርጎ፦ "ትዕቢተኞች የት አሉ? ኩሩዎች የት አሉ?" ይላል። عَبْدُ اللَّهِ بْنُ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ يَطْوِي اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ السَّمَوَاتِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ثُمَّ يَأْخُذُهُنَّ بِيَدِهِ الْيُمْنَى ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ثُمَّ يَطْوِي الأَرَضِينَ بِشِمَالِهِ ثُمَّ يَقُولُ أَنَا الْمَلِكُ أَيْنَ الْجَبَّارُونَ أَيْنَ الْمُتَكَبِّرُونَ ‏"‏ ‏.‏ "በቀኝ እጁ" እና "በግራ እጁ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! የእርሱን እጆች ትርጉም በመስጠት ሳናራቁጥ እና ከፍጡራን እጆች ጋር ሳናነጻጽር እርሱ በነገረን መሠረት እንቀበላለን። ወደ ባይብሉ ስንገባ ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር ያበጀው በእጆቹ ነው፦ መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም። יָדֶ֣יךָ עָ֭שׂוּנִי וַֽיְכֹונְנ֑וּנִי ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር "አበጀው"። וַיִּיצֶר֩ יְהוָ֨ה אֱלֹהִ֜ים אֶת־הָֽאָדָ֗ם עָפָר֙ מִן־הָ֣אֲדָמָ֔ה "እጆች" የሚለው ቃል "እጅ" ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "ጭቃ" ማለት "የውኃ እና የአፈር ቅልቅል ነው። ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጁ ለውሶ ሠራው፦ ኢዮብ 10፥8 እጅህ ለወሰችኝ ሠራችኝም። יָדֶ֣יךָ עִ֭צְּבוּנִי וַֽיַּעֲשׂ֑וּנִי ኢዮብ 33፥6 እኔ ደግሞ ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ። מֵ֝חֹ֗מֶר קֹרַ֥צְתִּי גַם־אָֽנִי׃ ፈጣሪ ሰውን ከጭቃ በእጆቹ ካበጀ እና ከሠራ እጆቹ ቀኝ እና ግራ ናቸው፥ ምክንያቱም ፈጣሪ ቀኝ እና ግራ ካለው ቀኝ እና ግራ እጆች አሉት፦ 1ኛ ነገሥት 22፥19 ሚክያስም አለ፦ እንግዲህ የያህዌህን ቃል ስማ! ያህዌህ በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ "በቀኙ" እና "በግራው" ቆመው አየሁ። וַיֹּ֕אמֶר לָכֵ֖ן שְׁמַ֣ע דְּבַר־יְהוָ֑ה רָאִ֤יתִי אֶת־יְהוָה֙ יֹשֵׁ֣ב עַל־כִּסְאֹ֔ו וְכָל־צְבָ֤א הַשָּׁמַ֙יִם֙ עֹמֵ֣ד עָלָ֔יו מִימִינֹ֖ו וּמִשְּׂמֹאלֹֽו׃ እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀኝ" ለሚለው የገባው ቃል "የሚን" יָמִין ሲሆን "ግራ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሸሙል" שְׂמֹאול ነው። "ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱም "ፈጣሪ እጅ አለው" ሲባል የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም" ብለዋል፦ ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30 “ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።
إظهار الكل...
"ሥሉስ አምላክ" በሚል ትምህርት ተለቋል። “ሥሉስ” ማለት “ሥስት”three" ማለት ሲሆን "ሥሉስ አምላክ" ማለት "ሦስት አምላክ" ማለት ነው። ሥላሴአውያን "አምላክ ሦስት ነው" ብለው በትውፊታቸው ማስቀመጣቸው ዳሰናል። ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/iZuSQVwoI3A?si=8wQKlLznMBEH-fOd ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!
إظهار الكل...
ትራይፎም አምላክ እና መልአክ የተለያዩ ምንነቶች እንደሆነ ሲነግረው ዮስጦስም የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል የሚመጣው ሌላው አምላክ ኢየሱስ እንጂ የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የተባለው አንድ አምላክ አብ እንዳይደለ ነግሮታል፦ "አንተ እንዳልከው "ሁለቱ መልአክ እና አምላክ ነበሩ" ቢሆን በጣም ትንሽ ዕውቀት ያለው ሰው ካልሆነ በቀር፦"የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል ላይ ታየ" ብሎ ለማስረገጥ አይደፈርም"። Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60. ዮስጦስ የጂፒተር ልጆች ለሚባሉት ለግሪካውያን የአምላክ በኵር የሆነው ቃል ያለ ተራክቦ መገኘት "እናንተ የጂፒተር ልጆችን ከምታምኑባቸው ጋር ተመሳሳይን እንጂ የተለያየ ነገር አላመጣንም" በማለት ዓይኑን አፍጦ እና ጥርሱን አግጦ ትምህርቱ ከአማውያን እንደሚመሳሰል ተናግሯል፦ "እንዲሁ የአምላክ በኵር የሆነው ቃል ያለ ተራክቦ መገኘት እና መምህራችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቀለ፣ ሞተ፣ ተነሳ እና ወደ ሰማይ ዐረገ ስንል እናንተ የጂፒተር ልጆችን ከምታምኑባቸው ጋር ተመሳሳይን እንጂ የተለያየ ነገር አላመጣንም"። The Ante-Nicene Fathers: The first Apology of justin chapter 21 እንግዲህ ሐዋርያት "አንድ አምላክ አብ ነው" ብለው ስላስተማሩ "አሐዳውያን"unitarian" የነበሩ ሲሆን ከሐዋርያት ቀጥለው የመጡት አበው የሄሌናዊውን ዐረማዊነት በመቀየጥ ከአንዱ አምላክ ከአብ ሌላ ኢየሱስን ሁለተኛ እና ሌላ አምላክ በማድረጋቸው "ክልዔታውያን"Binitarian" ነበሩ። የክርስትና ታሪክ ምሁር ኤድዋርድ ጊቦን "History of christianity" በተባለው መጽሐፋቸው ላይ ስለ ክርስትና ዐረማዊነት"paganism" እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ "አረማዊነት በክርስትና ድል ቢነሳም ክርስትናም በዚያው መጠን በአረማዊነት ተበክሏል"። History of christianity (Edward Gibbon) page XVI(16) ከዚህ ሁሉ ውዝግብ በኃላ አምላካችን አሏህ ቁርኣንን በነቢያች"ﷺ" ላይ እነዚያን "ፈጣሪ ልጅ ወልዷል" ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው፦ 18፥4 እነዚያንም «አሏህ ልጅን ወልዷል» ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው፡፡ وَيُنذِرَ الَّذِينَ قَالُوا اتَّخَذَ اللَّهُ وَلَدًا "ፈጣሪ ልጅ ወልዷል" የሚለው ይህ የዐረማዊ ትምህርት ዓለም ላይ ያለውን ሁለት ቢልዮን ክርስቲያን የሚያወዛግብ ስለሆነ ቁርኣን ይህንን ለማስጠንቀቅ መውረዱ ተገቢ ነው። አሏህ አንድ ነው፥ አሏህ የሁሉ መጠጊያ ነው፦ 114፥1 በል «እርሱ አሏህ አንድ ነው»፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ 112፥2 «አሏህ የሁሉ መጠጊያ ነው»፡፡ اللَّهُ الصَّمَدُ እርሱ የሁሉ መጠጊያ ከሆነ ጊዜን እና ቦታን ያካበበ ፈጣሪ በጊዜ እና በቦታ ውስጥ ገብቶ እና ተወልዶ በአጭር ቁመት እና በጠባብ ደረት አይወሰንም፥ በእርሱ ባሕርይ መውለድ እና መወለድ ስለሌለ አልወለደም አልተወለደምም፦ 112፥3 «አልወለደም አልተወለደምም»፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ 114፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም»። وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ "ኩፉው" كُفُو ማለት "ወደር" "እኩያ" "አቻ" "ቢጤ" "አምሳያ" "ተፎካካሪ" ማለት ሲሆን እርሱ የሚተካከለው አቻ እና እኩያ እንዲሁ የሚመሳሰለው አምሳያ እና ቢጤ ከሌለው ምንም ልጅን አልወለደም፥ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፦ 23፥91 አሏህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ ከእርሱ ጋር ሌላ ወይም ሁለተኛ አምላክ ቢኖር ኖሮ በመካከላቸው መለያየት ኖሮ ከፊሉ በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፥ አሏህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፦ 23፥91 ያን ጊዜ ሌላ አምላክ በነበረ አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር፡፡ ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፡፡ አሏህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡ إِذًا لَّذَهَبَ كُلُّ إِلَـٰهٍ بِمَا خَلَقَ وَلَعَلَا بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! እኛንም በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱ ሙሥሊም ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...
ሁለተኛ አምላክ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 23፥91 አሏህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ "ክርስትና" የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የሰየመው አግናጢዮስ ዘአንጾኪያያ በ 110 ድኅረ-ልደት ነው። ክርስትና በአውሮፓ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው፥ ክርስትና የየአውሮፓ ግሪክ ወሮም"Graeco-Roman" ፍልስፍና እና የኢየሱስ ትምህርት ቅይጥ ነው። የክርስትና ታሪክ ምሁር አዶልፍ ሃርናክ "Outlines of the History of Dogma" በተባለው መጽሐፋቸው ላይ ክርስትና ሥሩን በሄሌናውነት"hellenism" አፈር ውስጥ እንዴት እንደሰደደ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ "ክርስትና ሥሩን በሄሌናዊነት አፈር ውስጥ ሰደደ፥ በዚህም ምክንያት ለአብዛኞቹ ክርስቲያኖች ምሥጢር ሆነ"። Outlines of the History of Dogma(Adolf Harnack) Page 194 በሄለናዊ ግሪክ ሥነ-ተረት"hellenistic Greek mythology" ስለ አማልክት ያላቸው እሳቦት "ዙስ" Ζεύς የሄርሜስ አባት ሲሆን ማዕረጉ "ሆ ቴዎስ ሆ ፓትሮስ" Ο Θεός ο Πατρὸς ነው፥ "ሆ ቴዎስ ሆ ፓትሮስ" ማለት "አምላክ አባት"God the father" ማለት ነው። "ሄርሜስ" Ἑρμῆς ደግሞ የዙስ ልጅ ሲሆን በሰማይ እና በምድር መካከል ያለ መካከለኛ "መልእክተኛ" ነው። ይህ መልእክተኛው ልጅ ማዕረጉ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዎስ" Ο Θεός ο γιος ነው፥ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዎስ" ማለት "አምላክ ልጅ"God the son" ማለት ነው። አረማውያን አምላኪዎች በሊቃኦንያ ከተማ "አማልክት ሰዎችን መስለው ወደ እኛ ወርደዋል" በማለት በርናባስንም "ዙስ" ጳውሎስ "ሄርሜስ" አሉዋቸው፥ የድያ ካህን እና ሕዝቡ መሥዋዕት ሊሠውላቸው ወደዱ፦ የሐዋርያት ሥራ 14፥12 በርናባስንም "ዙስ" አሉት፤ ጳውሎስንም እርሱ በመናገር ዋና ስለ ነበረ "ሄርሜስ" አሉት። ἐκάλουν τε τὸν Βαρνάβαν Δία, τὸν δὲ Παῦλον Ἑρμῆν, ἐπειδὴ αὐτὸς ἦν ὁ ἡγούμενος τοῦ λόγου. ዙስ በንግግር ሳይናገር ከእርሱ ተልእኮ የሚናገር መልእክተኛ ሄርሜስን እንደሚልክ በተመሳሳይ የማይናገረውን በርናባስን "ዙስ" የሚናገረውን ጳውሎስን "ሄርሜስ" የማለታቸው ምክንያት ይህ ነው፥ "ዙስ" Ζεύς በሮማውያን "ጁፒተር" ሲባል "ሄርሜስ" Ἑρμῆς ደግሞ በሮማውያን "ሜርኩርይ" ይባላል። ከ 20 ቅድመ ልደት እስከ 50 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረ ፊሎስ ዘእስክንድርያ የግሪክን ፍልስፍና ከአይሁድ ትምህርት ጋር የሚቀይጥ አይሁዳዊ ፈላስፋ እና መካከለኛ አፍላጦናዊነትን"middle platonism" የሚያቀነቅን የነበረ ሲሆን ስለ ሎጎስ እንዲህ ይላል፦ "ሎጎስ የአምላክ የበኵር ልጅ እና የአምላክ መልአክ ነው"። Frederick Copleston, A History of Philosophy, Volume 1, Continuum, (2003), pp. 458–462. "ዲዩቴሮ ቴዎስ" δεύτερο Θεός ማለት "ሁለተኛ አምላክ" ማለት ሲሆን ይህ ሄለናዊ ፊሎስ ሎጎስን "ሁለተኛ አምላክ ነው" ብሎ ያስተምር ነበር፦ "በአምላክ የተነገረው ይህ የንግግር ዓረፍተ ነገር በጣም ተገቢ እና ምንም ውሸት የሌለበት ነበር፥ ሟች የሆነ ነገር የአጽናፈ ዓለም ታላቁ አባት በሆነው ምሳሌ ሊፈጠር አይችልምና። ነገር ግን(የተፈጠረው) የታላቁ ኑባሬ ቃል በሆነው "በሁለተኛው አምላክ" ምሳሌ በኃላ ነው"። Philo: Questions and Answers on Genesis, Chapter 2 Number 62 "ሁለተኛው አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! የእስክንድሪያው አርጌንስ ደግሞ ኢየሱስን "ሁለተኛ አምላክ" ብሎ ያስተምር ነበር፦ "ቢሆንም እኛ "ሁለተኛ አምላክ" ብለን ልንጠራው እንችላለን፥ "ሁለተኛ አምላክ" በሚለው ቃል ስንጠራው ሌሎችን በጎነቶችን የማካተት ችሎታ ካለው በጎነት በቀር ምንም ማለት እንዳልሆነ ይወቁ። Origen Against(Contra) Celsum, Book 5 chapter 39 "ሁለተኛው አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! "ሄቴሮ ቴዎስ" ἕτερο Θεός ማለት "ሌላ አምላክ" ማለት ሲሆን ዮስጦስ ሰማዕቱ ትራይፎ ለሚባለው አይሁዳዊ ጓደኛው ኢየሱስን "ሌላ አምላክ" ብሎታል፦ "መጻሕፍትን ስለ ተረዳችሁ ላሳምናችሁ እሞክራለሁ፥ እኔ ከምለው ነገር አለ እና አለ ከተባለው፣ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ የሚገዛ "ሌላ አምላክ" እና ጌታ አለ። እርሱም መልአክም ተብሎም ተጠርቷል"። Justin Martyr, Dialogue with Trypho, chapter 56 "ሌላ አምላክ" የተባለው ኢየሱስ "ለሁሉን ነገር ፈጣሪ" ለተባለው ለአብ ይገዛል፥ ዮስጦስ ይህንን ሌላ አምላክ መልአክ ተብሎ የተጠራ እና ለሙሴ የተናገረው አምላክ ብሎ የጠራው ከሁሉ ነገር ፈጣሪ ከሆነው ማንነት ለይቶታል፦ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ እና የያዕቆብም አምላክ የነበረው ለሙሴ የተናገረው አምላክ የሁሉ ነገር ፈጣሪ አይደለም"። Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60. ትራይፎም አምላክ እና መልአክ የተለያዩ ምንነቶች እንደሆነ ሲነግረው ዮስጦስም የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል የሚመጣው ሌላው አምላክ ኢየሱስ እንጂ የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የተባለው አንድ አምላክ አብ እንዳይደለ ነግሮታል፦ "አንተ እንዳልከው "ሁለቱ መልአክ እና አምላክ ነበሩ" ቢሆን በጣም ትንሽ ዕውቀት ያለው ሰው ካልሆነ በቀር፦"የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል ላይ ታየ" ብሎ ለማስረገጥ አይደፈርም"። Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60.
إظهار الكل...
02:03
Video unavailableShow in Telegram
የውኃ ጥምቀት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ "ባፕቲዝማ" βάπτισμα የሚለው ቃል "ባፕቲዞ" βᾰπτῐ́ζω ማለትም "ነከረ" "አጠለቀ" "አጠመቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መንክር" "ጥልቀት" "ጥምቀት" ማለት ነው፦ ማርቆስ 1፥4 ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ። ἐγένετο Ἰωάνης ὁ βαπτίζων ἐν τῇ ἐρήμῳ κηρύσσων βάπτισμα μετανοίας εἰς ἄφεσιν ἁμαρτιῶν. ዮሐንስ የሚያጠምቀው ጥምቀት የንስሐ ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት ሲሆን ሰዎች ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር፦ ማርቆስ 1፥5 ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር። ኢየሱስም የንስሐ ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ፥ ሲጠመቅ ጸሎት ይጸልይ ነበር፦ ማርቆስ 1፥9 በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ። ሉቃስ 3፥21 ሕዝቡም ሁሉ ከተጠመቁ በኋላ ኢየሱስ ደግሞ ተጠመቀ። ሲጸልይም ሰማይ ተከፈተ። የተጠመቀበት ምክንያት ጽድቅን ሁሉ ለመፈጸም ነው፥ ጽድቅ አምላክ ያዘዘው ትእዛዝ መታዘዝ ሲሆን ዓመፃ ደግሞ አምላክ የከለከለውን ማድረግ ነው። ኢየሱስ ጽድቅን በወደድ እና ዓመፃን በመጥላት የአምላኩን ትእዛዝ ለመጠበቅ እና ለማድረግ ተጠመቀ፦ ማቴዎስ 3፥15 "ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና" ዕብራውያን 1፥9 "ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ" ዮሐንስ 14፥31 "አብም እንዳዘዘኝ እንዲሁ አደርጋለሁ" ዮሐንስ 15፥10 "እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ" ኢየሱስ የተጠመቀው የውኃ ጥምቀት ብሉይ ኪዳን ላይ ያመ ጥምቀት ነው። የብሉይ ኪዳን ሰዎች የውኃ ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት ይጠመቁ ነበር፥ ይህንን የውኃ ጥምቀት የዕብራውያን ጸሐፊ ጥምቀት ይለዋል፦ ዘኍልቍ 8፥7 ታነጻቸው ዘንድ እንዲህ ታደርግላቸዋለህ፤ ኃጢአትን የሚያነጻውን ውኃ እርጫቸው። ዕብራውያን 9፥10 እስከ መታደስ ዘመን ድረስ ስለ ምግብ፣ ስለ መጠጥ፣ ስለ ልዩ ልዩ "መታጠብ" የሚሆኑ የሥጋ ሥርዓቶች ብቻ ናቸውና። μόνον ἐπὶ βρώμασιν καὶ πόμασιν καὶ διαφόροις βαπτισμοῖς, δικαιώματα σαρκὸς μέχρι καιροῦ διορθώσεως ἐπικείμενα. እዚህ አንቀጽ ላይ "መታጠብ" ለሚለው የገባው ቃል "ባፕቲዝሞስ" βαπτισμός ሲሆን "ጥምቀት" ማለት ነው፦ ዕብራውያን 6፥2 እርሱም ከሞተ ሥራ ንስሐ፣ በአምላክ እምነት፥ ስለ ጥምቀቶች፣ እጆችንም ስለ መጫን፣ ስለ ሙታንም ትንሣኤ እና ስለ ዘላለም ፍርድም ትምህርት ነው። እዚህ አንቀጽ ላይ "ጥምቀቶች" ለሚለው የገባው ቃል "ባፕቲዝሞን" βαπτισμῶν ሲሆን ይህ የውኃ ጥምቀት እስከ መታደስ ዘመን ድረስ ማለትም ኢየሱስ እስኪመጣ ድረስ የነበረ የብሉይ ሕግ ነው፥ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ስለ የውኃ ጥምቀት ምንም አላስተማረም። ቅሉ ግን እንደተናገረ አስመስለው አስዋሽተውታል፦ ማርቆስ 16፥16 ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። የሚገርመው የማርቆስ ወንጌል የጥንት ዐበይት የግሪክ ዕደ ክታባት ኮዴክስ ቫቲካነስ እና ኮዴክስ ሲናቲከስ የሚጨርሰው ማርቆስ 16፥8 ላይ ነው፥ New International Version፦ "ከ 9-20 ያሉትን አናቅጽ ጥንታውያን እደ ክታባት እና ሌሎች የጥንት ምስክሮች የላቸውም"The earliest manuscripts and some other ancient witnesses do not have verses 9–20" በማለት ሐቁን ሳይሸሽግ ተናግሯል። አብዛኞቹ የአዲስ ኪዳን ምሁራን ከ 9-20 ያሉት የማርቆስ የመጀመሪያ ጽሑፎች ክፍል እንዳልነበሩ ነገር ግን በኋላ የተጨመሩ እንደሆነ ይስማማሉ። ኢየሱስ "የውኃ ጥምቀት አጥምቁ" ብሎ አላዘዘም። ቅሉ ግን እንደተናገረ አስመስለው አስዋሽተውታል፦ ማቴዎስ 28፥19 “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው። "በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው" የሚለው በግሪክ ዕደ ክታባት ላይ የተጨመረ ሲሆን ማቴዎስ በጻፈው በመጀመርያው በዕብራይስጥ የተቀመጠው ቃል ግን "አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ" የሚል ነበር፥ ይህንን አሽቀንጥረው ስለጣሉት የሚያሳዝነው ይህ ንግግር ጠፍቷል። በዚህ ዙሪያ ከዚህ ቀደም የጻፍኩት መጣጥፍ ስላለ እንድትመለከቱት በትህትና እጠይቃለው፦ https://t.me/Wahidcom/3585 ስናጠቃልልለው ውስብስብ እና ውዝግብ የሌለበትን የአሏህን የተፈጥሮ ጥምቀት እንድትይዙ ጥሪያችን ነው፦ 2፥138 የአሏህን መንክር ያዙ! በመንከርም ከአሏህ ይበልጥ ያማረ ማነው? "እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን" በሉ፡፡ صِبْغَةَ اللَّهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُونَ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! እኛንም በተፈጥሮ ጥምቀት ጸንተው ከሚሞቱ ሙሥሊም ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
إظهار الكل...